TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ደብዛው የጠፋው ጋዜጠኛ⬇️

የቱርክ ፕሬዚዳንት #ጣይብ_ኤርዶሃንና የሳዑዲው ንጉስ #ሳልማን_ቢን አብዱልአዚዝ ደብዛው በጠፋው ጋዜጠኛ ጉዳይ ላይ በስልክ #ተወያዩ

ጋዜጠኛ #ጀማል_ካሾጊ ከሁለት ሳምንት በፊት ቱርክ በሚገኘው የሳዑዲ ዓረቢያ ኮንስላ ጽህፈት ቤት ጉዳይ #ሊያስፈፅም እንደገባ ደብዛው ከጠፋ 13 ቀናት ተቆጥረዋል።

የቱርክ ፕሬዚዳንት ጣይብ ኤርዶሃንና የሳዑዲው ንጉስ ሳልማን ትናንት ሌሊት በስልክ ባደረጉት ውይይት የጋዜጠኛው መጥፋት ጉዳይ አጀንዳቸው ነበር ተብሏል።

ኤርዶሃን በጀማል ካሾጊ ጉዳይ ላይ ጥምር ቡድን ተቋቁሞ ምርመራ እንዲካሄድ በአፅንኦት መናገራቸው ተሰምቷል።

ካሾጊ በሳዑዲ ቆንስላ ጽህፈት ቤት በነበረበት ወቅት 10 ሳዑዲዎች እና የመንግስት ባለስልጣናት በሁለት አውሮፕላኖች ወደ ኢስታንቡል በማምራት ጽህፈት ቤቱን በተመሳሳይ ቀን መጎብኘታቸውን የቱርክ ፖሊስ መረጃዎች ያሳያሉ።

የዋሽንግተን ፖስት ጋዜጣ አምደኛ የሆነው የሳዑዲ ዜግነት ያለው ጋዜጠኛ ጀማል ካሾጊ የት እንደገባ አለመታወቁን ተከትሎ ቱርክ፣ አሜሪካ እና ብሪታኒያ ከሳዑዲ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

ቱርክ ጋዜጠኛው #መገደሉን የሚያሳዩ መረጃዎችን አግኝቻለሁ እያለች ነው።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እንዳሉት ጋዜጠኛው በቆንስላ ጽህፈት ቤቱ ውስጥ መገደሉ ከተረጋገጠ ሳዑዲ ከባድ #ቅጣት ይጠብቃታል ብለዋል።

ይህን ተከትሎም ሳዑዲ በሰጠችው ምላሽ ማንኛውም ሀገር በጀማል ካሾጊ ጉዳይ ሀሰተኛ ውንጀላ የሚያቀርብ፣ ኢኮኖሚያዊም ሆነ ፖለቲካዊ ጫና ለመፍጠር የሚያስብ ሀገር ካለ የአፀፋ ምላሽ እንደምትወስድ አስጠንቅቃለች።

ምንጭ፦ አናዶሉና ሮይተርስ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የጀማል አስክሬን እንዲሟሟ ተደርጓል‼️

ጋዜጠኛ #ጀማል_ካሾጊ ከተገደለ በኋላ አስከሬኑ ተቆራርጦ #እንዲሟሟ ተደርጓል አሉ የፕሬዚዳንት #ኤርዶሃን ኣማካሪ።

የአሁኑ የአማካሪው መግለጫ “የጋዜጠኛው አስከሬን በአሲድ እንዲጠፋ ተደርጓል መባሉን ለማጣራት ምርመራ እየተካሄደ ነው” በማለት
አንድ ከፍተኛ የቱርክ ባለስልጣን ለዋሽንግተን ፖስት ጋዜጣ የሰጡትን መረጃ እውነትነት #ያረጋግጣል ተብሏል።

አማካሪው ያሲን አክታይ ቱርክ ውስጥ ለሚታተመው ሁርየት የተባለ ጋዜጣ እንደተናገሩት የካሾጊ አስከሬን ተቆራርጦ ብቻ ሳይሆን ሟሙቶ እንዲወገድ መደረጉን ነው ማወቅ የቻልነው ብለዋል።

እጃችን ላይ እንደደረሰው መረጃ ከሆነ ገዳዮቹ አስከሬኑን የቆራረጡት በቀላሉ ለማሟሟት እንዲመቻቸው ነው ብለዋል አማካሪው።

የቱርክ ዋና ዐቃቢ ህግ ባለፈው ረቡዕ ለመጀመሪያ ጊዜ በሰጡት መግለጫ ካሾጊ ኢስታንቡል ወደሚገኘው የሳዑዲ ቆንስላ እንደገባ በተደራጀ ሁኔታ #ግድያ ተፈጽሞበት አስከሬኑም ተቆራርጦ እንዲወገድ መደረጉን አረጋግጠዋል።

“አንድም የሰውነቱ አካል እንዳይገኝ አልመው ያደረጉት ነገር ነው። ንጹህ ሰው መግደል አንድ ወንጀል ሆኖ ሳለ አስከሬኑ እንዲጠፋ የተደረገበት መንገድ ደግሞ ሌላ አስከፊ ወንጀል ነው ብለዋል ያሲን አክታይ።

ምንጭ፦ ARTS TV WORLD
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሼክ አላሙዲን ነገር⁉️

"ቢቢሲ ዛሬ በለቀቀው ዘጋቢ ፊልም እነ ሼክ አላሙዲንን ከሳዑዲ ልዑላውያን ጋር ደምሮ ያሳረዉ የሳዑዲ መንግስት በታሳሪዎቹ ላይ የከፋ #ድብደባ እና #ማሰቃየት እንዲሁም #ግድያ እየፈፀመ ነዉ ሲል ዘጋቢ ፊልም ሰርቷል። ከሟቾች ዉስጥ ጄኔራል አሊ አልካታኒ አንዱ ናቸዉ። ሞሐመድ ቢን ሰልማን የሚባለዉ እና ፖለቲካዊ አመለካከቱ ሊበራል ነዉ ተብሎ ሲወደስ የነበረዉ በቅጽል ስሙ ኤም ቢ ኤስ የተባለዉ የሳዑዲ አልጋወራሽ በእርሱ ትዕዛዝ የታሰሩ ባለሀብቶችና ንጉሣውያን ቤተሰቦች በድብደባ ምክንያት የደረሰባቸውን ጉዳት በሌላ ሆስፒታል እንዳይታከሙ በሪትዝ ሆቴል ተንቀሳቃሽ ሆስፒታል ከፍቷል። ይህ ዘገባ የተሰራዉ በቅርቡ ቱርክ በሚገኘዉ በሳዑዲ አረቢያ ቆንስላ
በጋዜጠኛ #ጀማል_ካሾጊ ላይ የተፈፀመዉን ግድያ ጋር ተንተርሶ ነዉ። አላሙዲን ምን ሁኔታ ላይ ይገኛሉ? የኢትዮጵያ መንግስት ያለዉ መረጃ
ምንድነዉ? ከአላሙዲን ጋር ሲበሉ ሲጠጡ ሲያተርፉ ሲነግዱ ያዙን ልቀቁን ሲሉ የነበሩ የት አሉ ? አላሙዲ ታሰረ አልታሰረ ጉዳያቸዉ አይደለም። ነገር ግን በእርሳቸዉ እርዳታ ህክምና ላገኙ እርዳታ ለተደረገላቸው ጥቂት ኢትዮጵያውያን ቤት ተሰርቶ ለተሰጣቸዉ ድሆች ስንል የመሐመድ ቢን ሰልማን ሰለባ እንዲሆኑ አንሻም። በሙስና የሚጠየቁ ከሆነም በፍርድ ቤት በአግባቡ መሆን አለበት ከጥላሁን ገሠሠ እስከ ካሚላት ላደረጉት በጎ ምግባር እናመሰግናለን።"

©Hailemelekot Agizew
@tsegabwolde @tikvahethiopia