TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update አዲስ አበባ⬇️

አዲሱ የአዲስ አበባ አስተዳደር የኮንዶሚኒየምና የቀበሌ ቤቶች ቆጠራ #በድጋሚ እንዲካሄድ ትዕዛዝ መጠቱ ተሰማ፡፡

ካቢኔው ከ2003 ዓ.ም. ወዲህ ለመጀመርያ ጊዜ የመሬትና #መሬት ነክ አገልግሎት ዘርፍ #ኦዲት እንዲደረግ ወስኗል፡፡

በቀድሞ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ድሪባ ኩማ የሥልጣን ዘመን የኮንዶሚኒየም ቤቶችና የቀበሌ ቤቶች ቆጠራ ተካሂዶ የነበረ ቢሆንም አዲሱ አስተዳዳር “እንደገና ይቆጠር” ብሏል፡፡

©ዋዜማ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የመቐለ ከተማ አስተዳደር 13 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ላስመዘገቡ 222 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት #መሬት በዕጣ ማስረከቡ ተገልጿል፡፡ ባለሀብቶቹ ለ22 ሺ 9 መቶ ዜጎች #የሥራ_ዕድል ይፈጥራሉ ተብሏል፡፡

Via etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #አሁን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ስብሰባ እየተካሄደ ነው፡፡ ስብሰባው የኢፌዴሪ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት ነው እየተካሄደ የሚገኘው። የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላትም ጥያቄዎችና አስተያየቶችን እያቀረቡ ይገኛሉ። እስካሁን ባለው ከተወካዮች ም/ ቤት አባላት ምን ምን ጉዳዮች ተነሱ ? - የኦሮሚያ እና አማራ ክልል የፀጥታ ሁኔታ ፣ …
#ጥያቄ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ወ/ሮ ከድጃ ያሲን ፦

" ... የብልሹ አሰራር ከማስወገድና የፀረ-ሌብነት ትግልን ከማጠናከር አንፃር መንግሥት በየደረጃው ተጠያቂነትን ለማስፈን ምን ያህል ቁርጠኛ ነው ? በፀረ-ሌብነት ትግሉ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ምን ይጠበቃል ?

ሰፊ የሀብት ብክነት እና ሌብነት በሚታይባቸው ለምሳሌ እንደ #መሬት_አስተዳደር#ገቢዎች#የጉምሩክ_አገልግሎት ፣ ትላልቅ ግዢዎች እና የኮንስትራክሽን ዘርፍን ከሌብነት እና ከብክነት የፀዳ እንዲሆን እንደ መንግስት የተያዘው አቋም ላይ ማብራሪያ ይሰጥ። "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ፍትህን እስከምናገኝ ድረስ የሚከፈለውን መስዋዕትነት እንከፍላለን " - ካውንስሉ በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ከርስቲያን ኩሪፍቱ ማዕከል ላይ የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ኢ-ህገ መንግስታዊ ጥሰት እየፈጸመ እንደሆነ የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስትያናት ካውንስል አሳወቀ። ድርጊቱን በመቃወምም መግለጫ አውጥቷል። ካውንስሉ ፤ የኩሪፍቱ ማዕከል በህጋዊ መንገድ ለቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የተሰጠ…
🔈#የኢትዮጵያ_ቃለ_ሕይወት_ቤተክርስቲያን

በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የኩሪፍቱ ማዕከል ይዞታ ላይ በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት እየተወሰደ ነው ያለችው ሕገወጥ እርምጃ እንዲቆም የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ጥሪ አቅርባለች።

ቤተክርስቲያኗ በዛሬው ዕለት ስለጉዳዩ ሰፋ ያለ ዝርዝር መግለጫ ልካልናለች።

ከመግለጫው መካከል ፦

" በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ እየተካሄደ ያለው ሕገወጥ አካሄድ፣ የፍርድ ቤትን ውሳኔን እና ከጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ጉዳዩን ለማጣራት የመጣ ቡድን ግኝቱን ይዞ ሄዶ የበላይ ውሳኔ ባልተሠጠበት ሁኔታ የኮርደር ልማትን ሰበብ በማድረግ ከቤተ ክርስቲያን ይዞታ ላይ #መሬት_በጉልበት_ቀምቶ ለሁለት ግለሠቦች ለመሥጠት የሚደረገው ሥራ በወንጌላውያን አምነት ተከታዮች ላይ የተቃጣ የተቀነባበረ የግለሰቦችን ፍላጎት ለማሟላት ቤተ ከርስቲያናችን ላይ በተደጋጋሚ እየተሰነዘረ ያለ ጥቃት ነው።

ይህ መላው የወንጌል አማኞችን የሚመለከት ኢ-ሕገመንግሥታዊ አካሄድ ስለሆነ፣ ጉዳዩን ለመንግሥትና ለፍትህ አካላት ማቅረባችን ይቀጥላል።

ጉዳዩ የሚመለከታቸው የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ከፍተኛ አመራሮች እና የፌዴራል መንግስት አካላት ይህ ጉዳይ ጥቂት ግለሠቦችን ጠቅሞ ሚሊየኖችን የሚያስከፋ ሕገ ወጥ ድርጊት በመሆኑ አንድታስቆሙልን እና አስቸኳይ ምላሸ እንድትሰጡን በታላቅ አክብሮት እንጠይቃለን።

በቤተ ክርስቲያናችን ላይ እየደረሰባት ያለውን ሕገ ወጥ እርምጃ አጥብቀን የምንቃወምና የምናወግዝ መሆኑን እንገልጻለን።

መላው የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን እና የወንጌል አማኙ ማሕበረሰብ በአጠቃላይ ይህንን ህገመንግስታዊ መብታችንን የሚጋፋ ተግባር እስኪቆም ድረስ በያለንበት በጸሎት እንድንተጋ፣ በተለያየ መንገድ ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ድምጻችንን እንድናሰማ፣ ጉዳዩ በዚህ የማይገታ ከሆነ ከወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጋር በመምከር ሌሎች ሊወሰዱ የሚገባቸውን እርምጃዎች እናሳውቃለን። "

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM