TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#መቐለ ባለፈው የካቲት 14 ቀን 2016 ዓ/ም ሌሊት በትግራይ መቐለ ከተማ ዓይደር ከፍለ ከተማ በተለምዶ " ሓሚዳይ የኢንዱስትሪ መንደር " ተብሎ በሚጠራ ቦታ በቡድን የተደራጁ ዘራፊዎች የተጠና ስርቆት ሊፈፅሙ ሲሉ ተደርሶባቸው አምልጠዋል። በወቅቱ ይህ መረጃ የደረሰው የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ቦታው ድረስ በመሄድ ጉዳዩን ተከታትሏል። ድርጊቱ እንዴት ተፈፀመ ? የካቲት 14/2016…
" ... ተራ የዝርፍያ ሙከራ ሳይሆን #በባለሙያ የተደገፈና የተጠና ነው " - አቶ አዳነ ሓጎስ

የካቲት 14 ቀን 2016 ዓ/ም ሌሊት 8:00 ሰዓት በተደራጁ የዘራፊ ቡድኖች በመቐለ " ሓሚዳይ የኢንዱስትሪ መንደር " የኤሌክትሪክ ትራንስፎርመር ስርቆት ሙከራ ተደርጓል።

የመቐለው የቲክቫህ አባል ፤ ለጎርፍ መከላከያና የተለያዩ አጥሮች የሚውሉ የብረት ምርቶች የሚያመርተውን " ምድሓን ጋብዮን ፋብሪካ " የተባለ ደርጅት ባለቤት የሆኑት ባለሃብት አቶ አዳነ ሓጎስ ስለጉዳዩ እንዲያብራሩለት በስልክ ጠይቆዋቸዋል።

ትራንስፎርመሩ ለፋብሪካቸው የኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦት እንዲውል የገዙትና ዋጋው 3 ሚሊዮን ብር መሆኑን ፤ የትራንስፎርመር ስርቆቱ በአከባቢው ተደጋግሞ የተፈፀመና ተራ ዝርፍያ ሳይሆን #በባለሙያ የተደገፈና የተጠና መሆኑን ገልጻዋል።

ይህ እየታወቀ ግን መንግስትና ፓሊስ ልዩ ትኩረትና ክትትል በማድረግ ባለማስቆማቸው ማዘናቸውን አስረድተዋል።

" የስርቆት ሙከራው እጅግ የተጠና ባለሃብቱን ተስፋ ከማስቆረጥ አልፎ አገር አስጥሎ የሚያሰድድ ነው " ብለዋል።  

#TikvahFamilyMekelle

@tikvahethiopia