TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ባለፈው ሳምንት በምዕራብ ጎንደር የታገቱ ሰዎች #መለቀቃቸውን የአማራ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽነር አቶ ዘለዓለም ልጅዓለም በዛሬው ዕለት በባሕር ዳር ከተማ በሚገኘው ጽሕፈት ቤታቸው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ታጋቾቹ መለቀቃቸውን አረጋግጠዋል። ኃላፊው «የታገቱ ሰዎች ነበሩ ሙሉ በሙሉ ተለቅቀዋል» ሲሉ አረጋግጠዋል።
ከጎንደር ወደ ገንዳውሐ በመጓዝ ላይ የነበሩ መንገደኞች በምዕራብ ጎንደር ዞን መቃ በተባለች አነስተኛ ከተማ የታገቱት ባለፈው የካቲት 12 ቀን፣ 2011 ዓ.ም. ነበር። የምዕራብ ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪ እና የሰላምና የሕዝብ ደኅንነት መምሪያ ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ጣሰዉ «በአጠቃላይ የታገቱ ሰዎች ከሰባት እስከ ስምንት ሊሆኑ ይችላሉ» ብለው ነበር። የአማራ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ዘለዓለም ልጅዓለም በዛሬው መግለጫቸው አጋቾቹን #በቁጥጥር ሥር ለማዋል ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል።

ምንጭ፦ የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia