TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የትግራይ ዲያስፖራ ፌስቲቫል!

2ኛው ዓለምቀፍ የትግራይ ዲያስፓራ ፌስተቫል ለመካሄድ የሚያስችል ዝግጅት
#መጠናቀቁን የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት አስታውቋል፡፡

ፌስቲቫሉ በተለያዩ የዓለም ሃገራት የሚገኙ የትግራይ ዲያስፓራ ማህበረሰብ በክልሉ ብሎም በሃገራቱ እየተከናወኑ ባሉት የሰላም የዴሞክራሲና የልማት ስራዎች ተሳታፊ ለማድረግ ያለው ነው ተብሏል፡፡

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ የከተማ ልማትና ንግድ ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር #አብርሃም_ተከስተ ዝግጅቱን አስመልክቶ በሠጡት መግለጫ ፌስቲቫሉ የትግራይ ዲያስፓራ ስለሃገራቸውና ስለ ክልላቸው ተጨባጭ ሁኔታ ተገንዝበው ለትግራይ ህዝብ ሰላምና ደህንነት በተደራጀ መልኩ የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ለማድረግ ነው፡፡

ፌስቲቫሉ ዲያስፓራውን በክልሉ በሚካሄደው የንግድ የኢንቨስትመንትና የኢንዱስትሪ ልማት እንቅስቃሴዎች ተሳታፊ ለማድረግ ነው ያሉት ዶክተር አብርሃም የፐብሊክ ዲኘሎማሲውን በማጠናከር በኢትዮ ኤርትራ የተጀመረውን የሰላም ግንኙነት ተጠናክሮ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ነው፡፡

ዋናው ፌስቲባል ከሃምሌ 24 -ሃምሌ 3ዐ/ 2ዐ11 ዓ.ም ድረስ የሚካሄድ ሲሆን የህዝባዊ ወያነ ሐርነት ትግራይ /ህወሓት/ የተመሰረተበትን ቀን ምክንያት በማድረግ ከየካቲት 11/2ዐ11 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ ስነ-ስርዓቶች እንደሚካሄደ ተገልጿል፡፡

ምንጭ፦ ebc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ባህር ዳር🔝

#በኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየታዩ ያሉት የፀጥታ ችግሮች በርካቶች ከቀያቸው #እንዲፈናቀሉ እና የሰው ሕይወት በየቦታው #እንዲቀጠፍ ምክንያት እየሆኑ ነው፡፡ ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ 51 አህጉረ ስብከቶች ስለሰላም የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ እና አተገባበር ዙሪያ ለሃይማኖት አባቶች እና ለምዕመናን በባሕር ዳር ስልጠና እየሰጠች ነው፡፡

በባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ደብረ ፀሐይ ሰላም አድርጊው ማርያም ገዳም አስተዳዳሪ መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ ፍቅረ ማርያም ‹‹አሁን ላይ በሀገሪቱ የተፈጠረው የሰላም እጦት የሰው ልጆች ለእግዚአብሔር ያለመታዘዝ ምንጮች ናቸው፤ እግዚአብሔር ግን በመጽሐፍ ቅዱስ በምድር ላይ ሳለን የሰላም አስፈላጊነት የሁሉም ነገር ቁልፍ ናት ብሎ አስተምሮናል፤ ይህ ሰላም እንዲኖር የሃይማኖት አባቶች በጸሎት እና አስተምህሮ ከዚህ የበለጠ መሥራት እንደሚጠበቅብን አመላካች ነው›› ብለዋል፡፡

የፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ካቴድራል አስተዳዳሪ መልአከ ገነት ሰፊው ወልደትንሳኤ ካህናት ሕዝቡ ሰላምን ያገኝ ዘንድ እንዲያስተምሩ አደራ እንደተሰጣቸው ተናግረዋል፡፡ ‹‹ካህናት ስለሰላም የሠራነው ሥራ ስለምን በዚህ ትውልድ ፍሬ #አላፈራም? ሕዝቡስ ስለምን ሰላምን አጣ? ብለን ሁከት የሚፈጥር እንዳይኖር በትኩረት እንድንሠራ ኃለፊነት አለብን›› ብለዋል፡፡

የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብፁዕ አቡነ #አብርሃም ደግሞ ሀገሪቱ ዜጎች እየተሰደዱ፣ ሀብት ንብረታቸው እየወደመ እና ሕይወታቸውን እያጡ ያሉበት ወቅት ላይ እንደምትገኝ ነው የተናገሩት፡፡ ሁኔታው ቤተ ክርስቲያን #ስለሰላም ከዚህ በላይ መሥራት እንዳለባት አመላካች መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

ብጹዕነታቸው ‹‹ሰላምን የማይሻ ሰው ውስጡ የፍርሃት ባሕር አለ፡፡ በፍርሃት የሚቅበዘበዝ ትውልድ ደግሞ የተዋቡ ከተሞችን ዶግ አመድ ያደርጋል›› ነው ያሉት፡፡ ግጭት የሕጻናት እና እናቶችን ዋይታ እንደሚያበዛና ለፀብ የሚያነሳሱ ሰበቦችና መደለያዎች ግን በርካታ መሆናቸውንም አመልክተዋል፡፡ ‹‹የምንመራው ሕዝብ #ሰላም_ከሌለው አይጸድቅም፤ ጽድቅ የማያገኝ የእግዚአብሔር ትውልድ እንዳይኖር ደግሞ የሃይማኖት አባቶች ከዚህም በላይ መሥራት ይኖርብናል›› በማለትም አቡነ አብርሃም አሳስበዋል፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethioia
ገናሌ ዳዋ 3🔝

"ሀይ ፀግሽ የመብራት ሃይል ዋና ስራ አስኪያጅ ዶክተር #አብርሃም ገናሌ ዳዋ 3 ሃይል ማመንጫ ነው ሚገኙት ቅድም ለ20 ደቂቃ የቆየ ውይይት አርገን ነበር። ግድቡንም ጎብኝተናል። ለሚዲያዎችም ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጥቷል። Ib"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የታላቁን የህዳሴ ግድብ ግንባታ በ2015 ዓ.ም ለማጠናቀቅ እቅድ ተይዟል!

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል የታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ የመሃል ክፍል የአርማታ ሙሌት ስራ መጀመሩን አስታወቀ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር #አብርሃም_በላይ ከፋና ብሮድካስቲንግ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት የግድቡ ግንባታ በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ ነው።

የሁለቱ ቅድመ ሃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የብረታ ብረት ገጠማ እና ኤሌክትሮ መካኒካል ስራም ግማሽ ተጠናቋል ነው ያሉት። የግድቡ አካል ከሆኑት አንዱ የሆነው ኮርቻ ግድብ (ሳድል ዳም) ግንባታው ከሁለት ወራት በኋላ እንደሚጠናቀቅም ተናግረዋል። አሁን ላይ ግድቡ ከ16 ሚሊየን ሜትር ኪዩብ በላይ አለት የተሞላ ሲሆን፥ ኮንክሪት ለብሶ የማጠናቀቂያ እና የለቀማ ስራ ላይ መድረሱንም ገልጸዋል።

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-09-24

Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia