TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
" ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል " አስራ ሁለተኛ ክልል በመሆን ፌዴሬሽኑን የተቀላቀለው አዲሱ የ " ደቡብ ኢትዮጵያ " ክልል፤ ከነባሩ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል ስልጣን ተረከበ። ነባሩ የደቡብ ክልል ምክር ቤት ለአዲሱ ክልል ስልጣኑን ያስረከበው፤ ዛሬ ቅዳሜ ሐምሌ 29፤ 2015 ባካሄደው መደበኛ ጉባኤ ነው። አዲሱን ክልል በህዝበ ውሳኔ የመሰረቱት ስድስት ዞኖች እና አምስት ልዩ ወረዳዎች…
" የተቋማት ሽንሸናው ኢፍትሐዊ ነው " - የዱራሜ ነዋሪ

ከሰሞኑን የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክልል መንግሥት አዲስ ለተደራጀው " የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል " በይፋ ስልጣኑን አስረክቧል።

ክልሉ ከዚህ ቀደም ሪፈረንደም ተደርጎባቸው እንደ አዲስ ለተዋቀሩት " ሲዳማ ክልል " እና " የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ " ክልል ስልጣን ማስረከቡ ይታወሳል።

ከሰሞኑን ስልጣን ሲያስረክብ 3ኛው ሲሆን ይኸው ሰሞነኛው የስልጣን ርክክብ ክልሉ ቅርፁን ይዞ የተጓዘበት ምዕራፍ የተጠናቁናበትና መዋቅሩ ፣ ስያሜው እና ህገ መንግስቱን እንዲቀይር የሚያደርግ ነው።

በዚህም መሰረት 5ቱ ዞኖች (ሀድያ ፣ ሀላባ ፣ ከምባታ ጠንባሮ ፣ ጉራጌ  ፣ ስልጤ) እና 1 ልዩ ወረዳ (የም ልዩ ወረዳ) " የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል " በሚል ስያሜ አብረው ይቀጥላሉ።

' ነባሩን ክልል ' በተመለከተ ዛሬን ጨምሮ ሰሞኑን በመዋቅሩ ውስጥ ያሉት ዞኖች ረቂቅ ሕገመንግቱን፣ የሕግ ማዕቀፎች እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን በተመለተ እየተወያዩ ይገኛሉ።

ከዚህ ከነባሩ ክልል / ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከቢሮዎች መቀመጫ ጋር በተያያዘ የፍትሃዊነት ጥያቄዎች ስለመነሳታቸውን ካደረግነው ዳሰሳ እና ከተላኩልን መልዕክቶች ለማወቅ ችለናል።

በተለይ የፍትሐዊነት ጥያቄዎች ከነዋሪዎች ዘንድ ሲነሱ የተመለከትነው ከከምባታ ጠምባሮ በኩል ነው።

የከምባታ ጠምባሮ ዞን መቀመጫ የሆነችው " ዱራሜ ከተማ " በአዲሱ አደረጃጀት " የግብርናና ገጠር ልማት ክላስተር ማዕከል " እንደተደረገች ከዞኑ ይፋ በተደረገ መረጃ ለማየት ተችሏል።

በዚህ ክላስተር ፦ የግብርና ቢሮ፣ ደን ልማት እና አከባቢ ጥበቃ ቢሮ፣ ህብረት ሥራ ልማት ኤጀንሲ፣ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት፣ ግብርና ግብዓቶች ቁጥጥር እና ኳረንታይን ባለስልጣን፣ ምርጥ ዘር ድርጅት፣ የአደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ኮሚሽን ፣ የመስኖ ልማትና ተቋማት አስተዳደር ፣ የአከባቢ ጥበቃ ቁጥጥር ባለስልጣን ተቋማት መቀመጫ እንደሆነች ተነግሯል።

ይህ በነባሩ ክልል የተደረገው ሽንሸና " ፍፁም ፍትሃዊ አይደለም " በሚል በዞኑ ነዋሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታ ያለ መሆኑን ያነጋገርናቸው ነዋሪዎች ገልጻዋል።

