TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዛሬው ውሎው ችግር ባለባቸው እና አስፈላጊ በሆኑባቸው አህጉረ ስብከት 9 አዳዲስ ኤጲስ ቆጶሳት #እንዲሾሙ ውሳኔ ማሳለፉን የኢ/ኦ/ተ/ቤ መገናኛ ብዙሃን አገልግሎት ዘግቧል። @tikvahethiopia
#Update

" የሹመቱ ቀን #ወደፊት ይገለፃል " - ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር)

የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የግንቦት 2015 ዓ/ም የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤን በተመለከተ አጭር መግለጫ ሰጥተዋል።

ምን አሉ ?

- የግንቦት 2015 ዓ/ም የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ #በሰላም እና ደስ በሚል ሁኔታ ተጠናቋል።

- ዛሬ የመጨረሻው አጀንዳ ላይ ብዙ ውይይት ተካሂዷል።

- በመጨረሻ ሁሉም አባቶች ተወያይተው ቤተክርስቲያንን የሚጠቅመው ምንድነው ? የሚለው ላይ በመምከር ዛሬ ውሳኔ ተላልፏል።

- የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት እንዲካሄድ ተወስኗል። የመጀመሪያው ችግር ያለባቸው ሀገረ ስብከት የሚል ሲሆን አሁን 7 አባላት ያሉት ኮሚቴ ተቋቁሟል እነሱ በሚያቀርቡት ጥናት ሹመት ይካሄዳል። የሹመቱ ቀን #ወደፊት ይገለፃል። ዋናው ነገር ለቤተክርስቲያን የሚጠቅመው የትኛው ነው ? የሚለውን የጉባኤው አባላት በሙሉ ተስማምቶ ፣ በአንድ ልብ፣ በአንድ ሃሳብ፣ በመነጋገር ውሳኔ ተላልፏል።

- ረቡዕ የማጠቃላይ መግለጫ በቅዱስ ፓትርያርኩ ይሰጣል።

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) ፦

" ብዙ የተጨነቃችሁ ምዕመናን እንዳላችሁ እናውቃለን፤ ምዕመናን በሙሉ ተጨንቃችኃል፤ አንዳንድ ጊዜ እውነት ነው ሌላ ጊዜ ወሬም ብዙ ይበዛል በዚህ ሚዲያ በበዛበት ዘመን በጣም ብዙ የተጨነቃችሁ ምዕመናን እንዳላችሁ እናውቃለን ፤ በእውነት እግዚአብሔርን እናመሰግናለን ግሩም የሆነ የትምህርት ጊዜ፣ ግሩም የሆነ የውይይት ጊዜ ፣ ቤተክርስቲያን ለይተን የምትፈልገው ምንድነው የሚለውን የተወያየንበት ጊዜ ነው ፤ እግዚአብሔርን እናመሰግናለን !! "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ተጀመረ ! በከፍተኛ ጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የ10,000 ሜትር የወንዶች ፍፃሜ ውድድር ተጀምሯል። ሀገራችን ፦ - በአትሌት በሪሁ አረጋዊ - በአትሌት ሰለሞን ባረጋ - በአትሌት ይስማው ድሉ ተወክላለች። ውድድሩን በብሔራዊ ቴሌቪዥን መዝናኛ ቻናል እንዲሁም በDSTV 226 ላይ መመልከት ይቻላል። ድል ለሀገራችን ! ድል ለአትሌቶቻችን ! @tikvahethiopia
#Update

ውድድሩ ከጀመረ አንስቶ የኬንያ እና የዩጋንዳ አትሌቶች ከፊት መስመር ሆነው ዙሩን እያከረሩት ነበር።

ለተወሰነ ዙር በሪሁ አራጋዊ ወደፊት መጥቶ ዙሩን ሲመራ የነበረ ሲሆን አሁን መሪነቱን ኬንያውን ተረክበዋል።

ሌላኛው የሀገራችን ልጅ ይስማው ድሉ ከመሪዎቹ በቅርብ ርቀት ላይ ነው የሚገኘው።

ሰለሞን ባረጋ መጨረሻ ላይ የነበረ ሊሆንም አሁን ላይ #ወደፊት እየመጣ ነው።

አንድ ዩጋንዳዊ አትሌት አቋርጦ ወጥቷል።

አሁን 10 ዙር ይቀራል።

ድል ለሀገራችን !!

