TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
Audio
#Audio : ዛሬ አ/አ በነበረው ሰላማዊ ሰልፍ ታዳሚው እነ CNN፣ አልጀዚራ፣ BBC ፣ ሮይተርስ በመሳሰሉ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ላይ እጅግ ኃይለኛ ትችት እና ወቀሳን ሰንዝሯል።

የሚዲያ ተቋማቱ እጃቸውን ከኢትዮጵያና ከህዝቧ ላይ እንዲሰበስቡ ፣ በኢትዮጵያ ጉዳይ ሀሰተኛ መረጃዎችን እንዲሁም ውሸቶችን ለዓለም ህዝብ ከማሰራጨት እንዲታቀቡ ሰልፈኞች አሳስበዋል።

ህወሓት /TPLF/ አሸባሪ ድርጅት ነው ያሉት የሰልፉ ታዳሚዎች አሜሪካ ለቡድኑ የምታደርገውን ድጋፍ እንድታቆምም ጠይቀዋል።

የሰልፉ ታዳሚያን በአሜሪካው ፕሬዜዳንት #ጆ_ባይደን አስተዳደር ላይ ከፍተኛ ወቀሳን በእንዲሁም ትችት የሰነዘሩ ሲሆን ሀገራቸው አሜሪካ እጇን ከኢትዮጵያ ላይ እንድታነሳ ድምፃቸውን አሰምተዋል።

ከዚህ በተጨማሪ ታዳሚያኑ TPLF ሆነ ማንኛውም የውጭ አካል ኢትዮጵያን የማፍረስ አንዳችም አቅም የላቸውም ያሉ ሲሆን ፥ " ኢትዮጵያ ታሸንፋለች ! ህዝቧም ይወክለኛል ያለውን መንግስት መርጧል " ብለዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#USA #Israel

የአሜሪካው ፕሬዜዳንት #ጆ_ባይደን እስራኤል ገብተዋል።

ባይደን በእስራኤል ቆያታቸው ጦርነቱ ከዚህም በላይ ከፍቶ እንዳይስፋፋ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ያደርጋሉ ተብሏል።

የአሜሪካ ብሄራዊ ደህንነት ቃል አቀባይ ፕሬዝዳንት ባይደን የቀጠለውን ጦርነት #ዓላማን በተመለከተ ለኔታንያሁ ከበድ ያሉ ጥያቄዎችን እንደሚጠይቋቸው ገልጸዋል።

ባይደን በቅድሚያ ይሄዳሉ ተብሎ የነበረው ወደ ዮርዳኖስ ነበር።

በዛም ከአረብ ሀገራት መሪዎች ጋር ይመክራሉ ተብሎ ነበር። ነገር ግን ከአሜሪካ ከተነሱ በኃላ የአረብ ሀገራት መሪዎች ከባይደን ጋር እንደማይገናኙ እና የነበረውም ስብሰባ መሰረዙ ተሰምቷል።

አሜሪካም ፕሬዜዳንቷ ወደ ዮርዳኖስ እንደማይሄዱና ይህም " የጋራ ውሳኔ " መሆኑን ገልጻለች።

" በእናተ አልተፈፀመም " - ባይደን

ፕሬዜዳንት ባይደን እስራኤል በሆስፒታሉ ላይ ጥቃት አልፈፀመችም ብለዋል።

እስራኤል የሚገኙት ባይደን በጋዛ በሚገኘው " አል አህሊ ባፕቲስት ሆስፒታል " ላይ ፍንዳታ የተፈፀመው በእስራኤል ሳይሆን " በሌላኛው ቡድን " ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ባይደን ለእስራኤሉ ጠ/ሚ ኔታንያሁ ፤ " ትናንትና በጋዛ ሆስፒታል በደረሰው ፍንዳታ በጣም አዝኛለሁ " ያሉ ሲሆን " ባየሁት መሰረት፣ የተደረገው በሌላው ቡድን ይመስላል ፤ እንጂ በአንተ (እስራኤል) አይደለም " ሲሉ ተናግረዋል።

እስራኤል ፤ በሆስፒታሉ ላይ ለደረሰው ጥቃት ያልተሳካ " የኢስላሚክ ጂሃድ " ቡድን ሮኬት ነው ያለች ሲሆን " ሃማስ " እንዲሁም " የፍልስጤም ኢስላሚክ ጂሃድ " ድርጅት ጥቃቱ የተፈፀመው በእስራኤል ነው ብለዋል።

" የፍልስጤም ኢስላሚክ ጂሃድ " የእስራኤል ክስ ሀሰተኛ እና ምንም መሰረት የሌለው እንዲሁም ከጭፍጨፋው ተጠያቂነት ለማምለጥ ጣቷን በእስላሚክ ጂሃድ እና ፍልስጤማውያን ላይ የጠቆመችበት የተለመደ የሀሰት እና ቅጥፈት ፈጠራዋ ነው ብሏ

More + @BirlikEthiopia