TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ፌደራል ፖሊስ⬇️

በሶማሌ ክልል በተከሰተው ቀውስ በአንድ ቀን 96 ሰዎች መገደላቸውን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል #ዘይኑ_ጀማል ለቢቢሲ ገልፀዋል።

ሰዎቹ የተገደሉት ቀውሱ በተነሳበት የመጀመርያው ቀን #ሐምሌ 27፣ 2010 ዓ. ም. ሲሆን፤ በሶማሌ ክልል ዋና ከተማ ጅግጅጋን ጨምሮ በክልሉ የተለያዩ ከተሞች #ግድያው መፈጸሙን ተናግረዋል።

ሰዎቹ የተገደሉት #በአሰቃቂ ሁኔታ መሆኑን ተናግረው፤ ሀይማኖትና ብሔርን ለይቶ የተሰነዘረ ጥቃት እንደሆነ አክለዋል።

"ከዘር #ጭፍጨፋ አይተናነስም" ብለዋል። መነሻው የክልሉ አመራሮች አቅደው፤ ተግባሩን የሚፈጽሙ ሰዎች አሰልጥነውና አሰማርተው መሆኑን ኮሚሽነሩ ገልጸዋል።

እስከ አሁን የክልሉን የቀድሞ ፕሬዘዳንት አቶ አብዲ ሞሀመድ ኡመርን ጨምሮ ሰባት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ተናግረዋል።

'ሄጎ' በመባል የሚታወቀው ቡድን በግድያው እጁ ስለመኖሩ ቢቢሲ ላቀረበላቸው ጥያቄ፤ "በዋናነት በግጭቱ ተሳትፈዋል የሚባሉት #ሄጎ በሚባለው ቡድን አባላት ናቸው። ሄጎ የሚባለውን #የፈጠሩ፣ እቅዱን ያቀነባበሩ የክልሉ የፖለቲካ #አመራሮች፣ የክልሉ የካቢኔ አባላትና ሌሎች የመንግስት ከፍተኛ #ባለስልጣኖችን በቁጥጥር ስር የማዋል ስራ እየሰራን ነው" ብለዋል።

ልዩ ፖሊስ በግድያው ተሳትፎ ስለመሆኑ ከቢቢሲ ለቀረበላቸው ጥያቄ "ማን በምን ደረጃ ተሳተፈ የሚለው ተጣርቶ ለህዝብ ይፋ ይደረጋል" ሲሉ ኮሚሽነሩ አስረድተዋል።

በጅግጅጋ የሚኖሩ የተለያዩ አካባቢዎች ተወላጆች ስጋት እንዳላቸው የሚናገሩት ጄኔራል ዘይኑ፤ የፌደራል ፖሊስና የመከላከያ ሰራዊት የክልልሉን ዋና ዋና ከተማዎች መቆጣጠሩ አንጻራዊ ሰላም ማስፈኑን ገልጸዋል።

በአሁን ወቅት አዲሱ የክልሉ ፕሬዘዳንት አቶ ሙስጠፋ ኡመር በተለያዩ አካባቢዎች እየተዘዋወሩ ህብረተሰቡን እየጎበኙ መሆኑን ተናግረዋል።

የተፈናቀሉ ሰዎችን ወደ አካባቢው መመለስ ቀጣዩ ስራ መሆኑን ተናግረው፤ በዚህ ረገድ የአካባቢው ማህበረሰብ እየተባበራቸው እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

ምንጭ፦ ቢቢሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ #አመራሮች መስከረም 5/2011 ዓ.ም ባሕር ዳር ይገባሉ፡፡ በባሕር ዳር ከተማ ስለሚኖረው የአቀባበል መርሀግብር ኮሚቴው መስከረም 2/2011 ዓ.ም መግለጫ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

©አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ቤንሻንጉል⬇️

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የካማሽ ዞን #አመራሮች ላይ በተፈፀመ ጥቃት፣ አራቱ ህይወታቸው አለፈ።

