TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#እንድታውቁት

የነዳጅ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል።

ከጥቅምት 6 ቀን 2016 ዓ.ም እኩለ ሌሊት 6:00 ሰዓት ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በመስከረም ወር ሲሸጥበት በነበረው እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።

በመስከረም ወር የነበረው የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ስንት ነው ?

- ቤንዚን በሊትር 77 ብር ከ65 ሳንቲም
- ነጭ ናፍጣ በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም
- ኬሮሲን በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም
- ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 62 ብር ከ36 ሳንቲም
- ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 61 ብር ከ16 ሳንቲም

ምንጭ፦ የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር

@tikvahethiopia
#የብድር_ገደብ

ብሔራዊ ባንክ የጣለው የብድር ገደብ በባንኮች እና ተበዳሪዎች ላይ ተግዳሮት መፍጠሩ ተነግሯል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ / #NBE ከጥቂት ወራት በፊት ያወጣው የገንዘብ ፖሊሲ ወደ ትግበራ ገብቷል፡፡

የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር ዋነኛ ዓላማ ያደረገው ይህ ፖሊሲ ፣ የባንኮች የብድር ምጣኔ ካለፈው ዓመት ከ14 በመቶ በላይ እንዳይበልጥ ገደብ የጣለ ነው፡፡

በተለይ ባንኮች የሚሰጡት ብድር በገንዘብ ፖሊሲው ከተጣለባቸው ገደብ ጋር ለማጣጣም በማሰብ ቀደም ብለው የፈቀዷቸውን ብድሮች ጭምር ከመልቀቅ እንዲቆጠቡ ወይም መሰል አሠራርን እንዲከተሉ እያደረጋቸው ስለመሆኑ ለማወቅ ተችሏል፡፡ 

ከመመርያው መውጣት ቀደም ብለው የተፈቀዱ ብድሮች ሊለቀቅላቸው እንዳልቻለ የተለያዩ ባለሀብቶችና የንግድ አንቀሳቃሾች ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል ገልጸዋል።

በዚህም የተፈቀደላቸውን ብድር ታሳቢ በማድረግ የገቧቸው የቢዝነስ ስምምነቶች እየተፋረሱባቸው መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ቤትና ተሽከርካሪ ግዥ ውሎች ሳይቀሩ በእንጥልጥል እንዲቆዩ ማድረጉንም ከተበዳሪዎች መገንዘብ ተችሏል፡፡ 

ብድር እንዲለቀቅላቸው #ማረጋገጫ አግኝተው የነበሩት ተበዳሪዎች አሁን ላይ ብድሩን ማግኘት ለምን እንዳልቻሉ ለሚያቀርቡት ጥያቄ የሚያገኙት ምላሽ " አዲሱ የገንዘብ ፖሊሲ የጣለው የብድር ዕቀባ " መሆኑን ያስረዳሉ።

አንዳንዶቹም የተፈቀደላቸውን ብድር በትዕግሥት እንዲጠብቁ እንደተነገራቸው ያመለክታሉ፡፡

ቤት ለመግዛት ተዋውለው ከሚገለገሉበት ባንክ የፈቀደላቸውን ብድር እየተጠባበቁ የነበሩ አንድ ተበዳሪ ብድሩ እንደሚያገኙት በተገለጸላቸው ወቅት ሊለቀቅላቸው ባለመቻሉ የቤት ሽያጭ ውላቸው ሊፈርስባቸው እንደሆነ ገልጸዋል። እንዲህ ያለው ችግር በአብዛኛው በግል ባንኮች አካባቢ የሚስተዋል ነው፡፡

ያንብቡ 👇
https://telegra.ph/Reporter-Newspaper-10-17

#ሪፖርተር

@tikvahethiopia
የእርስዎ ስኬት የኛም ስኬት ነው!
ህልምዎን እውን ለማድረግ በጋራ እንሰራለን፡፡

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ
ለጋራ ስኬታችን

የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ
https://publielectoral.lat/Globalbankethiopia123

#Globalbankethiopia #sharedsuccess
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ፍልስጤም #እስራኤል

በጋዛ በሚገኝ ሆስፒታል ላይ በተፈፀመ ጥቃት በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተገደሉ።

ሃማስ ጥቃቱን እስራኤል ነው የፈፀመችው ብሏል።

የእስራኤል መከላከያ ደግሞ " ኢስላሚክ ጂሃድ " የተባለው ቡድን እስራኤል ላይ ያስወነጨፈው ሮኬት ዒላማው ሳይሳካ ቀርቶ የተፈጠረ ነው ብሏል።

ትላንት ጋዛ ውስጥ በሚገኘው "አልአህሊ ባፕቲስት ሆስፒታል " ላይ በደረሰ የአየር ጥቃት በትንሹ 500 ሰዎች መገደላቸውን በጋዛ  የሚገኘው ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል።

ሃማስ ጥቃቱን እስራኤል ነው የፈፀመችው ብሏል። ጥቃቱን " የጦር ወንጀል ነው" ሲል ገልጾ " ሆስፒታሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ የታመሙ እና የቆሰሉ ሰዎች ነበሩበት ብሏል።

የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት ፤ በጋዛ የሚገኘው ሆስፒታል የተመታው ባያልተሳካ የ " እስላሚክ ጂሃድ " ቡድን ሮኬት ነው ብሏል።

ያልተሳካ ሮኬት ያስወነጨፈው ይኸው ቡድን ለሆስፒታሉ መመታት ተጠያቂ ነው ሲል ገልጿል።

" እኛ ሆስፒታሉ ላይ ጥቃት አልፈፀምንም " ብሏል።

የ " ፍልስጤም እስላሚክ ጂሃድ " ድርጅት የእስራኤል ክስ ሀሰተኛ እና ምንም መሰረት የሌለው የተለመደ ቅጥፈት ነው ብሏል። እስራኤል ከተለመደው ጭፍጨፋ ተጠያቂነት ለማምለጥ በፍልስጤማውያን እና ' ኢስላሚክ ጂሃድ ' ላይ ጣቷን ለመጠቆም የፈጠረችው ሀሰተኛ ፈጠራ ነው ሲል ገልጿል።

" ፍልስጤም እስላሚክ ጂሃድ " እኤአ 1981 የተመሰረተ ሲሆን በጋዛ እና ዌስት ባንክ ውስጥ ይንቀሳቀሳል።

በሌላ በኩል ፤ የፍልስጤም ፕሬዜዳንት ማሃሙድ አባስ በሆስፒታሉ ላይ በተፈፀመው ጥቃት እና በጠፋው የሰው ህይወት ምክንያት የ3 ቀን ሀዘን አውጀዋል።

በሆስፒታል ላይ የተፈፀመውን ጥቃት ሀገራት እና ተቋማት እያወገዙ ይገኛሉ። በተለያዩ ከተሞችም እስራኤልን የሚያወግዙ ሰልፎች እየተደረጉ ይገኛሉ።

ዓለም ለጋዛ ሆስፒታል ለደረሰው ጥቃት ምን ምላሽ ሰጠ ?

እስራኤል የአየር ጥቃቱን ፈፅማለች ብለው የከሰሱና ያወገዙ ፤ በጉዳቱ ሀዘናቸውን የገለፁ ፦

🇪🇬 የግብፅ ፕሬዝዳንት
🇯🇴 የዮርዳኖስ ንጉስ
🇸🇾 የሶሪያ ፕሬዝዳንት
🇨🇺 የኩባ ፕሬዝዳንት
🇮🇶 የኢራቅ መንግስት
🇸🇦 የሳዑዲ አረቢያ መንግስት
🇹🇷የቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
🇻🇪 የቬንዙዌላ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
🌍 የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሃላፊ
🇮🇷 የኢራን ፕሬዝዳንት (እስራኤል ብቻ ሳትሆን አሜሪካም ጭምር ከእስራኤል ጋር ሀላፊነት ትወስዳለች ብለዋል)

ጥቃቱን ያወገዙ ነገር ግን ማንንም ያልወቀሱ ፤ ይልቁንም ምርመራ እንዲደረግ የጠየቁ ፦

🇪🇺 የአውሮጳ ዲፕሎማሲ ኃላፊ
🇫🇷 የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት
🇳🇱 የኔዘርላንድስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
🇪🇸 የስፔን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
🇬🇧 የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት
🇯🇵 የጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
🇺🇸 አሜሪካ ማንም ሳትከስ ነገር ግን ስለ ተፈጠረው ሁኔታ ተጨማሪ መረጃዎችን ሰበስባለሁ ብላለች።

" ማስረጃ አቅርቢ " - ሩስያ

🇷🇺 የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እስራኤል በጥቃቱ ላይ የለሁበትም ካለች የሳተላይ ምስሎችን በማስረጃነት ታቅርብ ብሏል።

