TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ጅማ ዩኒቨርሲቲ🔝ዛሬ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር #ዐብይ_አህመድ እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ተገኝተው 40,000 ተመልካች የሚይዘውን የጅማ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየምና ስፖርት አካዳሚ በይፋ #ይመርቃሉ

ቪድዮ፦ ቢንያም ግርማይ(TIKVAH-ETH)
ፎቶ፦ ናቶሊ(TIKVAH-ETH)
@tsegabwolde @tikahethiopia
''ወንጀለኞቹ ማንም ይሁኑ ማን . . . አድነን ለሕግ ማቅረባችን አይቀሬ ነው'' ጠ/ሚ ዶ/ር #ዐብይ_አህመድ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዶክተር #ዐብይ_አህመድ የአፍሪካ ህብረት ሽልማትን ወስደዋል!!
ዶክተር አብይ አህመድ ተሸለሙ!
.
.
ዶክተር #ዐብይ_አህመድ የአፍሪካ ህብረት ሽልማትን ወስደዋል፡፡ ሽልማቱ በስርዓተ ጾታ እኩልነት ዙሪያ ጥሩ ተግባራትን ለፈጸሙ ግለሰቦች የሚሰጥ መሆኑ ተገልጿል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባሳለፍናቸው ወራት ውስጥ በአመራር ስፍራዎች ላይ #የሴቶችን_ተሳትፎ አሳድገዋል፡፡ ለአብነት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ግማሽ አባላት ሴቶች እንዲሆኑ አድርገዋል፡፡ ሴት ፕሬዝደንት፣ መከላከያ ሚንስትር፣ የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ እና የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት መሾማቸው ተነስቷል፡፡

#ሴቶች በሙስና ወንጀሎች የመሳተፍ እድላቸው አነስተኛ መሆኑን እና በስራቸው ውጤታማ መሆናቸውን በተደጋጋሚ እንደተናገሩ ተገልጿል፡፡ በስርዓተ ጾታ አቀንቃኞች ዘንድ ዶክተር ዐብይ እንደሚወደሱም ተመላክቷል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ ያገኙት ሽልማት በአፍሪካ ህብረት እና በመንግስታቱ ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን በጋራ የሚዘጋጅ መሆኑ ተነግሯል፡፡

ምንጭ፦ አፍሪካ ኒውስ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
‹‹እየተገነባ ያለው #የመከላከያ_ሠራዊት ዛሬ የሁሉንም #ሉዓላዊነት የሚጠብቅ ነገ ደግሞ የሕዝብ ውክልና አግኝታችሁ ሥልጣን የምትይዙ ተረክባችሁ የምታስቀጥሉት ተቋም ነው›› ጠቅላይ ሚኒስትርና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዶክተር #ዐብይ_አህመድ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ለተማሩና ሐሳብ ላላቸው ዜጎች #የብድር ሥርዓት ሊዘረጋ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አሕመድ ተናገሩ። የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስር ዶክተር #ዐብይ_አህመድ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ባለፉት ጊዜያት ትልልቅ ሐሳብ ላላቸው ሳይሆን ትልልቅ ሀብት ላላቸው ብቻ ከፍተኛ የብድር አገልግሎት ስትሰጥ ቆይታለች፤ በዚህም የሚፈለገው ለውጥ ሳይመዘገብ ቀርቷል፡፡

Via አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
መሪዎቹ አርባምንጭ ገብተዋል...

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠ/ሚ ዶ/ር #ዐብይ_አህመድ እና የኬንያው ፕሬዘዳንት #ኡሁሩ_ኬንያታ አርባምንጭ ከተማ ገብተዋል። መሪዎቹ አርባምንጭ ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

ፎቶ፦ Gamo Zone Administration Public Realtion office
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ባህር ዳር🛬አመሻሹን የኢ.ፌ.ዴሪ ጠ/ሚ ዶ/ር #ዐብይ_አህመድ ባህር ዳር ከተማ ገብተዋል። በምን ጉዳይ ባህር ዳር እንደሄዱ ግን እስካሁን የታወቀ ነገር የለም።

ፎቶ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ተቋማዊ ለውጥ የጋራ ኮሚቴ በዛሬው ዕለት ከጠቅላይ ሚኒስትር #ዐብይ_አህመድ (ዶ/ር) ጋር በሸራተን አዲስ እየተወያየ ነው፡፡

#etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፕሬዝዳንትና ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአንድ ቤተ መንግስት ውስጥ እንዲሆኑ ሊደረግ ነው። ቤተ መንግስቶችን በማደስና ህዝብ እንዲጎበኛቸው በማድርግ ለገቢ ማስገኛነት እንዲውሉ እየተሰራ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር #ዐብይ_አህመድ አስታውቀዋል፡፡ በዛሬው ዕለት በምክር ቤቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ 386 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር ሆኖ በተዘጋጀው ረቂቅ በጀት ዙሪያ ለተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ነው ቤተ መንግስቶችን በማደስ ለገቢ ማስገኛነት አገልግሎት እንዲውሉ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት።

🗞ቀን ሃምሌ 1/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia