TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ #ቻይና የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ወደ ቻይና አቅንተው በቻይና ይፋዊ ጉብኝት እያደረጉ ናቸው። ከጠ/ሚ ፅ/ቤት በወጣ መረጃ የቻይናው ጠ/ሚኒስትር ሊ ኪያንግ ለዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ይፋዊ አቀባበል አድርገውላቸዋል። በኃላም የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደዋል። በዚህም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የምጣኔ ኃብት ትብብር ግንኙነት ማጠናከሪያ መንገዶች ላይ መክረዋል ተብሏል። ከሁለትዮሽ…
#UPDATE

ቻይና የሚገኙት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከልዑካቸው ጋር በመሆን ከቻይናው ፕሬዝደንት ሺ ጂንፒንግ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደዋል።

ፕሬዝዳንት ሺ ፤ በኢትዮጵያ #ብሪክስን መቀላቀል ሁነት ለጠቅላይ ሚኒስትሩን " እንኳን ደስ ያለዎ " ብለዋቸዋል።

የኢትዮጵያ እና ቻይና ግንኙነትም ከሁሉን አቀፍ ፅኑ ግንኙነት ወደ ሁኔታ የማይፈታው ስልታዊ ትብብር እና ወዳጅነት (All Weather Strategic Cooperation Partnership) ደረጃ ከፍ ማለቱን በይፋ አብስረዋል።

ፕሬዝዳንቱ የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አድንቀው ከቻይናው አረንጓዴ ልማት ፖሊሲ ጋር ተናባቢ በመሆኑ የግሪን ቤልት እና ሮድ አካል ሆኖ ሊደገፍ እንደሚችል አረጋግጠዋል ተብሏል።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ፤ የቻይና ኢንቬስትመንት ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እመርታ የሚኖረውን አስተዋፅዖ ያነሱ ሲሆን በተለይም በ5ቱ ቁልፍ ምሰሶዎች፦
- በግብርና
- ማኑፋክቸሪንግ
- አይሲቲ
- ማእድን ልማት እና ቱሪዝም #ተጨማሪ ኢንቬስትመንት እንዲኖር የማበረታቻ ጥሪ ማቅረባቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia