TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የፌስቡክ አስተያየት ሰጪዎች እነማን ናቸው

#አብዛኞቹ በተለያዩ #የፌስቡክ_ፖስቶች ላይ/በዜና ማሰራጫዎች፣ በታዋቂ ግለሰቦች ገፅ፣ በአክቲቪስቶች እንዲሁም በሌሎች.../ የስድብ ናዳ የሚያወርዱት፤ ህዝብን የሚያሸብሩት፤ ሀገሪቱ ፍፁም እልቂት ውስጥ ልትገባ እንደሆነ የሚዝቱት፤ እርስ በእርስ ፍጅት እንዲነሳ የሚቀሰቅሱት፤ በተላለፉ መረጃዎች ላይ በሙሉ ስድብ እና ጥላቻን፣ አሉባልታን የሚፅፉት አብዛኞቹ #ሀሰተኛ ገፅ ናቸው። የሰዎቹ ማንነት የማይታወቅ፣ ምስላቸው የሌለ፣ ለግጭት እንዲሁም ህዝብን ለማወናበድ የተከፈቱ ናቸውና ተጠንቀቁ። በምታነቡት አስተያየትም ተስፋ አትቁረጡ።

በሌላ በኩል...

ትክክለኛ አመለካከታቸውን #በስድብ እና በኃይል ለመግለፅ የሚሞክሩም እንዳሉ ልታውቁ ይገባል። ማስረጃን አቅርቦ ከመከራከር ይልቅ ስድብ ባህል ያደረጉ ወገኖች አሉና ከቻልን ቀርበን እናስተካክላቸው።

ኢትዮጵያ ሰላም ትሁን፤
ዜጎቿም ሰላም ወጥተው ይግቡ!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia