TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE ትምህርት ሚኒስቴር ከነገ መስከረም 23 ጀምሮ የብሔራዊ የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ የልምምድ ፈተና (Mock Exam) መሰጠት እንደሚጀመር አሳውቋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሠጠው ብሔራዊ የድህረ-ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና ከመስከረም 28 እስከ 30 ቀን 2016 ዓ.ም በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይሰጣል። ሚኒስቴሩ ፤ በሁሉም የመንግስትና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት…
" ፈተናው የምርጫ ጥያቄዎችን የያዘ ነው " - ትምህርት ሚኒስቴር

ትምህርት ሚኒስቴር ከመስከረም 28 እስከ 30 /2016 ዓ/ም በሀገር ደረጃ የሚሰጠው የድህረ ምረቃ ትምህርት የመግቢያ ፈተና ወጥ በሆነ መንገድ በአንድ የፈተና መተግበሪያ የሚከወን መሆኑን ገልጿል።

ፈተናው #ምርጫ_ጥያቄዎችን የያዘ ነው ብሏል።

ለፈተናው 53 የፈተና ማእከላት እና 84 የፈተና ጣቢዎች የተዘጋጁ ሲሆን በግማሽ ቀን ውስጥ የሚጠናቀቅ ይሆናል ተብሎ ታቅዷል።

አይነስውራን ተፈታኞች የቃል እና ምክንያታዊ አስተሣሠብ ክህሎቶቻቸው ላይ ያተኮሩ ፈተናዎችን ይወስዳሉ ያለው ሚኒስቴሩ በወሠዱትም ፈተና ከ100% ይመዘናሉ ብሏል።

ብሄራዊ የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና ጥያቄዎች አመልካቾች መርጠው በሚያመለክቱበት የትምህርት መስክ ላይ ትኩረት ያደረገ እንዳልሆነ ትምህርት ሚኒስቴትር ገልጿል።

ትምህርት ሚኒስቴር የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና ዓላማ ፦

- በግል እና በመንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ገብተው የድህረ ምረቃ ትምህርት በ2ኛ እና 3ኛ ዲግሪ የትምህርት ፕሮግራሞች ገብቶ ትምህርት ለመከታተል ፍላጎት ያላቸውን አመልካቾች ብቃት ለመመዘን፤

- ድህረ ምረቃ ትምህርት ፕሮግራሞች የሚገቡ ተማሪዎች ሂሣባዊ ትንተና (Quantitative reasoning) ፣ ምክናያታዊ አስተሳሠብ (Analytical reasoning) ፣ የቃልና የጹህፍ ከህሎት ለመመዘን ነው ሲል አስታውሷል።

@tikvahethiopia