TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#የመንገድ_ጥያቄ

ከሀላባ-ደንቦያ-ዱራሜ-አንጋጫ-ዋቶ ያለው የ65 ኪሎ ሜትር የመንገድ ኘሮጀክት ባለመሰራቱና ባለመጠናቀቁ ህዝቡ ክፉኛ እየተቸገረ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪ የሆኑ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ቅሬታ አቅርበዋል።

አስተያየታቸው የላኩን አንድ ነዋሪ ፤ ለከምባታ ህዝብ ብቸኛ መተንፈሻ የሆነው ከሀላባ - ደንቦያ - ዱራሜ - አንጋጫ-ዋቶ ያለው የ65 ኪሎ ሜትር የመንገድ ኘሮጀክት ባለመጠናወቁ ህዝቡ እየተቸገረ ነው ብለዋል።

" የመንገዱን ስራ ለመስራትና ለማጠናቀቅ በየዓመቱ ሙከራ ከማድረግ ውጪ የረባ ተግባራዊ ጥረት አልተደረገም " ሲሉ ቅሬታቸውን ገልጸዋል።

ሌላ አስተያየይ የተቀበልናቸው አንድ ነዋሪ በዚህ መንገድ አለመሰራት ሳቢያ ህዝቡ ክፉኛ እየተሰቃየ ነው ብለዋል።

በመንገዱ አለመሰራት ምክንያት የሚደርሰውን ችግር እንዲሁ በቃላት ለመግለፅ እንደሚያዳግት አስረድተዋል።

የሚመለከተው አካል መንገዱን ለመስራት እና ለማጠናቀቅ ያልተቻለበትን ምክንያት በዝርዝር በመፈተሽ ፈጣን መፍትሄ እንዲሰጡ ጠይቀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በዚህ ህዝብ በሚንገላታበት የመንገድ ፕሮጀክት ዙሪያ የሚመለከታቸውን አካላት ለማነጋገር ጥረት ያደርጋል።

@tikvahethiopia