መስከረም 16፣2011 በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አመራሮች ላይ የተፈፀመዉን ጥቃት ተከትሎ በከማሽ ዞን የተፈጠረዉን #ዉጥረት ለማርገብ የፀጥታ ኃይል በስፍራዉ ደርሶ #የማረጋጋት ስራ እየሰራ መሆኑን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ #ሰይፈዲን_ሐሩን ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳሉት መስከረም 15፣ 2011 ዓ.ም በአሶሳ ከተማ ላይ ተካሂዶ በነበረዉ የቤኒሻንጉል እና የኦሮሚያ ክልሎች የጋራ የፀጥታ ጥምር ኮሚቴ የዉይይት መድረክ ላይ ተሳትፈዉ መስከረም 16፣ 2011 ዓ.ም ወደ ከማሽ ዞን በመመለስ ላይ የነበሩ የዞኑ አመራሮች ላይ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ጊምቢ አካባቢ ማንነታቸው ባልታወቁ ኃይሎች ጥቃት ተፈፅሞባቸዋል፡፡

በጥቃቱም 4 የካማሽ ዞን ከፍተኛ አመራሮች ህይወታቸዉ አልፏል፡፡ ጥቃቱን የፈፀሙ አካላትን በህግ ቁጥጥር ስር ለማዋል መንግስት #የፀጥታ ኃይሎችን በስፍራዉ ማሰማራቱን ኮሚሽነሩ አስታዉቀዋል፡፡

ይሁን እንጂ በከማሽ ዞን አመራሮች ላይ የተፈፀመዉን #ጥቃት ተከትሎ በካማሽ ከተማ ላይ ዉጥረት ነግሷል። የመንግስትና የንግድ ተቋማት ተዘግተዋል፡፡

ዉጥረቱን ለማብረድ የፀጥታ ሃይሎች በስፍራዉ ገብተዉ የማረጋጋት ስራ እየሰሩ መሆናቸዉን ኮሚሽነር ሰይፈዲን ተናግረዋል፡፡

በኦሮሚያና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ህዝቦች መካከል #ግጭት ለመፍጠር የተለያዩ የጥፋት አጀንዳዎችን ይዘዉ የሚንቀሳቀሱ ሀይሎች እንዳሉ ኮሚሽነሩ ተናግረዋል፡፡

እነዚህን ኃይሎች ለመመከት የኦሮሚያና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስታት የጋራ ዕቅድ አዉጥተዉ እየሰሩ መሆናቸዉን ኮሚሽነር ሰይፈዲን ገልጸዋል፡፡

በፀረ ሰላም ሃይሎች ዕኩይ ሴራ በሁለቱ ክልል ህዝቦች መካከል ያለዉ የአንድነትና የትብብር መንፈስ ይበልጥ ያጠነክረዋል እንጂ፣ ሊሸረሽረዉ እንደማይችል ኮሚሽነሩ በመግለጫቸዉ አስታዉቀዋል፡፡

የቤንሻንጉል ጉሙዝ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲን በመወከል በ12ኛው የብአዴን ድርጅታዊ ጉባኤ ላይ ተገኝተው ንግግር ያሰሙት አቶ አሸብር ረጋሳ ተፈፀመውን ጥቃት በማውገዝ ድርጊቱን የፈፀሙ ኃይሎችን በማጋለጥ ለህግ እንዲቀርቡ የአካባቢው ህዝብ እንዲተባበር ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በጥቃቱ ህይወታቸዉን ላጡ የከማሽ ዞን አመራሮች የክልሉ መንግስት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማዉ በመግለጫዉ አስታዉቋል፡፡

ምንጭ፦ etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰበር ዜና‼️

ቤንሻንጉል ጉሙዝ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ/ቤጉህዴፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ በክልሉ ለተከሰተው የጸጥታ መደፍረስ ምክንያት የሆኑ #አመራሮች ተለይተው #እርምጃ እንዲወሰድባቸው መወሰኑን አስታወቀ። ባለፈው ቅዳሜ የተጀመረው የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ እንደቀጠለ ነው፡፡

©ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኮማንድ ፖስት‼️

በቤኒሻንጉል ጉሙዝና በኦሮሚያ አጎራባች አካባቢዎች ተከስቶ በነበረው የጸጥታ መደፍረስ ችግር #የተጠረጠሩ 171 ሰዎች #በቁጥጥር ሥር ዋሉ።

በርካታ የጦር መሳሪያዎችና ገንዘብም በቁጥጥር ሥር እንዲውል መደረጉ ተመልክቷል፡፡

የአካባቢውን ሠላም ለመመለስ የተቋቋመው ኮማን ፖስት አባል እና በሀገር መከላከያ ሠራዊት የምዕራብ ዕዝ ኢንዶክትሪኔሽንና ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮሎኔል #ጌትነት_አዳነ ዛሬ ለኢዜአ እንደገለጹት ኮማንድ ፖስቱ ታህሳስ 11 ቀን 2011 ዓ.ም ከተቋቋመበት ጊዜ አንሰቶ ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ እየሰራ ነው።  

በእዚህም በክልሎቹ አጎራባች አካባቢዎች በታጠቀ ኃይል ተፈጥሮ በነበረ የጸጥታ መደፍረስ ጋር ተያይዞ በጠፋው የሰው ህይወትና በወደመው ንብረት የተጠረጠሩ 171 ሰዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን አስረድተዋል፡፡

ተጠርጣሪዎች የተያዙት ግጭት ከተከሰተባቸው ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ካማሽ ዞን እና ቶንጎ ልዩ ወረዳ እንዲሁም ከኦሮሚያ ክልል ደግሞ ምዕራብ ፣ ምስራቅና ቄለም ወለጋ፣ ሆሩ ጉድሩ፣ ኢሉአባቦራ እና ቡኖ በደሌ ዞኖች መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

በቁጥጥር ሥር ከዋሉት መካከል በየደረጃው የሚገኙ #አመራሮች እንደሚገኙበት ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል፡፡

የታጠቀው ኃይል ለግድያ እና ሌሎች #ጥፋቶች ሲጠቀምባቸው የነበሩ 49 ክላሽንኮብ ጠመንጃዎችና 1 ሺህ 31 የተለያዩ ጥይቶች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ኮሎኔል ጌትነት ጨምረው ገልጸዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ግለሰቦቹ በህገ-ወጥ መንገድ ሲያንቀሳቀሱት የነበረ 1 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር እና 12 ሺህ ዶላር ኮማንድ ፖስቱ መያዙን ነው ያስረዱት።

እንደ ኮሎኔል ጌትነት ገለጻ የጥፋት ኃይሎቹ ተጨማሪ ጥቃት ለመፈጸም ያዘጋጁት ሰባት ጸረ-ተሸከርካሪ ፈንጂዎች፣ 215 ቀስቶች እና የተለያዩ ኮምፒዩተሮችም ተይዘዋል፡፡

ታጣቂ ኃይሉ ከመንግስት መዋቅሮች እና ከግለሰቦች አስገድዶ በመውሰድ ለጥፋት ሲጠቀምባቸው የነበሩ ዘጠኝ አምቡላንሶች፣ አራት አይሱዙ የጭነት ተሽከርካሪዎች፣ ሦስት ቶዮታ ፒክአፕ መኪኖችም ኮማንድ ፖስቱ ማስመለሱን ነው የገለጹት፡፡

ቡድኑ ለጥፋት ሲጠቀምባቸው የነበረውን ንብረት ከማስመለስ ጎን ለጎን በጉዳዩ ላይ ሕብረተሰቡን የማወያየት ሥራ በስፋት እየተካሄደ መሆኑን ኮሎኔል ጌትነት አስረድተዋል፡፡

የጸጥታ ችግር ሲከሰትባቸው በነበረባቸው ዞኖች በአሁኑ ወቅት ግጭት ሙሉ ለሙሉ ቆሞ ወደ ሠላማዊ እንቅስቃሴ መመለሱን ጠቅሰዋል፡፡

ህብረተሰቡ ያደረገው እገዛ ከፍተኛ መሆኑን ኮሎኔል ጌትነት ጠቁመው ኮማንድ ፖስቱ በቀጣይ ችግሩ እንዳይደገም አደረጃጀቱን ከህብረተሰቡ ጋር አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስረድተዋል፡፡

በሁለቱ ክልሎች አጎራባች አካባቢ የደፈረሰውን ሠላም ለመመለስ የተቋቋመው ኮማንድ ፖስት ከፌደራልና ከሁለቱ ክልሎች መንግስታት እንዲሁም ከሀገር መከላከያ እና ከፌደራል ፖሊስ ሠራዊት የተውጣጡ አባላትን ያቀፈ ነው፡፡

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvqhethiopia
የፍቅር #ጉዟችንን በተመለከተ...

በTIKVAH-ETH በኩል #የተሰባሰቡት ወጣቶች ከሁሉም የሀገሪቱ ክፍል የተውጣጡ ትክክለኛውን የኢትዮጵያ ቀለም የያዙ ናቸው። ሁሉም ወጣቶች እናት ሀገራቸውን የሚወዱ እና በሀገሪቱ ላይ አዲስ ታሪክ ለመፃፍ ከሳምንት እስከ ሳምንት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ፤ የትምህርት እና የግል ጊዜያቸውን ትተው ለሰላምና ፍቅር የሚጓዙ ናቸው። ለዚህም ሰላም ወዳዱ የኢትዮጵያ ህዝብ #ሊያመሰግናቸው ይገባል።

ዩኒቨርስቲዎችን በተመለከተ፦

#StopHateSpeech በሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚካሄድ ሲሆን የመጀመሪያው ምዕራፍ ከተማሪዎች ጋር የሚደረግ #ውይይት እና #ንግግር የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ነው። ምክንያቱም ወጣቶች ከጥላቻ እና ከስሜታዊነት ርቀው ሀገር መገንባትና ለህዝብም #ተስፋ የሚሰጡ ዜጎች እንደሆኑ ማስመስከር ስለምንፈልግ ነው።

ይህ ጉዞ እና እንቅስቃሴ ከየትኛውም አይነት የፖለቲካ አመለካከት ነፃ የሆነ፤ ከየትኛውም ድርጅትም ሆነ ቡድን ገለልተኛ የሆነ በወጣቶች የሚደረግ እንቅስቃሴ ነው። ወጣቶቹም ትክክለኛ የሀገሪቱን ቅርፅ የያዙ በፍቅር እና በንግግር የሚያምኑ ሀገሪቷን ከጥላቻ አላቀው ትልቅ ሀገር የመገንባት ህልም ያላቸው ናቸው።

√ወጣቶቹ የሰላምን አርማ ይዘው በየሄዱበት የሚሰብኩት ስለፍቅር እና መተባበር እና መተጋገዝ ብቻ ነው። በሚዘጋጁት መድረኮችም የጥላቻ መዘዞችን ማስገንዘብ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀማቸውን እንዲያሻሽሉ ማስገንዘብ ነው።

√ውይይቶች በጠቅላላ የሚደረጉት #በወጣት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች #መካከል ብቻ ነው። ሌላው ተናጋሪዎች ተማሪዎች እና የዩኒቨርሲቲው አካላት ብቻ ናቸው።

በቀጣይ ምዕራፍ 2፦ ከዩኒቨርሲቲ #አመራሮች እና #ሰራተኞች ጋር ተመሳሳይ መድረክ ይኖረናል።

ኢትዮጵያን በፍቅር እንገንባ!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ እንገናኝ!
(ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ)

ውድ #የሀዋሳ_ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ውድ የTIKVAH-ETH ቤተሰቦች በፍቅር ሀገር እንገንባ #የጥላቻ_ንግግር በተለይ በማህበራዊ ሚዲያ ይቁም በሚል ልዩ መድረክ ተዘጋጅቷል። በዝግጅቱ ከፍተኛ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ #አመራሮች ይገኛሉ። ወጣት ተማሪዎች መልዕክቶችን ያስተላልፋሉ። ባለሞያዎች ስለማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ግንዛቤ ይሰጣሉ።

N.B በዝግጅቱ #ተሳታፊ የሚሆኑ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ #አባላት ለዲላ፣ መቀለ እና ቡሌሆራ ጉዞ ይመዘገባሉ!

ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች እንመጣለን!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ...

#በድሬዳዋ_ዩኒቨርስቲ ውስጥ በፀጥታ ሀይሎች እና በተማሪዎች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት ከትላንት ከሰዓት ጀምሮ ትምህርት መቋረጡን የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት ገልፀዋል።

√ዝርዝር ጉዳዮችን #ከተማሪዎች እና ከዩኒቨርሲቲው #አመራሮች አጣርቼ አሳውቃለሁ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሀሰተኛ የትምህርት መረጃ ...

(በዳውሮ ዞን)

በዳውሮ ዞን ፤  ከጪ በተባለው ወረዳ ለመጀመሪያ ዙር በተደረገ ማጣራት ከ264 የትምህርት መረጃ 127 #ሀሰተኛ ሆኖ መገኘቱ ተሰምቷል።

ሀሰተኛ ሆኖ ከተገኘው የትምህርት መረጃ መካከል 6ቱ #የአመራርና ቀሪው #የመንግስት_ሰራተኞች ነው።

የሁለተኛ ዙሪ የማጥራት ስራ እንደሚቀጥል ተገልጿል።

በዚሁ ዞን ፤ ቶጫ በተባለው ወረዳ በመጀመሪያ ዙር ከተደረገው ማጣራት ከ565 የትምህርት መረጃ የ218 ሰዎች #ሀሰተኛ ሆኖ ተገኝቷል።

መረጃቸው ወደ ግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተልኮ ከተጣራው ከ565 የመንግስት ሰራተኞች መካካል የ210 ባለሙያዎችና የ8 #አመራሮች የትምህርት መረጃ ነው ሀሰተኛ ሆኖ የተገኘው።

ይኸው የማጣራት ስራ ይቀጥላል ተብሏል።

መረጃው ከዳውሮ ኮሚኒኬሽን የተገኘ ነው።

@tikvahethiopia
#ወላይታሶዶ_ዩኒቨርሲቲ

• " ለጉልበት ሰራተኞች 4 ሚሊዮን ብር ተከፍሏል ቢባልም ገንዘብ መውጣቱን እንጂ #የት_እንደገባ ማረጋገጥ አልተቻለም " - የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲን የ2013 በጀት ዓመት የሒሳብ ህጋዊነት ኦዲት ሪፖርትን ከትምህርት ሚኒስቴር፣ ከገንዘብ ሚኒስቴር፣ ከዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ገምግሟል።

በዚህ ግምገማ ምን ተባለ ?

- ዩኒቨርሲቲው የኦዲት ግኝቱን የማስተካከያ እርምጃ እየወሰደ ባለመሆኑ ባለፉት አራት ዓመታት ተቀባይነት የሚያሳጣ የኦዲት አስተያየት ውስጥ ያለፈ ተቋም እንደሆነና በትኩረት መስራት እንዳለበት ቋሚ ኮሚቴው አስገንዝቧል።

- ዩኒቨርሲቲው ማስመለስ ከነበረበት የገንዘብ ምጣኔ 99.95% እንዳላስመለሰ እና የኦዲት ግኝት መስተካከል ከነበረበት 11 ጉልህ  የኦዲት ግኝቶች 1 ብቻ ምላሽ እንዳገኘ ኮሚቴው ገልጿል።

- የዩኒቨርሲቲው አመራር የፋይናንስ ህግጋትን እና አሰራሮችን ተከትሎ ከመስራት አኳያ ሰፊ ክፍተት በመኖሩ በትኩረት መስራት አለበት ተብሏል።

- ዩኒቨርሲቲው ባልተሰጠው ስልጣን አዳዲስ ደንቦችን እና መመሪያዎችን እያዘጋጀ ክፍያ ሲፈፅም የነበረ ሲሆን #ለጉልበት_ሰራተኞች አራት (4) ሚሊዮን ብር ተከፍሏል ቢባልም ገንዘብ መውጣቱን እንጂ የት እንደገባ ማረጋገጥ እንዳልተቻለ ኮሚቴው ገልጿል።

የኦዲት ግኝቶችን በተመለከተ የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ክርስትያን ታደለ ምን አሉ ?

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የተሻሻለ የኦዲት ግኝት ማሻሻያ መርሃ-ግብሩን እስከ መጋቢት 23/2015 ዓ.ም እንዲያቀርብ እና መርሃ-ግብሩም ፦
- ለገንዘብ ሚኒስቴር፣
- ለፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት እና ለሰው ኃብት ልማት፣ ስራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ግልባጭ ሪፖርት ማድረግ እንዳለበት አስገንዝበዋል።

ተቋሙ የኦዲት ግኝቶችን ትኩረት ሰጥቶ ተገቢውን የእርምት ዕርምጃዎችን እየወሰደ በየ 3 ወሩ ለቋሚ ኮሚቴው ሪፖርት ማቅረብ አለበት ብለዋል።

አያይዘውም ገንዘብ ሚኒስቴር ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ባልተወጡ የዩኒቨርሲቲው #አመራሮች እና የሥራ ኃላፊዎች ላይ አስተዳደራዊ ዕርምጃዎችን ወስዶ ሪፖርቱን በ10 ቀናት ውስጥ ማሳወቅ እንደሚገባው አስገንዝበዋል።

የፍትህ ሚኒስቴር #በወንጀለኛ እና #በፍትሃብሄር ተጠያቂነት የሚያስከትሉ ጉዳዮች ካሉ መርምሮ ክስ መመስረት እንዳለበት አቶ ክርስቲያን ታደለ አስረድተዋል።