እኤአ ጥቅምት 7 ጦርነት ከተቀሰቀሰ በኋላ እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ላይ ባደረሰችው ጥቃት የተገደሉ ሰዎች ከ3,200 በልጠዋል።

በእስራኤል ውስጥ በሃማስ ጥቃት የተገደሉ ከ1,400 በላይ ሰዎች ሆነዋል።

More 👉 @Birlikethiopia
#GudafTsegay #TigistAssefa

የዓለም አትሌቲክስ የአመቱ ምርጥ ሴት አትሌት ዘርፍ የመጨረሻ እጩዎች ይፋ ተደርገው ድምፅ እየተሰጠ ይገኛል።

ሁለት #ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ከምርጥ አስራ አንድ እጩዎች ውስጥ ይገኙበታል።

እጩዎቹም ፤ በቅርቡ የአለም የማራቶን ሪከርድን መስበር የቻለችው ኢትዮጵያዊት አትሌት ትዕግስት አሰፋ እንዲሁም የ5000ሜ የዓለም ክብረወሰን የሰበረችው ጉዳፍ ፀጋይ ናቸው።

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ በዚህ አመት የ5000 ሜትር የአለም ክብረወሰን ከመስበሯም በተጨማሪ የ10,000ሜ የዓለም ሻምፒዮን እንደነበረች ይታወሳል።

ምርጫው እንዴት ይካሄዳል ?

የዓለም አትሌቲክስ ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት የአሸናፊዎች ምርጫ ለዓለም አትሌቲክስ ኮሚቴ እና ለዓለም አትሌቲክስ ቤተሰቦች ድምፅ በኢሜል መስጠት እንደሚቻል ተገልጿል።

ደጋፊዎች እንዴት መምረጥ ይችላሉ ?

ሁሉም የአትሌቲክስ ደጋፊዎች የሚመርጧቸውን አትሌቶች ፎቶ በአለም አትሌቲክስ ማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ በመፈለግ በፌስቡክ ፣ ዩቲዩብ እና ኢንስታግራም ላይክ በማድረግ እንዲሁም በ " X " ሪፖስት በማድረግ መምረጥ ይችላሉ።

ጉዳፍ ፀጋይን #ላይክ / #ሪትዊት ለማድረግ ፦

ፌስቡክ ፦ https://www.facebook.com/100064391421386/posts/pfbid0hS68YYaTusAL2g6TrYMbMuuW1pDFv2KBQbfcD4piPiJc3XU1iDyb45k6CKCf3bgYl/?app=fbl

X / የቀድሞ ትዊተር ላይ ሪትዊት ለማድረግ ፦ https://twitter.com/WorldAthletics/status/1712082175250563508?t=rpGi0sYnnozLQvDtN4RTKQ&s=19

ኢንስታግራም ፦ https://www.instagram.com/p/CyQkhc9Mry7/?igshid=NjIwNzIyMDk2Mg==

ትዕግስት አሰፋን #ላይክ / #ሪትዊት ለማድረግ ፦

ፌስቡክ ፦ https://www.facebook.com/100064391421386/posts/pfbid01BPvP9Vb4sF7tRxmX2Lb5BqWDgXjFB17Agijp9vWQWsJufvbrkXL3yH7PZbidcaTl/?app=fbl

X / የቀድሞ ትዊተር ሪትዊት ለማድረግ ፦ https://twitter.com/WorldAthletics/status/1712082042391802157?t=xlF0PNgzEhsBxSb56pANlw&s=19

ኢንስታግራም ፦ https://www.instagram.com/p/CyQjzyRM8Iv/?igshid=NjIwNzIyMDk2Mg==

(ሼር ያድርጉ)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#USA #Israel

የአሜሪካው ፕሬዜዳንት #ጆ_ባይደን እስራኤል ገብተዋል።

ባይደን በእስራኤል ቆያታቸው ጦርነቱ ከዚህም በላይ ከፍቶ እንዳይስፋፋ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ያደርጋሉ ተብሏል።

የአሜሪካ ብሄራዊ ደህንነት ቃል አቀባይ ፕሬዝዳንት ባይደን የቀጠለውን ጦርነት #ዓላማን በተመለከተ ለኔታንያሁ ከበድ ያሉ ጥያቄዎችን እንደሚጠይቋቸው ገልጸዋል።

ባይደን በቅድሚያ ይሄዳሉ ተብሎ የነበረው ወደ ዮርዳኖስ ነበር።

በዛም ከአረብ ሀገራት መሪዎች ጋር ይመክራሉ ተብሎ ነበር። ነገር ግን ከአሜሪካ ከተነሱ በኃላ የአረብ ሀገራት መሪዎች ከባይደን ጋር እንደማይገናኙ እና የነበረውም ስብሰባ መሰረዙ ተሰምቷል።

አሜሪካም ፕሬዜዳንቷ ወደ ዮርዳኖስ እንደማይሄዱና ይህም " የጋራ ውሳኔ " መሆኑን ገልጻለች።

" በእናተ አልተፈፀመም " - ባይደን

ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን እስራኤል በሆስፒታሉ ላይ ጥቃት አልፈፀመችም ብለዋል።

እስራኤል የሚገኙት ጆ ባይደን በጋዛ በሚገኘው " አል አህሊ ባፕቲስት ሆስፒታል " ላይ ፍንዳታ የተፈፀመው በእስራኤል ሳይሆን " በሌላኛው ቡድን " ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ባይደን ለእስራኤሉ ጠ/ሚ ኔታንያሁ ፤ " ትናንትና በጋዛ ሆስፒታል በደረሰው ፍንዳታ በጣም አዝኛለሁ " ያሉ ሲሆን " ባየሁት መሰረት፣ የተደረገው በሌላው ቡድን ይመስላል ፤ እንጂ በአንተ (እስራኤል) አይደለም " ሲሉ ተናግረዋል።

እስራኤል ፤ በሆስፒታሉ ላይ ለደረሰው ጥቃት ያልተሳካ " የኢስላሚክ ጂሃድ " ቡድን ሮኬት ነው ያለች ሲሆን " ሃማስ " እንዲሁም " የፍልስጤም ኢስላሚክ ጂሃድ " ድርጅት ጥቃቱ የተፈፀመው በእስራኤል ነው ብለዋል።

" የፍልስጤም ኢስላሚክ ጂሃድ " የእስራኤል ክስ ሀሰተኛ እና ምንም መሰረት የሌለው እንዲሁም ከጭፍጨፋው ተጠያቂነት ለማምለጥ ጣቷን በእስላሚክ ጂሃድ እና ፍልስጤማውያን ላይ የጠቆመችበት የተለመደ የሀሰት እና ቅጥፈት ፈጠራዋ ነው ብሏ

More + @BirlikEthiopia
አቶ ታምሩ ገምበታን ጨምሮ ለጊዜው ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች መታሰራቸው ተሰምቷል።

የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ታምሩ ገምበታን ጨምሮ ቁጥራቸው ለጊዜው ያልታወቁ ሰዎች በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው መታሰራቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ሰሞኑን መሆኑንና አቶ ታምሩ ገምበታ ግን ጥቅምት 5 ቀን 2016 ዓ.ም. መሆኑ ተገልጿል።

የምክትል ዳይሬክተሩ ቤት በፍርድ ቤት የብርበራ ፈቃድ መበርበሩንና ዛሬ ጥቅምት 7 ቀን 2015 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ሊቀርቡ እንደሚችሉ ተጠቁሟል፡፡

የመንግሥት አስተዳደር ለውጥ ከተደረገ ጀምሮ የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ አገልግሎት ተቋም ውስጥ የተለያዩ ለውጦች (ሪፎርም) የተደረገ ቢሆንም፣ አንዳንድ የተቋሙ ሠራተኞች በድለላ ሥራ የተሰማሩ አካላት ጋር በመመሳጠር የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል ተብለው በቁጥጥር ሥር ውለው በምርመራ ላይ እንዳሉም ተመላክቷል።

አገልግሎቱን በዋና ዳይሬክተርነት ይመሩ የነበሩት አቶ ብሩህተስፋ ሙሉጌታ፣ ምክትል ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ፍራኦል ጣፋና አቶ ታምሩ ገምበታን ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ከ3 ወራት በፊት ሐምሌ መጀመሪያ ሳምንት አካባቢ ከኃላፊነት ማንሳታቸው ይታወሳል፡፡

ተቋሙ ከፓስፖርትና መሰል አገልግሎቶች ጋር በተያያዘ ቅሬታ ሲቀርብበት መቆየቱ ይታወቃል።

በተጨማሪ ከዜጎች ከፍተኛ ገንዘብ በመቀበል በሕወጥ መንገድ ወደ ውጭ አገር ሲልኩ ነበር የተባሉ 16 የተቋሙ ሠራተኞች፣ እንዲሁም 5 በአሠሪና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ስም ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ሰዎችም ከዚህ ቀደም በቁጥጥር ሥር ውለዋል።

በተያዘው ሳምንት በቁጥጥር ሥር መዋላቸው የተሰማው ምክትል ዳይሬክተሩን ጨምሮ ሌሎች ሰዎችም ከሙስና ጋር በተያያዘ መጠርጠራቸው ተገልጿል፡፡

ምንጭ፦ #ሪፖርተር_ጋዜጣ

@tikvahethiopia
የሳፋሪኮም ስልካችን ላይ ካርድ በመሙላት ቀኑን ሙሉ  ወይም ሳምንቱን ሙሉ በነፃ እንደዋወል።

ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/SafaricomET
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/safaricomet/
ትዊተር- https://twitter.com/SafaricomET
ሊንክዲን- https://www.linkedin.com/company/safaricom-ethiopia/
ቴሌግራም- https://publielectoral.lat/Safaricom_Ethiopia_PLC

#SafaricomEthiopia #FurtherAheadTogether
#GAT_Result

ብሔራዊ የድህረ ምረቃ የመግቢያ ፈተና (GAT) ውጤት ይፋ ሆኗል።

ፈተናውን የወሰዳችሁ አመልካቾች ተከታዩ ሊንክ ላይ በመግባትና የማመልከቻ ቁጥራችሁን በማስገባት ውጤታችሁን ማየት ትችላላችሁ።

ውጤት ለማየት፦

https://portal.aau.edu.et/Web/ApplyForAdmission/TestingStatus

የፈተናው የማለፊያ ነጥብ በቀጣይ ይፋ እንደሚደረግ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አሳውቋል።

@tikvahuniversity
" የትምህርት ሚኒስቴር በዋናነት ለተገኘው ውጤት የኔ ውድቀት ነው ብሎ ኃላፊነቱን ሊወስድ ይገባል " - ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ

የትምህርት ሚኒስቴር ለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዝቅተኛ ውጤት መመዝገብ ምክንያት የሆኑ ችግሮችን በጥናት ለይቶ እንዲያቀርብ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰዉ ኃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጠየቀ።

በይህ የተጠየቀው በምክር ቤቱ የሰዉ ኃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የትምህርት ሚኒስቴርን የ2016 እቅድና የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ዛሬ ሲገመግም ነው።

በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ " ቀደም ሲል ሲሰጡ የነበሩ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤቶች የተማሪዎችን ትክክለኛ ችሎታ ያሳዩ አልነበሩም " ብለዋል።

የፈተና አሰጣጡን በመቀየር የተመዘገበው የተማሪዎች ውጤት በዘርፉ ከዚህ ቀደም የነበሩ ችግሮች ማሳያ መሆናቸውን ጠቁመው ለዚህም ከወላጆች ጀምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተጠያቂ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የትምህርት ጥራት ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የተለያዩ ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑን ጠቅሰው እየተካሄዱ ያሉ የትምህርት ቤቶች ማሻሻያ መርኃ ግብሮችና የመምህራን አቅም ግንባታ ሥራዎችን ለአብነት አንስተዋል።

በምክር ቤቱ የሰዉ ኃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶክተር ነገሪ ሌንጮ ፤ " ሚኒስቴሩ ለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዝቅተኛ ውጤት መምጣት ሁሉንም ተጠያቂ ማድረግ አይቻልም " ብለዋል።

በመሆኑም የትምህርት ሚኒስቴር የማስተማርና ፈተና የማስፈተን ተልዕኮ ተሰጥቶት እንደሚሰራ ተቋም በዋናነት ለተገኘው ውጤት ኃላፊነቱን ሊወስድ ይገባዋል ነው ያሉት።

ትምህርት ሚኒስቴርን ጨምሮ ተጠሪ ተቋማትና የትምህርቱ ዘርፍ ተዋንያን ለውጤቱ የነበራቸው ድርሻ ተለይቶ መቅረብ እንዳለበትም አሳስበዋል።

ለተማሪዎች ዝቅተኛ ውጤት ማጣት ምክንያት የሆኑ ሌሎች ችግሮችም በጥናት ተለይተው ሊቀርቡ እንደሚገባም ዶክተር ነገሪ ተናግረዋል። #ኢዜአ

@tikvahethiopia