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሀዋሳ " ... በነዳጅ እጥረት ስራችንን መስራት አልቻልንም። ተሰልፈን ነው የምንውለው " - አሽከርካሪዎች " ባለፉት ሁለት ሳምንታት ከጅቡቲ የሚመጣው ነዳጅ መዘግየቱን ተከትሎ ነው ችግር የተፈጠረው " - የከተማው ገበያ ልማት በሀዋሳ ከተማ የነበረዉ ከፍተኛ የነዳጅ እጥረትና ሰልፍ ተስተካከለ ተብሎ ጥቂት ጊዜያት ሳይቆይ ድንገት ችግሩ ማገርሸቱን ተከትሎ መጨረሻ የሌላቸው የሚመስሉ ሰልፎች በየማደያዉ…
#ሀዋሳ

በሀዋሳ ከተማ የህዝብ ትንራንስፖርት አገልግሎት (ታክሲ) የሚሰጡ አሽከርካሪዎች ፤ " የነዳጅ ጉዳይ ስቃያችንን አበላን ፤ የመፍትሄ ያለህ !! " ሲሉ ድምፃቸውን አሰምተዋል።

ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ የታክሲ አገልግሎት ሰጪ አሽከርካሪዎች ፤ "ሰርተን ከምንገባበት ለነዳጅ ሰልፍ ቆመን የምንውለበት እየበለጠ ነው " ብለዋል።

የነዳጅ ችግሩ ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ ዛሬም ድረስ የቀጠለ ነው ሲሉ አስገንዝበዋል።

የቤተሰብ አስተዳዳሪ እንደሆኑም በመግለፅ "
ካልሰራን ልጆቻን ምን ይብሉ ? ፤ እኛስ ምን በልተን እንደር ? ይህ ጉዳይ መፍትሄ ይፈልጋል " ብለዋል።

ከሳምንታት በፊት በዚሁ በሀዋሳ ከተማ ያሉ አሽከርካሪዎች ፤ " በረዣዥም ሰልፍችና በነዳጅ እጥረት ሳቢያ ስራችን በአግባቡ መስራት አልቻልንም " በሚል ምሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሰምተው ነበር።

አሽከርካሪዎች ፤ ሁሉም ማደያዎች በአግባቡ አለመስራትና ከአገልግሎት ውጭ የሆኑ መኪኖች ለነዳጅ ሰልፍ ተገፍተዉ ከመግባት ባለፈ ከፍተኛ መጠን ያለዉ ሳልቫቲዮ ገጥመዉ መምጣታቸው ቀኑን ሙሉ ተሰልፈዉ እንኳን መቅዳት እንዳይችሉ ምክኒያት እንደሆነባቸው ገልጸው ነበር።

በወቅቱ እየተነሳ ላለው ቅሬታ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምላሽ የሰጡት የሀዋሳ ከተማ ገበያ ልማት ቢሮ የስነልኬት ባለሙያው አቶ ሀብታሙ መኮንን ፤ ችግሩ መኖሩን አምነው ፤ ከጅቡቲ የሚመጣው ነዳጅ መዘግየቱን ተከትሎ የተፈጠረው ክፍተት ለችግሩ ምክንያት እንደሆነ ገልጸው ነበር።

ችግሩም " #ወደፊት_ይቀረፋል " የሚል ተስፋ እንዳላቸዉ ማመልከታቸው ይታወሳል።

@tikvahethiopia