አቶ ክርስትያን የሰው ኃብት ልማት፣ ስራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኦዲት ሪፖርቱን መነሻ በማድረግ ተገቢውን የቁጥጥር ስራ እንዲሰራ እና የኦዲት ግኝቶች ዩኒቨርሲቲው የእቅድ አካል አድርጎ እንዲያካትታቸው ተገቢውን አመራር  እንዲሰጥ አሳስበዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ከስልጣኑ ውጪ ባወጣቸው ደንቦች እና መመሪያዎች የሚያደርጋቸውን ክፍያዎች እንዲያቆም እና በቀጣይም በመንግስት የፋይናንስ ህግጋት እና መመሪያዎች ተንተርሶ ብቻ መስራት እንዳለበት፤ ያለ አግባብ የተከፈሉ ክፍያዎችም ተመላሽ እንዲሆኑ አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡

#FDRE_HoPR

@tikvahethiopia
#DrAbrhamBelay

የሀገር መከላከያ ሚኒስትር ዶክተር አብርሃም በላይ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በትግርኛ ቋንቋ ለብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት ቃለ ምልልስ ምን አሉ ?

- ሁሉም ክልሎች እና የፌደራል መንግስት ተቋማት ለትግራይ መልሶ ማቋቋም እንዲረዱ ፣ ትምህርት ጨምሮ ሁሉም የመንግስት አገልግሎቶች እንዲጀምሩ ያስቻለው የፕሪቶሪያው የሰላም ውል ነው ፡፡ ስለሆንም የፕሪቶሪያው የሰላም ውል አሁንም በቦታው ነው ያለው።

- ከጦርነቱ በፊት የነበረው #ግጭት_ቆስቋሽ ሁኔታ እና አካሄድ ወደ ጦርነት እንዳይሸጋገር ለማድረግ በፌደራሉ መንግስት ብዙ ጥረት ተደርጓል። ክልሉን ይመሩ የነበሩ ሰዎች ሁኔታውን ከማባባስ እንዲቆጠቡ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት ተደርጓል። ጦርነቱ በትግራይ #አመራሮች እና #ኤሊቶች ገፋፊነት ከተጀመረ በኋላም ጦርነቱ ቆሞ ወደ ውይይት እንዲገባ ጥረት ተደርጓል። ጦርነቱ ውድመቱ እንዳይባባስ በድብቅም ይሁን በግላጭ በርካታ ውይይቶች ቢካሄዱም ሊሳካ አልቻለም።

- ጦርነቱ ተከትሎ በተለይም ከትግራይ ውጪ በመላ አገሪቱ ውስጥ የነበሩ ባለሃብቶች ፣ የመንግስት ሰራተኞችና በሌላ ስራ የተሰማሩ ከስራ ውጪ የሆኑበት ፣ የታሰሩበት ፣ ንብረታቸው በርካሽ በመሸጥ እንዲሰደዱ የሚገደዱበት ሁኔታ ተፈጥሮ ነበር። ይህን እንዲቆም የፌደራል መንግስት ባደረገው ሰፊ ጥረት ሙሉ በሙሉ ባይሆንም ብዙ አላሳፈላጊ ነገሮች ማቆም ተችሏል።

- " በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ከኔ በላይ ደስተኛ ያለ አይመስለኝም። ምክንያቱ ስምምነቱ ብዙ ነገሮችን ከማባባስ ታድጓል፡፡ በፌደራል መንግሥት በኩል ስምምነቱን የፈረሙ የመንግስት ልኡካን ጀግኖች ናቸው፡፡ ምክንያቱ እንደ አገር ሊቀጥል የነበረው የስውና የንብረት ኪሳራ እንዲቆም ያደረጉ ናቸውና፡፡ "

- የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ሁሉም የትግራይ ችግሮች ይፈታል ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው። ስምምነቱ እንደ አገርና ትግራይ ብዙ ጥፋቶችን አስቁሞልናል፡፡ ስምምነቱ በመፈረሙ ምክንያት ተኩሶ ቆሞ ህዝቡ የሰላም አየር እንዲተነፍስ ሆኗል፡፡ ትልቁ የስምምነቱ ትሩፋት ይህ ነው።

- ከተወሰኑት በቀር በርካታው የትግራይ አከባቢዎች በፌደራል መንግስት ቁጥጥር ስር ውለው ነበር። በፕሪቶሪያ ስምምነት መሰረት የአከካቢው አስተዳደር ተረክቧል። አሁን የተቀሩት አከራካሪ የሚባሉ ቦታዎች ናቸው። እነዚህም ተጨማሪ ግጭትና ደም መፋሰስ እንዳያስከትሉ በማሰብ በፌደራል መከላከያ ሰራዊት ስር እንዲቆዩ ተደርጓል።

