TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ትውልድ አድን‼️

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት #ሠላማዊ የመማር ማስተማር ከባቢ ይፈጥራል ተብሎ የታመነበት “ትውልድ አድን” የተሰኘ የህይወት ክህሎት ሥልጠና መርሃ-ግብር ሊጀመር ነው።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችም ሠላማዊ የመማር ማስተማር ከባቢ ለመፍጠር የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡም ጥሪ ቀርቧል።

የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ወልደማርያም ዛሬ በዩኒቨርስቲዎች ወቅታዊ ሁኔታ ላይ መግለጫ በሰጡበት ወቅት ነው  ይህንን የተናገሩት።

ሚኒስቴር መሥሪያ ቤታቸውም ሠላማዊ የመማር ማስተማር ከባቢ ለመፍጠር የሚያስችል “ትውልድ አድን” የተሰኘ የህይወት ክህሎት ሥልጠና መርሃ-ግብር ሊጀመር መሆኑን በዚህ ወቅት ጠቁመዋል።

በአንዳንድ ዩኒቨርስቲዎችም መርሃ-ግብሩ በጅምር ላይ መሆኑን ጠቁመው በታዋቂ ግለሰቦች፣ በአርቲስቶችና በሥነ-ልቦና ባለሙያዎች የሚካሄድ ነው ብለዋል።

ሚኒስትሯ እንዳሉት አገሪቱ በአሁኑ ወቅት ሥር-ነቀል የለውጥ ሂደት ላይ በመሆኗ የተለያዩ ችግሮችን እያስተናገደች ነው።

በተለይም ሂደቱን #ለማደናቀፍ የሚሠሩ ኃይሎች ዩኒቨርሲቲዎች ትኩረት ማድረጋቸውን ጠቁመው ይህ እንዲሆን የተፈለገው ተቋማቱ “ትንሿን ኢትዮጵያ” የመወከል አቅም ስላላቸው ነው ብለዋል።

ተማሪዎች ይህንን በመገንዘብ ችግሮችን ከወዲሁ መከላከል እንደሚገባ ገልጸው በዩኒቨርስቲዎች ሠላማዊ የመማር ማስተማር እንዲጠናከር መሥራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ማሳሰቢያ‼️

ወህዴግ በማህበራዊ ሚዲያ በቀን 19/03/2011 ዓ.ም #በወላይታ_ሶዶ ከተማ #ሠላማዊ_ሰልፍ እንደሚያደርግ እየገለፀ ያለ ቢሆንም የዞኑ አስተዳደር አሁን ያለውን #የፀጥታ ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት ፍቃድ ያልተሰጠ ስለሆነና ነባራዊ ሁኔታን በመገምገም ወደፊት የሚፈቅድ መሆኑ ታውቆ በተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮችም ሆነ አባላት የሚደረገው ቅስቀሳ ተገቢ ያለመሆኑን በመገንዘብ #ጥንቃቄ እንዲደረግ እናሳስባለን፡፡

©Wolaita ZONE Culture, tourisim and Governmental Communication Affairs Office
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ🔝

ከወርሃ ጥር ጀምሮ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ቦርድ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአመራርና አስተዳደደር ሃላፊዎች #ሹመትን አስመልክቶ የወጣውን መመሪያ ተከትሎ የፕሬዝዳንት አፈላላጊ ኮሚቴ በመሰየም ተግባራዊ እንቅስቃሴ ሲያደርግ መቆየቱ ይታወሳል፡፡

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የፕሬዝዳንት አፈላላጊ ኮሚቴም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአመራርና አስተዳደደር ሃላፊዎችን ምርጫና ሹመት/ምደባ አስመልክቶ የወጣውን መመሪያ ቁጥር 002/2011 ተግባራዊ በማደረግ ሃላፊነቱን በብቃት ሲወጣ ቆይቷል፡፡

በምልመላ እና መረጣ ሂደት ውስጥ በመስፈርትነት የተቀመጡ የትምህርት ዝግጅት፣ የአመራር ልምድ፣ በማስተማር እና በምርምር የተገኘ ልምድን መሰረት በማድረግ ከቀረቡ አሰር ዕጩዎች ተገቢውን መስፈርት የሚያሟሉ ስምንት ተወዳዳሪዎችን ለስትራቴጂክ ዕቅድ ገለጻ ኮሚቴው በመምረጥ ለውድድር አቅርቧል፡፡

ዕጩ ተወዳዳሪዎቹም የቦርድ አመራሮች፣ የሴኔት መማክርት አባላት፣የማኔጅመንት ሃላፊዎች፣በተቋሙ ከሚገኙ ከሁሉም የአካዳሚክ ዘርፎች እና የአስተዳዳር ክፍሎች የተወጣጡ የስራ ሃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ስትራቴጂክ እቅዳቸውን ማቅረብ ችለዋል፡፡

በተሰጣቸው አስራ አምስት ደቂቃ ስትራቴጅክ ዕቅዳቸውን በማቅረብ፣ ከተሳታፊ ለሚነሳላቸው ጥያቄ ለአስራ አመስት ተጨማሪ ደቂቃ ማብራሪያ እንዲሰጡ ተደርጎ በሚስጥራዊ የድምጽ አሰጣጥ ሂደት ዕጩ #ተወዳዳሪዎች ድምጽ እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡

በምርጫው ሂደት ከተሳተፉ ስምንት ዕጩዎች አምስቱ ተለይተው ለቀጣዩ ሂደት ለዩኒቨርሲቲው ቦርድ የቀረቡ ሲሆን፤መስፈርቱን በማሟላት ከአንድ እስከ አምስት የወጡ ጩዎች ይፋ ተደርገዋል፡፡

በዚህም መሰረት፡-

1. ዶ/ር ታከለ ታደሰ (ተባባሪ ፕሮፌሰር) 88.33 በማምጣት 1ኛ
2. ዶ/ር አብርሃም አላኖ(ተባባሪ ፕሮፌሰር) 77.7 በማምጣት 2ኛ
3. ዶ/ር ሰለሞን ለማ (ተባባሪ ፕሮፌሰር) 72.94 በማምጣት 3ኛ
4. ዶ/ር ወንድሙ ወልዴ( ረዳት ፕሮፌሰር) 70.37 በማምጣት 4ኛ
5. ዶ/ር መስፍን ቢቢሶ(ተባባሪ ፕሮፌሰር) 66.78 በማምጣት 5ኛ ደረጃን የያዙ ሲሆን በአሰራሩ መሰረት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአመራርና አስተዳደደር #ሃላፊዎች ሹመትን አስመልክቶ የወጣውን መመሪያ በሚደነግገው መሰረት #የዩኒቨርሲቲው ቦርድ ከሚቀርቡለት አምስት ዕጩዎች ሶስቱን ለይቶ ለትምህርት ሚኒስቴር እንሚልክ ተጠቁሟል፡፡

የውድድር ሂደቱ ፍጹም #ሠላማዊ እንደነበር እና መመሪያና ደንቡ በሚፈቅደው ልክ ግልጽ አሰራርን ተከትሎ ተግባራዊ መደረጉን የዩኒቨርሲቲው ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር #ቶላ_በሪሶ ገልጸዋል ሲል የዘገበው የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮሚኒዩኬሽንና ዓለም ዓቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ነው፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በምዕራብ ኢትዮጵያ #የጥፋት ኃይሎች በስፋት ሲንቀሳቀሱበት የነበረውን የምዕራብ ኦሮሚያና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች የምዕራብ ኢትዮጵያ ኮማንድ ፖስት በወሰደው #እርምጃ ማረጋጋት እንደተቻለ የኢፌዴሪ መከላከያ ምክትል ኢታማጆር ሹም ጀኔራል #ብርሃኑ_ጁላ ተናገሩ ። ዛሬ የምዕራብ ኢትዮጵያ ኮማንድ ፖስት በአሶሳ ከተማ ገምገማ አካሂዷል። በግምገማው ወቅት ህብረተሰቡ ከነበረበት የሥጋት ስሜት ወጥቶ በአካባቢው #ሠላማዊ በሆነ መንገድ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ተገልጿል፤ ቀጣይነቱን ለማረጋገጥ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱን ማጠናከር ይገባል ተብሏል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
በሐዋሳ አካባቢ ያለው እንቅስቃሴ ወደ #ሠላማዊ ሁኔታ እየተመለሠ መሆኑ ተገልጿል።

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/HW-07-21