TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Oceanስክሪፕቶ

ድርጅታችን በከፍተኛ  ጥራት የሚያመርተውን "Ocean" ስክሪፕቶ በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች የሚያከፋፍሉለት ውስን ወኪል ነጋዴዎች አወዳድሮ በመምረጥ መመደብ ይፈልጋል።

ስለሆነም በዘርፉ የተሰማራቹ ፍላጎትና  አቅም ያላችሁ አከፉፉዮች  ከታች ባሉት ስልክ ቁጥሮች በመደወል ለወኪል አከፋፋይ ያዘጋጀነውን የልዩ ሽያጭ ዋጋ ስምምነት ውል በማድረግ የድርጅታችን ወኪል ይሁኑ::

+251901835555
+251901832222
#እገታ

በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች ላይ በሰላማዊ ዜጎች ላይ የሚፈፀመው እገታ መባባሱን ነዋሪዎችን ዋቢ አድርጎ ቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ ዘግቧል።

በቅርብ ጊዜ እገታ ተፈፅሞባቸዋል ከተባሉ አካባቢዎች አንዱ የምስራቅ ሸዋ ዞን ፈንታሌ ወረዳ ነው።

በዋናው የፌዴራል መንገድ ላይ ወረዳውን አቋርጠው በተሽከርካሪ ሲሄዱ የነበሩ 10 የግንባታ ባለሞያዎች በታጣቂዎች ታግተው 20 ቀናት ያህል ከቆዩ በኃላ የተጠየቁትን የማስለቀቂያ ገንዘብ ከፍለው ከእገታ ነፃ ወጥተዋል።

ከታጋቾቹ አንዱ እገታውን የፈፀሙት የ #ሸኔ / የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ታጣቂዎች ናቸው ያሉ ሲሆን አጋቾቹ " ለመገናኛ ብዙሃን መረጃ ከሰጠን እንደሚገድሉን አስጠንቅቀውናል " ብለዋል።

በወቅቱ የግንባታ ባለሞያዎቹን ጨምሮ 30 የሚደርሱ የአንድ ድርጅት ሰራተኞች በአንድ ተሽከርካሪ ሆነው ሲጓዙ የነበረ ሲሆን 20 የሚደርሱት ሴቶች እንደነበሩ አስታውሰዋል።

ሴቶቹን ለአንድ ቀን ካሳደሯቸው በኃላ በነፃ ሲለቋቸው ሌሎች ታጋቾች ግን አጠቃላይ ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ ከፍለው ከ20 ቀን በኃላ መለቀቃቸውን ገልጸዋል።

በምዕራብ ሸዋ ዞን ዳንዲ ወረዳ በፊንጫ ጎደቲ ከ10 ቀናት በፊት 8 አርሶ አደሮች ታግተው እያንዳንዳቸው ከ250 እስከ 300 ሺህ ብር ከፍለው ተለቀዋል።

አንድ የአካባቢው ተወላጅ ፤ ታጣቂዎቹ በቀጥታ ወደ ሰዎች ቤት በመሄድ፣ ስልካቸውንም በመቀማት ነው አግተው የሚወስዱት ብለዋል።

በኃላም ታጋቾች በጎረቤትና በቤተሰብ ስልክ ደውለው አጋቾች የጠየቁት ብር እንዲከፈላቸው ተደርጎ እንደሚለቀቁ አስረድተዋል።

ስምንቱ አርሶ አደሮች ከ 250 ሺህ እስከ 300 ሺህ ብር ተጠይቀው ከብት ያለው ሽጦ ፤ ዘመድ ያላቸውም ተበድረው ከእገታው ወጥተዋል ብለዋል።

ታግተው የተለቀቁት ሰዎች እንደሚናገሩት ፤ እገታውን የሚፈፅሙት መንግስት " ሸኔ " የሚላቸው ኃይሎች እንደሆነ የገለፁት ተወላጁ ከታጋቾች ባገኙት ቃል አጋቾቹ " ታጋዮች ነን ለህዝብ ነው የምንዋጋው ለመኖር የሚያስፈልገንን ገንዘብ ማግኘት አለብን " በሚል ሰዎችን ይዘው እንደሚሄዱ ነው የገለጹት።

" እነሱ ይሁኑ ፤ በእነሱ ስም የተደራጁ ይሁኑ በግልፅ ባይታወቅም አንድ መረጃ ከተናገራችሁ ' በህይወት አትኖሩም ' የሚል ማስጠንቀቂያ ሰጥተው ነው የሚለቁት " ያሉት የአካባቢው ተወላጅ " በዚህም የተለቀቁ ሰዎች ምንም ነገር መናገር ይፈራሉ። " ብለዋል።

የሰሞኑን እገታ ብቻ ሳይሆን በ2 ወራት በፊት 3 ሰዎች ታግተው ከ300 ሺህ እስከ 350 ሺህ ብር ከፍለው መውጣታቸውን አመልክተዋል።

በአካባቢው በተደጋጋሚ ጊዜ እየተፈፀመ ባለው እገታ ምክንያት ነዋሪው በስጋት ቄዬውን እየለቀቀ እየሸሸ ነው ሲሉ አሳውቋል።

ከዚህ በተጨማሪ ከሳምንታት በፊት የ " አሉቶ ላንጋኖ ጂኦተርማል ፕሮጀክት " ሰራተኞች በታጣቂዎች ታግተዋል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልም ምን ያህል ሰራተኞች እንደሆኑ ባይገልጽም " ሰራተኞቹ ባልታወቁ ኃይሎች መታጋታቸውን አመልክቷል።

የስራ ባልደረቦቻቸው የታገቱት 6 ሰራተኞች እንደሆኑ ገልጸዋል።

እነዚህ ሰራተኞች አሁን ምን ላይ እንዳሉ አይታወቅም። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና ባልደረቦቻቸው ለታጋቾች ደህንነት በመስጋት መረጃ ለመስጠት እንደማይፈልጉ ተነግሯል።

ጥቅምት 9 / 2015 ዓ/ም በሰሜን ሸዋ ዞን፣ የኢስት ሲሚንቶ ፋብሪካ ሰራተኞች የሆኑ " የቻይና ዜጎች ታግተው " መወሰዳቸውን ነዋሪዎችን ዋቢ አድርጎ " አዲስ ስታንዳርድ " ዘግቧል።

ነዋሪዎች እንዳሉት የሸኔ ታጣቂዎች ከሀምቢሶ ከተማ በአምስት ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኘውን ኢስት ሲሚንቶ ፉብሪካ በመቆጣጠር በቁጥር ያልታወቁ የቻይና ዜጎችን አግተው ወስደዋል።

ታጣቂዎቹ " ፊቼ " ን ለመቆጣጠር በማሰብ ጋረ ሹሂ በሚባል ቦታ ላይ ከመንግስት ጸጥታ ኃይሎች ጋር ረዘም ያለ እና ከፍተኛ ውጊያ ማድረጋቸውን ነዋሪዎቹ ገልጸው ታጣቂዎቹ ወደ ጫካ ሲያፈገፍጉ የቻይና ዜጎች አግተው ነው ብለዋል።

በኦሮሚያ ፤ ስለተባባሰው እገታ የክልሉ መንግሥት ኮሚኒኬሽን ለቪኦኤ ሬድዮ በሰጠው ቃል ድርጊቱን የሚፈፅሙት የሽብርተኛ ቡድኑ " ሸኔ ነው " ብሏል።

ይህን የሚፈፀመው የፀጥታ ኃይል ስምሪትን እያየ ነው ሲል ገልጿል።

" ቡድኑ አለሁ ለማለት እና ኪሱን ለማደለብ በንፁሃን ላይ እገታ ይፈፅማል ፣ ያፍናል ፣ ይገድላል " ያለው ክልሉ ፤ " መንግሥት ዜጎች ወጥተው እንዲገቡ ሰላም እንዲረጋገጥ የተቻለውን እየሰራ ነው " ብሏል።

" ሰላም የመላ ህዝብ ነው " ክልሉ " ህዝቡ ተደራጅቶ ሰላሙን ማስጠበቅ ፣ ልማቱን ማስቀጠል አለበት። እኛ እያንዳንዱ ቀበሌ እና ቤተሰብ ላይ የፀጥታ ኃይል ስምሪት መስጠት አንችልም። ስለዚህ ህብረተሰቡ ከመንግሥት የፀጥታ ጋር አብሮ በመስራት ፣ መረጃ በመስጠት ፤ ተደራጅቶ አካባቢውንም መጠበቅ አለበት " ሲል ገልጿል።

የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት / ኦነሰ በበኩሉ መሰል ድርጊት እንደማይፈፅም እና እጁ እንደሌለበት ገልጾ " ይህ የሽፍቶች ስራ ነው " ብሏል ለቪኦኤ ሬድዮ በሰጠው ቃል።

" ሁኔታው በስልጣን ላይ ካለው አካል አቅም በላይ እየሆነነው " ያለው ታጣቂ ቡድኑ " ይህ የሆነው ደግሞ በየቦታው ሽፍታ በመብዛቱ ነው " ሲል ገልጿል።

የታጣቂው ቡድን ፤ " የእገታ ተግባር ላይ ተሰማርተው የሚገኙት ኃይሎች ከመንግስት ኃይል ጋር ግንኙነት ሊኖራቸውም ላይኖራቸውም ይችላል " ብሏል።

" ነፍጥ ይዘው መሰል ድርጊት (እገታ) የሚፈፅሙ ተበራክተዋል ፤ በዚህ ምክንያት በስልጣን ላይ ያለው አካል የህዝብን ደህንነት ማስጠበቅ አቅቶታል " ያለው ቡድኑ " ሰላም እና ዴሞክራሲ በሰፈነበት ሀገር መንግት ነኝ የሚል አካል ነበር ተጠያቂነት ወስዶ ማስተካከል የነበረበት ይህን ግን እያየን አይደለም ስለዚህ ወንጀለኞች ነፍጥ አግኝተው መሰል ወንጀል ፈፅመው ራሳቸውን እያበለፀጉ ናቸው " ብሏል።

@tikvahethiopia
#ጥቆማ

የኢሰመኮ 3ኛ ዙር የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል የፎቶግራፎች እና የአጫጭር ፊልሞች ውድድር ላይ ተሳተፉ !

መኖሪያ ቤት/ቦታ ማለት ለአንድ ሰው ወይም ለአንድ ቤተሰብ ምን ማለት ነው ?

ሕይወት፣ ትርጉም ያለው ሕይወት፣ ምንድን ነው ? የአንድ ኢትዮጵያዊት ሴት፣ ወይም የአካል ጉዳተኛ ወይም የተፈናቃይ ወይም የአረጋዊ ሕይወት ምን ይመስላል ?

በሕይወት እና በመኖሪያ ቤት ዙርያ እነዚህን እና የመሳሰሉ ጥያቄዎች ለኪነጥበብ አፍቃሪዎች፣ ለኪነጥበብ ሙያ ተማሪዎች፣ ባለሞያዎች እና አማተሮች እንዲሁም ለመገናኛ ብዙኃን አባላት እና ሌሎችም በኪነጥበብ እና በሰብአዊ መብቶች መካከል ያለውን ትስስር ማሳየት ለሚፈልጉ ሁሉ፣ በኢሰመኮ አዘጋጅነት በሚካሄደው የ3ኛው ዙር የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል የፎቶግራፍ እና የአጫጭር ፊልሞች ውድድር የቀረቡ ናቸው።

ኑ፣ ተሳተፉ፣ አብረን እንድናሰላስል የሚረዱ የፎቶግራፍ እና የአጫጭር ፊልም ሥራዎቻችሁን ለዕይታ አቅርቡ!
በውድድሩ ለመሳተፍ እና ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ዝርዝሩን በዚህ ይመልከቱ - https://bit.ly/46sReAw
ግሎባል ባንክ

ይገምቱ ይሸለሙ!!

በቴሌግራም ቻናላችን ብቻ የጨዋታውን ትክክለኛ ውጤት ለገመቱ 3 እድለኞች የ200 ብር ካርድ ይሸለማሉ፡፡

የቴሌግራም ቻናላችንን ለማግኘት ይህን ሊንክ ይጠቀሙ
https://publielectoral.lat/Globalbankethiopia123

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ
ለጋራ ስኬታችን
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች መታሰራቸው ተገለፀ። እንዚህ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ሊውሉ የቻሉት ፦ - ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት፣ - ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ - ከኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የተውጣጣ ግብረ-ኃይል ከሙስናና ሕገወጥ ተግባር ጋር በተያያዘ ክትትልና ምርመራ ሲያደርግ ከቆየ በኃላ ነው ተብሏል። ተጠርጣሪዎቹ ፤ ተገልጋዮች በመደበኛ…
" ... ሕገወጡ የድርጅቱ #ኦንላይን_ሲስተም ሙሉ በሙሉ ተቋርጦ ፕሮፌሽናል በሆኑ የሙያ ተቋማት በአዲስ መልክ መልማት ይኖርበታል " - አምባሳደር ሱሌማን ደደፎ

ከሰሞኑ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ታምሩ ግንበቶ አዋልሶ ጨምሮ 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ከሙስናና ሕገወጥ ተግባር ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር ማዋላቸው ይታወቃል።

ይህንን በተመለከተ የተለያዩ አስተያየቶች እየተሰጡ ይገኛል።

#የግል አስተያየታቸውን ካጋሩት ውስጥ የቀድሞ በተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ (UAE) የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው ያገለገሉት ሱሌማን ደደፎ አንዱ ናቸው።

አምባሳደር ሱሌማን ፤ የተወሰደው እርምጃ የዘገየ ቢሆንም የይበል የሚያሰኝ ነው ብለዋል።

ነገር ግን ይህ ብቻውን በቂ እንዳልሆነ ገልጸዋል።

" እነዚህ ሰዎች ዘርግተው የሚጠቀሙበትና በበርካታ ደላሎች የሚሠራበት ሕገወጡ የድርጅቱ #ኦንላይን_ሲስተም ሙሉ በሙሉ ተቋርጦ ፕሮፌሽናል በሆኑ የሙያ ተቋማት በአዲስ መልክ መልማት ይኖርበታል " ብለዋል።

አምባደሩ ፤ " ዛሬም የኢትዮጵያ ፓስፖርት በበርካታ የመካከለኛው ምሥራቅ እና የባሕረ ሰላጤው ሀገራት በደላሎች ሱቆች ውስጥ በይፋ በመቸብቸብ ላይ ይገኛል  " ሲል ገልጸዋል።

" ዜጎቻችን ፓስፖርታቸውን ለማሳደስ እስከ 60,000 ብር የሚጠየቁበት፣ ከቪዛና ከፓስፓርት እድሳት እያንዳንዱ አገልግሎት ጠያቂ $100 ዶላር ላልታወቀ ግለሰብ ወይም ተቋም የሚከፍልበት አሠራር ዛሬም ስላለ በሥራ ላይ ያለው የኦንላይን ሲስተም scrap ተደርጎ በአዲስ መተካት ይኖርበታል። " ብለዋል።

ኦንላይን የቪዛ ጥያቄ አሁንም ሁለት ሦስት ጊዜ ካልተከፈለበት መልስ እንደማይሰጥ ይታወቃል ሲሉም አክለዋል።

ከዚህ በተጨማሪም ፤ አምባሳደር ሱሌማን ደደፎ ፤ ከክልል እስከ ፌዴራል ያሉት ሁሉም የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በጥብቅ መፈተሽ አለባቸው ብለዋል።

" ካሉን ቁልፍ የደህነት ተቋማት መካከል የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ መ/ቤት ምን ዓይነት ውርደት/ውድቀት ውስጥ እንደከተተን አይተናል። " ያሉት አምባሳደሩ " ተቋሙ ብቻውን ለዚህ አልበቃም፤ የባሰም እንዳለ ምንም ጥርጥር የለውም፣ በየዕለቱ የምናየውና የምንሰማው ጉዳይ ስለሆነ። " ሲሉ ገልጸዋል።

" ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ በሕጋዊ መንገድ ለማደስ ሁለት ሚሊዮን ብር ጉቦ የሚጠየቅበት አገር ውስጥ መሆናችንን ስናስብ እጅግ በጣም እንደነግጣለን "ም ብለዋል።

" መንግሥት ብዙ ቅድሚያ የሚሰጣቸው (Priorities) ቢኖሩትም የሥልጣን ብልግናና የአስተዳደር በደሎች፣ በተለይም ሌብነት አሁን ቅድሚያ ከምንሰጣቸው ጉዳዮች መካከል መሆን ይኖርባቸዋል " ሲሉ ገልጸዋል።

በዚህም ኢሚግሬሽን ብቻውን እንዳልበሰበሰ ታውቆ ከክልል እስከ ፌዴራል ያሉት ሁሉም የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በጥብቅ መፈተሽ አለባቸው ሲሉ አስገንዝበዋል።

@tikvahethiopia
ሃገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ኮንፈረንስ ላይ ጥናታዊ ጽሁፍ ማቅረብ ለሚፈልጉ የቀረበ ጥሪ

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር 4ኛውን ሃገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር አስመልክቶ ጥቅምት 29/2016 ዓ.ም ሃገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት የጥናትና ምርምር ኮንፈረንስ አዘጋጅቷል።

በመሆኑም በኢንፎርሜሽን አሹራንስ ፣ ኢንተሊጀንስ እና ኢንፎርሜሽን ዋርፌር እና ተዛማጅ በሆኑ የሳይበር ደህንነት የምርምርና ጥናት ውጤቶች ላይ ጥናታዊ ጽሁፍና የምርምር ውጤቶችን ማቅረብ የሚፈልጉ ሁሉ እንዲሳተፉ ጥሪ እያስተላለፍን።

የምርምርና ጥናታዊ ጽሁፎችን ከዚህ በታች በተገለጸው ኢ-ሜይል አድራሻ መሰረት እስከ ጥቅምት 23/2016 ዓ.ም መላክ የምትችሉ ሲሆን በኮንፈረንሱ የተመረጡ የጥናትና ምርምር ውጤቶች እውቅና የሚያገኙ መሆኑን እንገልጻለን።

Email address:  ncsconference@insa.gov.et
ለበለጠ መረጃ: ተረፈ ፈይሳ +251-9-13-23-90-36

ድረ ገጽ ፌስቡክ ዩትዩብ ቴሌግራም

ትዊተር ቲክቶክ
‘ታታሪዎቹ’/ ቀጠሌዋን በቅርብ ቀን
****************
‘ታታሪዎቹ’/ ቀጠሌዋን የሁለተኛ ዙር የአዋሽ ባንክ የስራ ፈጠራ ውድድር በቅርቡ የሚጀምር ሲሆን የፈጠራ ሀሳብ ያላቸው የውድድሩ ተሳታፊዎች ከጥቅምት 12 እስከ ህዳር 13 ቀን 2016 ዓ.ም በባንኩ በይነ መረብ (ኦን ላይን) ወይንም በሁሉም አዋሽ ባንክ ቅርንጯፎች በአካል በመገኘት ማመልከት ይችላሉ፡፡
Dorgommiin kalaqa hojii marsaa 2ffaa Qaxaleewwan Baankii Awaash yeroo dhihootti kan eegalu yoo ta'u dorgomtoonni yaada kalaqaa qabdan Onkololeessa 12 bara 2016 haga Sadaasa 13 bara 2016 A.L.I tti Marsareetii Baankii Awaashiifi dameelee Baankii Awaash hundatti qaamaan argamuun galmaa'uu ni dandeessu.
https://tatariwochu.awashbank.com
#AwashBank #TATARIWOCHU #Qaxaleewwan #Empowering_The_Visionaries #Coming_Soon #Ethiopia #ኢትዮጵያ
#ደራ_ወረዳ #ትኩረት

በደራ ወረዳ ያለው የፀጥታ ችግር አሁንም #አሳሳቢ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ፣ የሰዎች ህይወት እያለፈ ፣ ንብረትም እየወደመ መሆኑን ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

የደራ ወረዳ ነዋሪዎች በሰጡት ጥቆማ አንድ የቀድሞ የኦሮሚያ ፖሊስ አባል የልጆቻቸው እናት የሆነች ሚስታቸውን ከ " ኦነግ ሸኔ " ታጣቂዎች ጋር በመወገን ገድለዋል ብለዋል።

አንድ ቃላቸውን ለ ' ቲክቫህ ኢትዮጵያ ' የሰጡ የሟች የቅርብ ቤተሰብ ነኝ ያሉ ግለሰብ ፤ " በደራ ጁሩ የተባለ አካባቢ አንድ የቀድሞ የኦሮሚያ ክልል የፓሊስ አባል ከኦነግ ሸኔ ጋር በመወገን የአራት ልጆቹን እናትና የ5 ወር ነፍሰጡር ሚስቱን ገድሏል " ሲሉ ተናግረዋል።

ሌላኛው የሟች የቅርብ ቤተሰብ ይህ ግድያ በጥቅምት 6 ቀን 2016 ዓ.ም ፤ " ጁሩ " የተባለ አካባቢ ላይ እንደትፈጸመ አስረድተው፣ " የሟቿን እናት ጨምሮ ሌሎች የቤተሰቡ አባላት ጉዳት ደርሶባቸዋል። እኛም ልባችን ተሰብሮ አለን " ብለዋል።

በሌላ በኩል ፤ ሌላኛው የዓይን እማኝ #ጥቅምት_9 በገለጹት መሠረት፣ በደራ ወረዳ " ቆሮ ግንደ በርበሬ " ቀበሌ የኦነግ ሸኔ ጦር አካባቢውን እና መንደሩን ካቃጠለ 2 ሴቶችን እና አንድ ወንድ ገድሏል ሲሉ ከሰዋል።

እንደ ነዋሪው ገለፃ ን በታጣቂ ቡድኑ የተገደሉት ፀጋ እምነት፣ ጌታው አቤቱ እና ለግዜው ስሟን ያላወቁት ሴት ናቸው።

እኚሁ እማኝ ፤ " በመንግሥት ይሁንታ #የደራ_ህዝብ ከፍተኛ የዘር የፍጅት እየደረሰበት ነው " ብለዋል።

ይኸው ዘገባ እየተዘጋጀበት እስከነበረበት ጊዜ ድረስ ታጣቂ ቡድኑ ያለበትን ሁኔታ ሲያስሩዱም፣ " አሁንም በተለያዩ ቀበሌዎች እንደቀጠለ ነው። መንግሥት ምንም እርምጃ አልወሰደም። አድማሱን እያሰፋ ይገኛል " ነው ያሉት።

እኚሁን ምንጭ ጨምሮ ሌሎች የኦሮሚያ እና የአማራ ተወላጅ የደራ ወረዳ ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በገለጹት መሠረት ፣  አሙማ ገንዶ፣ ኢሉ ጎደ ጨፌ ፣ ሀርቡ ደሶ ፣ ዴኙ ወቤንሶ ፣ ጁሩ ዳዳ፣ ሀቼ ኩሳዬ፣ ካራ፣ ጎዲማ ሶስት ዋርካ፣ ጊሊ ወዲሳ፣  ቆሮ ግንደ በርበሬ፣ በዮ ኖኖ፣ ደንቢ ብርጄ፣ ባቡ ድሬ፣ ወሬ ገበሮ፣ መንቃታ፣ የተባሉና ላሎችም ቀበሌዎች እስካሁን (ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ) በታጣቂ ቡድኑ ስር ናቸው ይላሉ።

በሌላ በኩል ደግሞ ፤ በጉዳዩ ዙሪያ ቃላቸውን በስልክ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ የኦሮሚያ ክልል ተወላጅ፣ መከላከያ በአካባቢው እንዳለ፣ እንደ አጠቃላይ ግን ነዋሪው የጸጥታ ችግር ውስጥ እንደሆነ አስረድተው ስማቸው እንዳይጠቀስ ጠይቀዋል።

ሌላኛው ነዋሪ በበኩላቸው ፤ " ፋኖ ታጣቂዎችም አልፎ አልፎ ጥቃት እያደረሱ  ነው። በመካከል እየተጎዳ ያለው ንጹሐኑ ነው። መንግሥት እርምጃ ቢወስድ ምን አለ ? " ሲሉ ተይቀው ተጨማሪ ሀሳብ ለመስጠት ተቆጥበዋል።

የደራ ወረዳ ነዋሪዎች ባለፉት ሳምንታት በርካታ ሰዎች በታጣቂ ቡድኑ እንደታገቱ ፣ ከእገታ ለመለቀቅም ከ500 እስከ አንድ ሚሊዮን ብር እየተጠየቀባቸው እንደነበር፣ በጥቃቱ ከ200 በላይ ሰዎች እንደተገደሉ ፣ በርካታ ቤቶች እንዲሁም አብያተ ክርስቲያናት እንደተቃጠሉ መግለፃቸው ይታወሳል።

የኦሮሚያ ተወላጆችም ፤ " የፋኖ ታጣቂዎች በርካታ ቁጥራቸው ገና በትክክል ያልታወቀ ሰዎችን ገድለዋል " ማለታቸው አይዘነጋም።

መንግሥት " ኦነግ ሸኔ " እያለ በሚጠራው የታጣቂ ቡድን ታገቱ የተባሉ ሰዎች ከምን እንደደረሱ፣ የሟቾች ቁጥር ስንት እንደሆነ፣ የቤት ቃጠሎ ጥቃቱ እንደቆመና እንዳልቆመ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላቀረበው ጥያቄ ፣ " ከ500 ሺህ እስከ 1 ሚሊየን ብር የከፈሉ ተለቀዋል፣ ያልከፈሉትን ገድሏል " ብለዋል ሁኔታውን ሲከታተሉ የነበሩ ታማኝ ምንጭ።

ሌሎች ነዋሪዎች በበኩላቸው፣ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች የሚሰነዝሩትን ግድያ፣ ቃጠሎ፣ እገታ እንዳላቆሙ የሟቾችን ቁጥር ማወቅ እንዳልተቻለ ግን በመቶዎች የሚቆጠሩ እንደተገደሉ አስረድተው፣ ይህን ልጓም ያጣ ጥቃት መንግሥት ቸል ብሎታል የዓለም መንግሥታት፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ይወቁልን ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ ደረሰ እና አልቆምመ የተባለውን ጥቃት በተመለከተ ምን ምላሽ እንዳላቸው በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የደራ ወረዳ አስተዳዳሪ ለአቶ ሺበሺን በስልክና በአጭር ጽሑፍ እንዲያብራሩ ጥያቄ ቢያቀርብም #ምላሽ_ለመስጠት_ፈቃደኛ_አልሆኑም

አቶ ሺበሺ ከዚህ በፊት ጉዳዩን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ ችግሩን ለመቅረፍ የጸጥታ ኃይል እጥረት እንዳለ አስረድተው ነበር።

በተጨማሪ ከዞኑ አስተዳደር፣ ከክልሉ የጸጥታ ቢሮ የተደረገው ተመሳሳይ ሙከራ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሳይሳካ ቀርቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ በደራ ስላለው ሁኔታ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽንን ያነጋገረ ሲሆን " ክትትል ተጀምሯል ግን ገና አላለቀም " የሚል አጭር ምላሽ አግኝቷል።

መረጃው በአ/አ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ተጠናቅሮ የቀረበ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በወልቂጤ ከተማና በቀቤና ልዩ ወረዳ 'በወሰን ይገባኛል' ጥያቄ የተነሳው ግጭት በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የቀረበላቸው ታማኝ ምንጭ፣ " ግጭቱ ወደ ገጠሩ የመዛመት ሁኔታ ነው የሚስተዋለው። ወልቂጤ ከተማ አልፎ አልፎ  ካልሆነ በቀር የከፋ ነገር የለም " ብለዋል። ወሸርቤ፣ ወልቂጤ ዙሪያ ግጭቱ መዛመት አዝማሚያ ያንዣበበባቸው የገጠር ቦታዎች…
#Update

የጊዜያዊ ኮማንድ ፓስት በወልቂጤ ህብረተሰቡ በሰላም ወጥቶ እንዳይገባ እና ወደ መደበኛ ስራው እንዳይመለስ እያደረጉ ነው ያላቸውን ህገ-ወጥ ግለሰቦችን አስጠነቀቀ።

ኮማንድ ፖስቱ ፤ በየቦታው የተለያዩ ትንኮሳዎችን በመፍጠር የከተማው ማህበረሰብ እንዳይረጋጋ እያደረጉ ነው ያላቸውን በስም ጠርቶ ያልገለፃቸውን አካላት በጥብቅ አስጠንቅቋል።

በተጨማሪ ፤ በተሽከርካሪና በእግር የሚንቀሳቀሱ ዜጎች ላይ ህገ-ወጥ ድርጊት እየተፈጸመ እንደሆነ ገልጾ " ይህ መቆም መቻል አለበት " ብሏል። የሚፈፀመውን ድርጊት እንዲሁም ስለፈፃሚዎች በዝርዝር ያለው ነገር የለም።

ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስቱ ከዚህ ሰዓት ጀምሮ ይህን ማስጠንቀዊያ ሳይቀበል ወይም ተግባራዊ ሳያደርግ ቀርቶ በህገ-ወጥ ድርጊት የሚሳተፍ የየመዋቅሩ #የቀበሌ_አመራርና ግለሰብ በጸጥታው አካሉ ለሚወሰድበት #እርምጃ ኮማንድ ፖስጡ ኃላፊነት የማይወስድ መሆኑን በጥብቅ አስጠንቅቋል።

ከሰሞኑን በወልቃጤ ከተማ በተፈጠረ ግጭት የሰዎች ህይወት መጥፋቱ፣ ንብረትም መወደሙ የሚዘነጋ አይደለም።

@tikvahethiopia
#መቐለ

የመቐለ ከተማ አስተዳደር የተሰው ታጋዮች ቤተሰቦች በዘላቂ  ለማቋቋም የሚያስችል የ 11 ሚሊዮን ብር የመነሻ በጀት መመደቡ አስታወቀ። 

የመቐለ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ኤልያስ ካሕሳይ በማህበራዊ ሚድያ የትስስር ገፃቸው ባሰራጩት መረጃ መሰረት ፤ የከተማ አስተዳደሩ ጥቅምት 9 ቀም 2016 ዓ.ም ባካሄደው ሰብሰባ የሚከተሉት ወሳኔዎች አስተላልፈዋል።

1. በመቐለ ሰባት ክፍለከተሞች የሚገኙ የተሰው ታጋዮች ቤተሰቦች በ32 ቀበሌዎች በማህበር በመደራጀት የመሰቦ ስሚንቶ ለከተማው ነዋሪ እንዲያከፋፍሉ።

2. ለመነሻ የሚሆን ያለ ወለድ ሰርተው የሚመልሱት 11 ሚሊዮን ብር መመደቡ።  

3. የመቐለ ከተማ አስተዳደር በ32 ቀበሌዎች ስሚንቶ ለማከፋፈል ለሚደራጁት : የማከፋፈያ መጋዘን ሰርቶ እንዲያስረክባቸው።

4. የተሰው ታጋዮች ቤተሰቦች በሰሚንቶ ማከፋፈል ስራ ለሁለት አመት እንዲቆዩ።

5. በሁለት አመት ቆይታቸው የሚያጋጡማዋቸው እንቅፋቶች የከተማ አስተዳደሩ ቅድሚያ በመስጠት እንደሚፈታላቸውና እንደሚከታተላቸው ውሳኔ አስተላልፈዋል።

መረጃውን የመቐለ የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ነው ያደረሰን።

@tikvahethiopia
ይቆጥቡ፤ ይጓዙ!
ሲቢኢ ጉዞ የቁጠባ ሂሳብ
==============
ደንበኞች በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገራት ለሚያደርጉት ጉዞ ወጪ መሸፈኛ ገንዘብ አስቀድመው መቆጠብ እንዲችሉ የተዘጋጀ የቁጠባ ሂሳብ ነው፡፡ 

ሲቢኢ ጉዞ የቁጠባ ሂሳብ ከብር 1,000 ጀምሮ ይከፈታል፡፡

የቁጠባ ሂሳቡ የተለያዩ ጥቅሞች ያስገኛል፡፡

• ቆጣቢዎች በሀገር ወስጥ ጉዟቸው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ዲጂታል የክፍያ አማራጮች ተጠቅመው ለአየር ትኬት፣ ለቱሪስት መዳረሻዎች መግቢያ፣ ለሆቴል አገልግሎት እና ለመሳሰሉት ክፍያ በሚፈፅሙበት ወቅት ተመላሽ ያገኛሉ፤

• ዳያስፖራ ወይም የውጭ ሀገር ዜጎች የሲቢኢ ቱሪስት ካርድን ሲጠቀሙ እስከ 7 በመቶ የሚደርስ ተመላሽ ያገኛሉ ፤

• ለሀይማኖታዊ ጉዳይ ወደ ውጭ ሀገራት የሚጓዙ ደንበኞች ከአየር ትኬት ክፍያቸው እስከ 3 በመቶ የሚደርስ ተመላሽ ያገኛሉ፤
• ሌሎች ተጨማሪ ጥቅሞችንም ያስገኛል፡፡

ሂሳቡን በአቅራቢያዎ በሚገኝ ቅርንጫፍ ይክፈቱ፤ ለበለጠ መረጃ ወደ 951 ይደውሉ!