- በትግራይ ክልል የተቋቋመው ጊዚያዊ አስተዳደር የፕሪቶሪያው የሰላም ውል ውጤት ነው። ሁሉም ክልሎችና የፌደራል መንግስት ተቋማት ለክልሉ እንዲረዱ ፣ ትምህርት ጨምሮ ሁሉም የመንግስት አገልግሎት እንዲጀምሩ ያስቻለው የፕሪቶሪያው የሰላም ውል ነው ፣  ስለሆንም የፕሪቶሪያው የሰላም ውል አሁንም በቦታው አለ።

- ስምምነቱ ከውል በላይ በሁለቱ ተወያዮች በኩል መተማመን እንዲፈጠረ ያበረከተው አስተዋፅኦ ስምምነቱ ከስምምነት በላይ መሆኑ አንድ አመላካች ተደርጎ ይወሰዳል።

- የእርሻ እና የኢንዳስትሪ ስራ እንዲነቃቃ የሚያግዝ የማሽነሪና የውጭ ምንዛሪ መሰጠቱ፣ የክልሉ የትምህርትና የጤና ተቋማት መልሶ የመገንባት ሂደት እንዲፋጠን ያስቻለው የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ውጤት ነው።

- የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት የፌደራል መንግስት የሚመራውን የብልፅግና ፓርቲ ጨምሮ ሌሎች የፓለቲካ ፓርቲዎች የተካተቱበት አሳታፊ ጊዚያዊ አስተዳደር እንዲቋቋም ቢደነግግም ፣ የፌደራል መንግስትና የብልፅግና ፓርቲ በሆደ ሰፊነትና ለሰላም ካለቸው ፍላጎት በሚመነጭ ክልሉ ሃላፊነት ወስዶ በፍጥነት ጊዚያዊ አስተዳደር እንዲመሰረት እድል መሰጠቱ ሊመሰገንና እውቅና ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው።

- ከትግራይ ምዕራባዊና ደቡባዊ ዞኖች የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ ቄያቸው የመመለስ ጉዳይ መዘግየቱ አለ የሚባል ቢሆንም የተዘነጋ እንዳልሆነ ግን ሊሰመርበት ይገባል። የፌደራል መንግስት ፍላጎት ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ ማድረግ ነው። ይህ አቋሙም ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ውል ማግስት ጥረት ከማድረግ ባሻገር 2015 ዓ.ም ክረምት እንዲመለስ ፍላጎት ነበር። ይሁን እንጂ በአፈፃፀም መዘግየት ምክንያት እስከ አሁን አልተሳካም።

- ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው የመመለስ ጉዳይ ዳግም ወደ ጦርነት በማይመልሰን መልኩ መፈፀም አለበት የሚለው አቅጣጫ ተቀምጦ የፌደራል መከላከያ ሰራዊት ጥያቄዎች በሚነሳባቸው አከባቢዎች ያሉ ታጣቂዎች ትጥቃቸው እንዲፈቱ የማድረግ ስራ እየሰራ ነው። ቢሆንም ህዝቡ ሙሉ በሙሉ ወደ አከባቢው አልተመለሰም የፌደራል መንግስት አቋም ህዝቡ ወደ ቄየው ተመልሶ የራሱ አመራሮች መርጦ በአመቺ ጊዜ በአከባቢው ህዝብ ውሳኔ እንዲካሄድ ማድረግ ነው።

- የፌደራል መንግስት አቋም ግልፅ ነው ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው ይመለሱ ፣ ራሳቸው በመረጡዋቸው መሪዎች ይተዳደሩ ፣ የህዝበ ውሳኔው ጉዳይ ጊዜ ሲደርስ የሚከናወን ይሆናል። አሁንም አቅጣጫው እንዲፈፀም በመጠባበቅ ላይ ነን ፣ ዳግም ግጭት ሳይፈጠር ከዚህ በላይ የተሻለ አማራጭ አለኝ የሚል ካለ ደግሞ የፌደራል መንግስት ለማዳመጥ ዝግጁ ነው። 

- የሻብዕያ ሰራዊት ከኢትዮጵያ መሬት ስለመውጣት ጉዳይ ምን አሉ ? 👉 "  ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በፊት በበርካታ የትግራይ አከባቢዎች የሻዕብያ ሃይል ገብቶ ነበር ፣ ከስምምነቱ በኋላ እንዲወጣ ተደርጓል ፣ አሁንም የተቀሩ ቦታዎች ካሉ ቦታዎቹ እና ቀበሌዎች ከፌደራልና ከትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የተውጣጣ ቡድን በዝርዝር አጥንቶ እንዲያቀርብና መፍትሄ እንዲሰጠው እየሰራን ነው ሁሉም ልክና መስመር ይይዛል። "