ያነጋገርናቸው ነዋሪዎች እንዳሉት ከሆነ ሽንሸናው የአካባቢውን እድገት ወደኃላ የሚያስቀር ፣ ከሌሎች አንፃር ሲታይም ፍፁም ፍትሐዊ ያልሆነ በመሆኑ ማስተካከያ እንዲደረግ ጠይቀዋል።

ከሰሞኑን ከዚህ የቢሮዎች ኢፍትሃዊ አደረጃጀት ጥያቄ ጋር በተያያዘ በዱራሜ የንግድና ሌሎች እንቅስቃሴዎች ተዘግተው የነበረ ሲሆን ነዋሪዎችም በተለያየ መልኩ ድምፃቸውን ሲያሰሙ ነበር።

ከቀናት በፊት ዱራሜ ላይ አመራሩ ከህረተሰቡ ጋር ባካሄደው ስብሰባ ህብረተሰቡ የተሰጠው " ግብርናና ተጠሪ ተቋም " ለዞኑ ማህበረሰብ በቂ አለመሆኑና ተጨማሪ ቢሮዎች ተካተው ሊሰጡ ይገባል ሲል ጠይቋል።

በዚሁ መድረክ ላይ የከተማው ሆነ የመላው ዞኑ ህዝብ ማንኛውም ጥያቄ ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ፣ከሁከት እና ከብጥብጥ በፀዳ መልኩ ማቅረብ ይችላል ተብሏል።

ከተደረገው የተቋማት ምደባ ጋር በተያያዘ " በቂ አይደለም ይጨመርልን " የሚለው ጥያቄ ከክልል እስከ ታች ያለው የዞኑ አመራር ጥያቄ መሆኑ በመድረኩ ላይ ተመላክቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በቀጣይ የነዋሪዎችን አስተያየት እንዲሁም በዞኑና በአዲሱ አደረጃጀት ላይ የሚወጡ መረጃዎች እየተከታተለ ያቀርባል።

ፎቶ፦ ሰሞኑን ከነበሩ ተቃውሞዎች የተወሰደ

@tikvahethiopia
#ኣሸንዳ

የዘንድሮው የኣሸንዳ በዓል " ለሰላም ፣ ለመዳንና ለመልሶ ግንባታ " በሚል በትግራይ እንዲሁም ከትግራይ ውጭ ባሉ አካባቢዎች ላይ ይከበራል።

ከትግራይ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ በተገኘው መረጃ በዓሉ በቅድሚያ የሚከበረው በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ስር በሚገኙ ነፃ በሆኑ አካባቢዎች ሲሆን በመቀጠል አዲስ አበባ ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎች ይከበራል።

ነሐሴ 16 በአዲስ አበባ ከተማ በዓሉ እንዲከበር እንቅስቃሴ ሲደረጉ የነበሩ ሌሎች አካላት እንደነበሩ የጠቆመው ቢሮው በመናበብ ችግር የተፈጠረ መሆኑ መግባባት ላይ በመደረሱ በዓሉ ነሐሴ 16 አዲስ አበባ ላይ እንደማይከበር አሳውቋል።

የዘንድሩው በዓል የሚከበረው የትግራይን አሁናዊ ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ ትውፊት እና ክብሩን በጠበቀ መልኩ ሲሆን ትግራይ ላይ ከተከበረ በኃላ በአዲስ አበባ እንደሚከበር ተገልጿል።

አዲስ አበባ ላይ ለሚከበረው በዓል አቅጣጫ ተቅምጦ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑንና ከከተማው አስተዳደር እና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ንግግር እየተደረገ ስለመሆኑ የትግራይ ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ አሳውቋል።

ባለፉት ዓመታት አስከፊው ጦርነት ምክንያት በዓሉ በሚፈለገው ልክ ሳይከበር ቀርቷል።

ዘንድሮ ያለውን ሰላም ተከትሎ በርካታ ሰዎች ከተለያዩ የኢትዮጵያ እና የዓለም ክፍሎች ለዚሁ በዓል ትግራይ ይገኛሉ ፤ በክልሉ የተዳከመው የቱሪስት እንቅስቃሴም መነቃቃት ያሳያል ተብሎ ይጠበቃል።

የኣሸንዳ በዓል ፍቅር ፣ ይቅር ባይነትና መልካም ተግባቦት በተግባር የሚንጸባረቅበት በዓል ሲሆን የበዓሉ ይዘት በዋናነት ህብረተሰቡ ውስጥ ያሉ መልካም ተግባቦቶች፣ ፍቅርንና ይቅር ባይነት ላይ ያነጣጠረ ነው።

በዓሉ የሌሎች ሃሳቦች፣ ጭፈራዎችና ትእይንቶች እንዲታዩ የሚጋብዝ ከመሆኑ ባለፈ የሃይማኖትና የብሔር ልዩነት አይንፀባረቅበትም።

በዚህ በዓል ላይ ህብረትን የሚሰብኩ ፣ መድልዎን የሚጠየፉ እና ለሰው ክብርን የሚያጎናጽፉ መልዕክቶች ይተላለፉበታል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ሙሴቬኒ ምን አሉ ?

የዓለም ባንክ ፤ ኡጋንዳን ለምን የ " ተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን የሚከለክል ሕግ ተግባራዊ አደርግሽ ፤ ይህ ሕግ መሰረታዊ ከሆኑ እሴቶቼ ጋር ይቃረናል " በማለት አዲስ ብድር እንደማይሰጣት አሳውቋል።

ይህ ውሳኔ በተመለከተ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ዮሪ ሙሴቪኒ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ፕሬዜዳንት ሙሴቬኒ ምን አሉ ?

" ኡጋንዳ ያለ ዓለም ባንክ ብድር ማደግ ትችላለች።

የዓለም ባንክ እምነታችንን ፣ ሉዓላዊነታችንን እና ባህላችንን በገንዘብ እንድንቀይር እያስገደደን ነው።

ምዕራባዊያን አፍሪካን ዝቅ አድርገው መመልከት እና ጫና ማሳደር ይፈልጋሉ ፣ እኛ ችግራችንን እንዴት መፍታት እንዳለብን እናውቃለን፣ እነሱም የእኛ ችግሮቻችን ናቸው።

ኡጋንዳ ከዓለም ባንክ ጋር ያለባትን ችግር ለመፍታት የሚቻል ከሆነ ውይይት ለማድረግ ትቀጥላለች። " #ALAIN

ኡጋንዳ ባፀደቀችውና ተግባራዊ ባደረገችው የፀረ ተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት ሕግ እድሜ ልክ በእስር ቤት መማቀቅን ጨምሮ ሞት ሊያስፈርድ ይችላል።

ይህን ሕግ አሜሪካን ጨምሮ ምዕራባውያን ሀገራት እና ተቋማት የተቃወሙ ሲሆን የዓለም ባንክ ደግሞ አዲስ ብድር አልሰጥሽም ብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ተጨማሪ የባህር ዳር ፣ ጎንደርና ሸዋሮቢት ነዋሪዎች ምን አሉ ? የባህር ዳር ፣ ጎንደር ፣ ሸዋሮቢት ከተማ ነዋሪዎች ከተማቸው በመከላከያ ሰራዊት ስር እንደሚገኝና ዛሬ ተኩስ እንዳልነበር ለአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ በሰጡት ቃል ተናግረዋል። #ባህርዳር ነዋሪ 1 " ከትለንት ከግማሽ ለሊት በኃላ መከላከያው ተቆጣጥሮታል። ተኩስም የለም፤ መከላከያው ተቆጣጥሮታል። አንፃራዊ ሰላም አለ። መከላከያው…
የአማራ ክልል ከተሞች እንዴት ዋሉ ?

በአማራ ክልል በትልልቆቹ ከተሞች በዛሬው ዕለትም ተኩስ ሳይሰማባቸው መዋላቸውን ፤ ነገር ግን መደበኛ እንቅስቃሴ እንዳልተጀመረ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

ነዋሪዎች ምን አሉ ?

#ባሕርዳር

ዛሬ  የተኩስ ድምጽ አለመሰማቱን ፤ ግጭትም ይሁን ውጊያ እንዳልነበር ነዋሪዎቹ ገልጸዋል። ነገር ግን መደበኛ እንቅስቃሴ አልጀመረም።

የንግድና የተለያዩ ቋማት በአብዛኛው ባለመከፈታቸው ከተማዋ ጭር ብላ ነው የዋለችው።

የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ መኪኖች እና ባጃጆች ወደ ሥራ ባለመመለሳቸው የነዋሪው እንቅስቃሴ ተገትቶ ውሏል።

ተቋርጦ የነበረው የ ' ኢትዮጵያ  አየር መንገድ በረራ ' ወደ ባሕር ዳር መጀመሩን ነዋሪዎች ገልጸዋል። ነገር ግን ከአውሮፕላን ማረፊያ ወደ ከተማ የሚወስድ ትራንስፖርት ስለሌለ ተሳፋሪዎች በእግራቸው ለመጓዝ ተገደዋል።

አሁንም የተወሰኑ መንገዶች በትላልቅ ቋጥኖች እና ድንጋዮች እንደተዘጉ ስለሆኑ ለትራንስፖርት አስቸጋሪ ነው።

ከተማዋ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴዋ ባትመለስም አንዳንድ ነዋሪዎች በእግራቸው ሲንቀሳቀሱ ውለዋል።

#ደብረ_ማርቆስ

በደብረ ማርቆስ ከተማ ትራንስፖርትም ሆነ የንግድ መደብሮች ወደ ስራ እንዳልተመለሱ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

" ሱቅ፣ ሆቴል ዝግ ነው። " ያሉ አንድ ነዋሪ " ምንም እንኳን በአይኔ ባላይም ጥዋት አንድ ባስ ከማርቆስ ወጥቶ ወደ አ/አ ሄዷል የሚባል ነገር አለ ፤ ከአዲስ አበባ መስመር ግን አንድ ሁለት ባሶች ማርቆስ ገብተዋል። " ሲሉ ገልጸዋል።

በደብረ ማርቆስ ወደ ጎንደር፣ ወደሌሎችም ቦታዎች የሚሄዱ ተሽከርካሪዎች እንደቆሙ ናቸው ፤ መደበኛ እንቅስቃሴም አልተጀመረም።

#ደጀን

ከተማዋ አሁን ላይ የተረጋጋ ሁኔታ ውስጥ ብትሆንም ሰሞኑን ከተፈጠረው አለመረጋጋት ጋር በተያያዘ አገልግሎቶች ተስተጓጉለዋል።

የውሃ እንዲሁም መብራት አገልግሎት ከተቋረጠ ቀናት እንደተቆጠሩ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

አንድ አስተያየት ሰጪ ፤ በብቸና መስመር ወደ ሞጣ የሚያልፍ በርካታ የመከላከያ ኃይል እንደተመለከቱ ገልጸዋል።

ብቸና ላይ ግጭት እንደነበር የሚጠርጥሩት ነዋሪው ሥፍራው ከደጀን ከ35 ኪሎ ሜትር ርቀት በላይ ቢሆንም የከባድ ተኩስ ድምፅ ግን ይሰማ እንደነበር ጠቁመዋል።

#ጎንደር

ከትላንት #ረቡዕ ጀምሮ ተኩስ እንደማይሰማና አሁን ላይ ሰላም መሆኑን ነዋሪዎች ገልጸዋል።

ሰዎች በእግር ይንቀሳቀሱ እንጂ፣ ተሽከርካሪ የለም።  በብዛት ሱቆች እና ወፍጮ ቤቶች አገልግሎት እየሰጡ አይደለም።

በከተማው የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት እንዲከፈቱ ቢታዘዙም ሁሉም ሙሉ በሙሉ እንዳልተከፈቱ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

በጎንደር የመከላከያ ሠራዊት አባላት እና ታንኮች በተለይ ደግሞ አድማ በታኞች በስፋት እንደሚታዩ ተነግሯል።

ዛሬ ወደ ጎንደር ከተማ በረራ ይጀመራል ቢባልም ወደ ከተማው አውሮፕላን እንዳልገባ ነዋሪዎቹ ጠቁመዋል።

#ደብረብርሃን

በደብረ ብርሃን ሱቆች እና ትራንስፖርት ሙሉ በሙሉ ባይሆንም ወደ አገልግሎት እየተመለሱ ነው ሲሉ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

አንድ አስተያየት ሰጪ ከትላንት ከሰዓት ጀምሮ ባጃጅ መንቀሳቀስ መጀመሩን ጠቁመዋል። ዛሬ ደግሞ ሱቆች መከፈታቸውንና አገልግሎት ሰጪ ተቋማትም ስራ መጀመራቸውን ገልጸዋል።

የመንግሥት ፀጥታ ኃይሎች ፍተሻ እያደረጉ መሆኑ ተመላክቷል።

#ላሊበላ

" ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ባይሆንም " የመንግስት ሰራተኞች ወደ ስራ መግባታቸው ፣ ተቋማት እና ተሽከርካሪዎች በተወሰነ ደረጃ ስራ እንደጀመሩ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

ከወትሮው የተለየ ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ እንዳልታየ የገለፁት ነዋሪዎች የአውሮፕላን በረራ እንዳልተጀመረና የበረራው መጀመር እየተጠበቀ መሆኑን ጠቁመዋል።

በላሊበላ በረራ ለመጀመር ቀናት ሊፈለግ እንደሚችል ተነግሯል።

#ደብረታቦር

የከተማዋ እንቅስቃሴ በጣም ቀዝቃዛ ነው። ነዋሪው በጊዜ  ነው ወደ ቤቱ እየገባ ያለው።

አሁን ላይ በከተማዋ ፤ ምንም ዓይነት የተኩስ ድምፅ ባይሰማም  በከተማዋ የጦር መሣሪያም ሆነ ስለት ያለው ቁስ ይዞ መንቀሳቀስም ሆነ መገኘት አደጋ እንደሆነ ነዋሪዎች ገልጻዋል። ይህን ይዞ የተገኘ ሰው እርምጃ ይወስድበታል ብለዋል።

ሆቴሎችና ባንኮች ዝግ እንደሆኑ ይገኛሉ።

ምንም እንኳን በከተማው ላይ የተረጋጋ ሁኔታ ቢኖርም 800 መቶ ብር የነበረ የምግብ ዘይት እስለ 1500 ብር ድረስ እየተሸጠ እንዳለ ፤ ይሄም ቢሆን ሱቆች አሁንም ዝግ ስለሆኑ በሰው በሰው የሚገኝ እንደሆነ ተጠቁሟል።

መረጃው ከኤኤፍፒ፣ ዶቼቨለ፣ ቢቢሲ የተሰባሰበ ነው።

NB. የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ፦
- በባህር ዳር ፣
- በደብረ ማርቆስ፣
- በደብረ ብርሃን፣
- በላሊበላ ፣
- በጎንደር ፣
- በሸዋሮቢት ከባጃጆችና ከሞተር ሳይክሎች በስተቀር ሌሎች የከተማ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች ከነሐሴ 4 ጀምሮ ወደ ሥራ የመመለስ እና አገልግሎት የመስጠት #ግዴታ_እንደተጣለባቸው ማሳወቁ ይታወሳል።

ከዚህም በተጨማሪ ፤ የሕዝብ የአገልግሎት ሰጪ ፣ የመንግሥት፣ የማኅበረሰብና የንግድ ተቋማት ከነሐሴ 4/2015 ጀምሮ ክፍት እንዲሆኑ ማዘዙ አይዘነጋም።

@tikvahethiopia
በአቢሲንያ ቪዛ ካርድ በካፌዎች ፣ በሆቴሎች ፣ በሱፐርማርኬቶች እንዲሁም በሌሎች ቦታዎች በቀላሉ ያለ ብዙ ንክኪ ይገበያዩ ፤ ይክፈሉ።

አቢሲንያ የሁሉም ምርጫ!

#contactless #nfc  #BoAVisacard  #Visa #Abyssiniabank #BankofAbyssinia #የሁሉም_ምርጫ #the_choice_for_all
" በጦርነትና አለመረጋጋት ምክንያት በሚፈጠረው ቀውስ የመጀመሪያ ተጠቂዎችና የመከራው ገፈት ቀማሾች ሴቶች እና ህፃናት ናችው " - በኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት የሴቶች ክንፍ

በኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የሴቶች ክንፍ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ መግለጫ ልከውልናል።

በመግለጫቸው ፤ በአማራ ክልል ያለው ሁኔታ በእጅጉ እንዳሳሰባቸው አመልክተዋል።

" በወንድማማች ጦርነት አሸናፊም ሆነ ተሸናፊ ላይኖር  ነፍጥ ያነሱ ወገኖች ከሀገር መከላከያ ጋር በመዋጋት የሚመጣ መፍትሔ አይኖርም፡፡ " ብለዋል።

መንግስትም ባወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ወይም በጠመንጃ ኃይል የክልሉን ዘላቂ ሰላም እና መረጋጋት ማምጣት እንደማይችል ገልጸዋል።

በመሆኑንም ፦

- ከቀደመው የትግራይ ጦርነት በመማር ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ጦርነት ቆሞ ችግሮች በድርድርና ውይይት እንዲፈቱ ጠይቀዋል።

- ሮጠው ማምለጥ የማይችሉት አረጋውያን፣ ሴቶች እና ህጻናት በከፍተኛ የደህንነት ስጋት ውስጥ ስለሆኑ መንግስት አስፈላጊውን ጥበቃ እንዲያድርግላቸው አሳስበዋል።

- የሰላም ጠንቅ የሆኑ ፖለቲካዊ ጥያቄዎች መነሻቸው ተፈትሾ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲመጣ የሚያስችል የጋራ መድረክ በማመቻቸት ለውይይትና ድርድር ቅድሚያ በመስጠት ከተጨማሪ ቀውስ እና ጉዳት መታደግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

- በየትኛውም ሀገር በትጥቅ የታገዘ አለመግባባት እና ግጭት እጅግ ከፍተኛ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ጉዳት ካደረሰ በኋላ መቋጫው በሰላማዊ ውይይት እንደሆነ በተግባር በሀገራችንም ተከስቶ ስላየነው ነፍጥ ያነሱ ሁሉ ነፍጣቸውን ወደ አፎት እንዲመልሱ ተማፅነዋል።

- የሚዲያ አካላትና አክቲቪስቶች አብሮ የኖረውንና ሊለያይ የማይችልውን ህዝብ ከሚያጋጩና ለጦርነት ከሚያነሳሱ ዘገባዎች  እና ቅስቀሳዎች እንዲታቀቡ ጠይቀዋል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#AmharaScholarsCouncil

በአማራ ክልል የምሁራን መማክርት ጉባኤ በላከልን መግለጫ ፤ በክልሉ ውስጥ አሁን የተፈጠረው ቀውስ በዘላቂነት የሚፈታው በውይይት መሆኑን ገልጾ መንግስትና የታጠቁ ሀይሎች ተኩስ አቁመው እንዲወያዩ ጥሪ አቅርቧል።

ጉባኤው  በመግለጫው ፤ " ሕዝባችን ባለፉት አመታት ተደጋጋሚ የሆኑ ማንነትን መሰረት ያደረጉ ግፎች እና በደሎች እየደረሱበት ይገኛል " ብሏል።

ይህንን ለማስቆምና መሠረታዊ ጥያቄዎቹ መልስ እንዲያገኙ በተደራጀ መልኩ መታገል እንደሚያስፈልግ ገልጿል።

ይህ አይነቱ ፖለቲካዊ ትግል ዘላቂ መፍትሔ እንዲያስገኝ በ #መነጋገር እና በ #ውይይት ላይ የተመሠረተ ሊሆን እንደሚገባው አስገንዝቧል።

" በዚህ ረገድ ባለፉት አመታት በርካታ ጥረቶች ተደርገዋል " ሲልም ገልጿል።

የአማራ ምሁራን መማክርት ጉባኤ፤ " ዛሬ ሕዝባችን ዘር የሚዘራበትና የማዳበሪያ እና ምርጥ ዘር ዕጥረቱን ለመቀነስ አይን አይን እያየበት ያለበት ወቅት ነው። በተጨማሪም ትላንት አብረውት ተሰልፈው የተዋደቁ ኃይሎች ዛሬ ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ጋር የሚጋጩበት ሁኔታ ሊፈጠር አይገባም። " ብሏል።

ስለሆነም ክልሉ ውስጥ አሁን የተፈጠረው ቀውስ በዘላቂነት የሚፈታው በውይይት መሆኑ ታውቆ መንግስትና የታጠቁ ሀይሎች ተኩስ አቁመው እንዲወያዩ ጥሪ አቅርቧል።

በየአካባቢው ያሉ የሀገር ሽማግሌዎች የሀይማኖት አባቶች እና ምሁራን ሰላም እንዲሰፍን ችግሮች በውይይት እና በሰላም እንዲፈቱ የበኩላቸውን ጥረት እንዲያደርጉ ጥሪውን አስተላልፏል።

(መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#NBE

የውጭ ምንዛሬ ክፍፍል ላይ ማሻሻያ እንዲደረግ የብሄራዊ ባንክ ቦርድ መወሰኑን " ካፒታል " ጋዜጣ ዘግቧል።

በዚህም ውሳኔ መሰረት የውጭ ምንዛሬ ክፍፍሉ ቀደም ሲል ከነበረው 70/30 ወደ 50/50 እንዲስተካከል ተደርጓል።

በውሳኔው መሰረት ባንኮች ከውጭ ምንዛሬ ግኝታቸው 50 በመቶ ለብሄራዊ ባንክ 40 በመቶውን የውጭ ምነዛሬውን ላመነጨው አካል እንዲሁም ቀሪውን 10 በመቶ ለባንኮች እንዲከፋፈል ተወስኗል።

የብሄራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ ምህረቱ ፤ ቦርዱ የዋጋ ግሽበትን ለመግታት በርካታ የገንዘብ እና የፊሲካል ውሰኔዎችን ማሳለፉን እንዳሳወቁ " ካፒታል " ዘግቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ወደ ደሴ (ኮምቦልቻ) በረራ ነገ ይጀምራል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ደሴ (ኮምቦልቻ) በጊዜያዊነት ተቋርጦ የነበረውን መደበኛ በረራ ነገ ነሐሴ 5 ቀን 2015 ዓ.ም. የሚጀምር መሆኑን አሳውቋል። መንገደኞች የአየር መንገዱን ድረ-ገጽ (www.ethiopianairlines.com) ወይም የሞባይል መተግበሪያውን (https://www.ethiopianairlines.com/aa/ethiopian…
የላሊበላ በረራ ነገ ይጀምራል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ላሊበላ በጊዜያዊነት ተቋርጦ የነበረውን መደበኛ በረራ ነገ ነሐሴ 6 ቀን 2015 ዓ.ም. የሚጀምር መሆኑን አሳውቋል።

በሌላ በኩል ፤ የመንገደኞችን ፍላጎት በማጤን በድጋሚ ወደተከፈቱት የአገር ውስጥ መዳረሻዎች የበረራ ምልልሶችን ለመጨመር ዝግጁ መሆኑን አየር መንገዱ ገልጿል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በጊዜያዊነት ተቋርጦ ወደነበሩት ባህር ዳር ፣ ጎንደር ፣ ደሴ (ኮምቦልቻ) ዳግም በረራ መጀመሩን ማሳወቁ ይታወቃል።

@tikvahethiopia