#CBE
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
መምጣቱ ላይቀር የሚያስጠብቀን የእረፍት ቀን ደርሷል! ዘና ፈታ እንበል! #መክሰስTime ደርሷል- ከ #ሰንቺፕስ 😋 ጋር #ሰኒሞመንትስ ☀️
Looking forward to snacking on the weekend with SUNChips. #SUNChips 😋 #SunnyMoments. ☀️
Facebook: https://www.facebook.com/sunchipsethiopia
Instagram: https://instagram.com/sunchipsethiopia 
#Oromia

በኦሮሚያ ክልል እስከ መስከረም መጨረሻ ድረስ 1.3 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች ተፈናቅለዋል።

CDCB (Center For Development &Capacity Building ) ባወጣው ሪፖርት የቡሳ ጎኖፋን መረጃ ዋቢ አድርጎ በኦሮሚያ ክልል እስከ መስከረም ባለው ጊዜ 1.3 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች መፈናቀላቸውንና ከተመዘገቡት ተፈናቃዮች ውስጥ 859,000 (66%) የሚሆኑት ከምስራቅ ወለጋ እና ምዕራብ ወለጋ ብቻ መሆናቸውን ይጠቅሳል።

በመግለጫው የተጠቀሱት ቁጥሮች ምን ያሳያሉ ?

- የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር 1,292,323 መሆኑ የተገለጸ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 29 በመቶው ብቻ (374,448) ወደ መጠለያዎች መድረሳቸውን ያመለክታል። 71 በመቶ (916,606) የሚሆኑት በአካባቢው እና ራቅ ብለው በሚገኙ ማኅበረሰቦች ውስጥ ተበታትነው ይገኛሉ።

- 739 ትምህርት ቤቶች ከአገልግሎት ውጪ ሆነዋል።

- ከ210,000 በላይ ህጻናት ከትምህርት ውጪ ሆነዋል።

- 1,117 መምህራንና የትምህርት ባለሙያዎች ወደ ሥራቸው አልተመለሱም።

- 208 ጤና ተቋማት ሙሉ በሙሉ ወድመዋል፤  788 በከፊል ወድመዋል። ( ከእነዚህ ውስጥ 13ቱ ሆስፒታሎች ሲሆኑ የተቀሩት ጤና ጣቢያዎች ናቸው)

በዚህ አጭር መግለጫ በምዕራብ ኦሮሚያ እና መካከለኛው አከባቢ በፌዴራል መንግስት እና በሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት በሽብርተኝነት የተፈረጀው ራሱን የኦሮሞ ሕዝብ ነጻ አውጭ ብሎ በሚጠራውና መንግሥት " ኦነግ ሸኔ " የሚለው ታጣቂ ቡድን መካከል የተፈጠረው ግጭት፣ እንዲሁም በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ድንበር ላይ በአማራ ክልል በሚንቀሳቀሰው " ፋኖ " በመባል የሚታወቀው ታጣቂ ቡድን ጋር በሚፈጠሩ ግጭቶች ለችግሮቹ መንስዔ መሆናቸውን ይጠቅሳል።

በእነዚህ ግጭቶች በተለይ ሴቶች እና ህጻናት ለአደጋ የተጋለጡ ናቸው ያለው ይህ አጭር መግለጫ እናቶቻቸውን እና አባቶቻቸውን በድንገት የሚያጡ ህፃናት ቁጥር እየጨመረ ነው፤ ባል የሞቱባቸው ሴቶች ለዝርፊያ እና ለ አስገድዶ መድፈር (በፆታ ላይ የተመሰረተ ጥቃት) እና አካላዊ ጥቃት እየተጋለጡ መሆናቸውን ያነሳል።

"በኦሮሚያ ክልል ያለው ግጭት ውስብስብ እና አሳሳቢ ሁኔታን ፈጥሯል። ይሄን ግጭት ለማስቆም ሁሉን አቀፍ ውይይት እና ሰላም ማስፈን ያስፈልጋል። በግጭቱ ወቅት ለተፈናቀሉ እና ችግር ውስጥ ላሉ ዜጎች አስቸኳይ የተቀናጀ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል።" ሲል በCDCB የቀረበው የፓሊሲ ብሪፍ ጠይቋል።

በአፋን ኦሮሞ ቋንቋ የተዘጋጀውን ሙሉ መግለጫ @tikvahethafaanoromoo ላይ ያገኙታል።

@tikvahethiopia
የሀገር_ውስጥ_ተፈናቃዮች_የሰብአዊ_መብቶች_ሁኔታ_ዓመታዊ_ሪፖርት.pdf
3.8 MB
#ኢሰመኮ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) 2ኛውን በአገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሰብዓዊ መብቶች አያያዝ ላይ የሚያተኩር ዓመታዊ ሪፖርት በቀናት በፊት ይፋ አድርጓል፡፡

በሪፖርቱ ምን አለ ?

- ዜጎችን ከመደበኛ የመኖሪያ ቦታቸው ያፈናቀሉ፣ የሰው ሕይወት ያጠፉ፣ ሀብት ያወደሙ፣ አካላዊ ጉዳት ያደረሱ ቡድኖችና ግለሰቦች በሕግ ተጠያቂ ለማድረግ በቂ ዕርምጃዎች ባለመወሰዳቸው የሕግ በላይነት፣ ተጠያቂነትንና የተፈናቃዮችን ፍትሕ የማግኘት መብት የሚነፍግ ነው።

- በዘፈቀደ ለሚደረጉ የማፈናቀል ድርጊቶች አስተማሪ ዕርምጃዎች እየተወሰዱ አይደሉም።

- ዘላቂ የመፍትሔ አማራጮች አተገባበርም የመፈናቀል ምክንያት የሆኑትን የደኅንነት ሥጋቶች ባስወገደ፣ ተፈናቃዮችንና ተቀባይ ማኅበረሰብን ባሳተፈ፣ የተፈናቃዮችን ፍላጎት ባገናዘበ፣ እንዲሁም ተፈናቃዮችን በዘላቂነት በሚያቋቁም ሁኔታ ባለመሆኑ፣ ለዳግም መፈናቀል የሚያጋልጥ ነው።

- አብዛኛዎቹ ተፈናቃዮች ዘላቂ መፍትሔ ሳያገኙ በመጠለያ ጣቢያዎችና ከተቀባይ ማኅበረሰብ ጋር ተቀላቅለው መኖር ከጀመሩ በትንሹ ሦስት ዓመታት አልፏቸዋል።

- ተገቢው ጥበቃ የማይደረግላቸው፣ እንዲሁም የሲቪልነት ባህሪን ያልጠበቁ በወታደራዊ ካምፖች አካባቢ የሚኖሩ ተፈናቃዮች የሚገኙባቸው መጠለያ ጣቢያዎች መኖራቸው፣ የተፈናቃዮች የደኅነነት ሁኔታ አደጋ ላይ መሆኑን እንደሚያሳይ፣ በተጨማሪም መንግሥት በካምፓላ ስምምነት መሠረት የተጣለበትን ግዴታ በአግባቡ አለመወጣቱን የሚጠቁም ነው።

- መንግሥት ፈርሞ የተቀበለውን የካምፓላ ስምምነትን ለማስፈጸም የተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ፀድቆ ሥራ ላይ አለመዋሉና የተፈናቃዮችን ጉዳይ በባለቤትነት የሚያስተዳድር ተቋማዊ አደረጃጀት የለም።

- መፈናቀልን ለመከላከል ለተፈናቃዮች የሚደረጉ የጥበቃና ድጋፍ ሥራዎች፣ እንዲሁም የዘላቂ መፍትሔ ማፈላለግ ሒደቶች ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶች አሁንም አሳሳቢነታቸው ቀጥሏል።

- የተፈናቃዮች ምዝገባና ሰነድ የማግኘት ሥርዓቱ ላይ ያለው ክፍተት ለተፈናቃዮች የሚደረገው ድጋፍ በአግባቡ እንዳይከናወን አሉታዊ ተፅዕኖ አሳድሯል። በተጨማሪ ተፈናቃዮች ሌሎች የመንቀሳቀስና የማኅበራዊ አገልግሎት የማግኘት መብቶቻቸውን ለመጠቀም እንዳይችሉ አድርጓል።

- በኢትዮጵያ 80 በመቶ የሚሆነው መፈናቀል ኃይል በተቀላቀለባቸው ግጭቶች ምክንያት የሚከሰት በመሆኑ መፈናቀልን ለመከላከልና በዘላቂነት መፍትሔ ለመስጠት፣ በዋናነት ግጭቶችን ወቅታዊ በሆነ ሁኔታ በሰላማዊ መንገድ መፍታት ያስፈልጋል፡፡ #ሪፖርተር

(ከኢሰመኮ የተላከ ሙሉ ሪፖርት ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
" ያፈራሀው ሃብት ውጤት የሚኖረው ህዝብ ተጠቃሚ ማድረግ በሚችል ቁምነገር ስታውለው ነው " - ባለሃብቱ ዘርኡ ገ/ሊባኖስ

ባለሃብቱ በሰባቱ የትግራይ ዞኖች ሰባት ትምህርት ቤቶች ለመገንባት የሚያስችል የሰምምነት ሰነድ ተፈራረሙ።

ትምህርት ቤቶቹ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ የመነሻ ካፒታል ናቸው የሚገነቡት። 

ባለሃብቱ ኣቶ ዘርኡ ገ/ሊባኖስ ጥቅምት 11/2016 ዓ.ም በመቐለ በተከናወነው የመሰረት ድንጋይ ማስቀመጥና የስምምነት ፊርማ ስነ-ሰርአት እንዳሉት ፤ " ያፈራሀው ሃብት ውጤት የሚኖረው ህዝብ ተጠቃሚ ማድረግ በሚችል ቁምነገር ስታውለው ነው " ብለዋል። 

ትግራይ በደም አፋሳሹ ጦርነት ምክንያት ያጋጠማት ውድመት ከፍተኛ መሆኑ የጠቆሙት ባለሃብቱ ፤ ሁሉም በየአቅሙ በመልሶ ግንባታ በመሳተፍ ለትውልድ የሚተርፍ ቅዱስ ነገር መፈፀም እንዳለበት አሳስበዋል።  

በማብሰሪያ ስነ-ሰርዓቱ የተገኙት የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕረዚደንት ጌታቸው ረዳ በበኩላቸው ፤ " በጦርነት የወደመቸው ትግራይ መልሶ ለመገንባትና የተሰው ታጋዮች አደራ ለመፈፀም በሚደረገው ጥረት የሁሉም ትግራዋይ ተሳትፎ እጅግ ወሳኝ ነው " ብለዋል። 

በስነ-ሰርዓቱ ማብሰሪያ እንደተገለፀው የሚገነቡት ሰባት ትምህርት ቤቶች ለያንዳንዳቸው ብር 50 ሚሊዮን ፤ በአጠቃላይ 350 ሚሊዮን ብር መመደቡንና በጥራትና በጊዜ ሰሌዳ ለመፈፀም ይሰራል ተብሏል። 

ባለሃብቱ አቶ ዘርኡ ገ/ሊባኖስ የተቸገሩትን በመርዳት ባሳዩት መልካምነት ከናይጀሪያው ዎልደስ የኒቨርስቲ መስከረም 9/2016 ዓ.ም የክብር ዶክትሬት አግኝተዋል።

መረጃውን የመቐለ የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ነው ያደረሰን።

@tikvahethiopia