- በትግራይ የተከሰተው ድርቅ እና ረሃብ በተለመደው አካሄድ ይፈታል የሚል እምነት የለንም ፣  እርግጥ ነው ወደ አከባቢው መድረስ ያለበት የሰብአዊ ድጋፍ እየደረሰ ነው ፣ እየተላከ ያለው ድጋፍ ወደ ተጠቃሚው መድረሱ ማረጋገጥ እንዳለ ሆኖ ፣ ሁሉም የኢትዮጵያ ክልሎችና የፈደራል የመንግስት ተቋማት እገዛ በማድረግ ችግሩ በመፍታት እንዲረባረቡ አቅጣጫ ተቀምጧል።

- በትግራይ የተከሰተው ድርቅ እና ረሃብ በዘላቂነት የሚፈታ ከፌደራልና ከክልሉ የተውጣጣ ግብረ ሃይል ተቋቁሞ በቅርቡ ይፋ ይደረጋል። ይህንን ግብረ ሃይል የሚያቀርበው ጥያቄ ለመመለስ ሁሉም የትግራይ ተወላጆችና መላ ኢትዮጵያውያን ዝግጁ እንዲሆኑ ከወዲሁ ጥሪ እናቀርባለን።

ቃለ ምልልሱን ተከታትሎና ወደ አማርኛ ትርጉም መልሶ ያቀረበው የመቐለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው፡፡

#TikvahMekelleFamily

@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

" ይህ ጉባኤ ትግራይን እና ህዝቡን ወደ አደጋ ከመክተት የዘለለ እርባና የለውም " - አቶ ጌታቸው ረዳ

የህወሓት ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳ ከደቂቃዎች በፊት መግለጫ አውጥተዋል።

ጉባኤው " በችኮላና የጋራ መግባባት ሳይደረስበት ፤ በማደናገርና በአቋም አልባነት አሰባስበናቸዋል በሚሉት ኔትወርክ  ' ይቃወሙናል ' የሚሉዋቸው የተወሰኑ #አመራሮች_ለማስወገድ በማለም የሚካሄድ ጉባኤ ነው " ብለውታል።

" ይህ ጉባኤ ትግራይን እና ህዝቡን ወደ አደጋ ከመክተት የዘለለ እርባና የለውም " ሲሉ ገልጸዋል።

ምክትል ሊቀመንበሩ  ፤ " የተሻሻለው የፓለቲካ ፓርቲዎች የምዝገባ አዋጅ ህወሓት እንደ አዲስ እንደሚዘገብ የሚያደርግ ፣ ወርቃዊው የትግራይ ህዝብ ትግል የሚያጎድፍ በቀጣይ ቅርቃር ውስጥ የሚከት መሆኑን በመገንዘብ ችግሮች በሰላማዊ መንገድ ብቻ እንዲፈቱ በማእከላዊ ኮሚቴ አባላት መግባባት ተደርሶ ነበር " ብለዋል።

" ይሁን እንጂ የተደረሰው መግባባትና መተማመን ወደ ጎን በመተው ' ከፌደራል መንግስት ተማምነናል ' በሚል ማደናገሪያ ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለመነጋገር  ከማእከላዊ ኮሚቴ እና ካድሬ በመደበቅ የተሄዴበት ሂደት ወዳልተፈለገ ወጥመድ እንድንገባ ተደርገናል " ብለዋል።

" በዚህ ምክንያት የሚፈጠር ማንኛውም ጥፋት ተጠያቂው ለጠባብ ቡድናዊ ፍላጎቱ ብቻ የሚንቀሳቀሰው ቡድን ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

አቶ ጌታቸው ፥ " የህዝቡ ሰላም እንዳይደፈርስና እንዳይረበሽ ከህዝባችንና ከመላ አባላችን በመሆን እንታገላለን " ብለዋል።

" ሁሉም የትግራይ አቅሞች በማቀናጀት በተደራጀ ትግል ከፍተኛ ፓለቲካዊ ድርድር በማካሄድ የህወሓት ህጋዊነት በመመለስ ካጠላብን ዙርያ መለስ ፈተና በመውጣት የትግራይ የተሟላ ደህንነትና እድገት እንደሚረጋገጥ ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ " ብለዋል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia