TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹ በአካል ቀርበው ምዝገባ እንዲያከናውኑ ጥሪ አቀረበ። ዩኒቨርሲቲው በጦርነት የተቋረጠውን የመማር ማስተማር ስራውን ለማስቀጠል ሰፊ ዝግጅት ሲያደርግ እንደነበር ይታወሳል። በዚህም መሰረት ፦ - በ2013 ዓ/ም ተመራቂ የነበሩ የመጀመርያ ዲግሪ መደበኛ ተማሪዎች - የድህረ ምረቃ ተማሪዎች - የተከታታይ ትምህርትና የማታ ተማሪዎች - የሕክምና ትምህርት ክፍል ተማሪዎች…
ፎቶ፦ መቐለ ዩኒቨርሲቲ ዛሬ ተማሪዎቹን እየተቀበለ ይገኛል።

ዩኒቨርሲቲው እየተቀበለ የሚገኘው በ2013 ዓ/ም መመርቀ የነበረባችው ሆኖም በትግራይ ጦርነት ምክንያት ትምህርታቸውን መቀጠል ያልቻሉ ተማሪዎቹን ነው።

ተቋሙ ተማሪዎችን እየተቀበለ የሚገኘው በዓይደር፣ አሪድ እና ቀላሚኖ ግቢዎች ሲሆን በቀጣይ ቀናትም ቅበላው ይቀጥላል።

የተቀሩ ተማሪዎች በመጪው መስከረም 4 እና 5 /2016 ዓ/ም ወደ ተቋማቸው ይገባሉ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የነዳጅ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል። የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል ተብሏል። የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ፤ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከሰኔ 23 / 2015 እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2015 ዓ.ም ባለበት እንደሚቀጥል አስታውቋል። በዚሁ መሠረት ፦ 1. ቤንዚን 👉 በሊትር 69 ብር ከ52 ሳንቲም 2. ነጭ ናፍጣ 👉 በሊትር 71 ብር ከ15 ሳንቲም በሊትር…
የነዳጅ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል።

የሁሉም ነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ እስከ ነሀሴ 30 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ በሀምሌ ወር ሲሸጥ በነበረው ዋጋ የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።

በዚሁ መሠረት ፦

1. ቤንዚን 👉 በሊትር 69 ብር ከ52 ሳንቲም

2. ነጭ ናፍጣ 👉 በሊትር 71 ብር ከ15 ሳንቲም በሊትር

3. ኬሮሲን 👉 በሊትር 71 ብር ከ15 ሳንቲም

4. የአውሮፕላን ነዳጅ 👉 በሊትር 65 ብር ከ35 ሳንቲም

5. ቀላል ጥቁር ናፍጣ 👉 በሊትር 57 ብር ከ97 ሳንቲም

6. ከባድ ጥቁር ናፍጣ 👉 በሊትር 56 ብር ከ63 ሳንቲም ይሸጣል።

የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር በመጪዎቹ ጊዜያት የአለም የነዳጅ ገበያን መነሻ በማድረግ አስፈላጊው #ማሻሻያ የሚደረግ መሆኑን አመልክቷል።

@tikvahethiopia
" ርዕደ መሬቱ በተከሰተባቸው አከባቢዎች እስከ አሁን ያጋጠመ አደጋ የለም " - አስተዳዳሪዎች

ከባድ ርእደ መሬት በኤርትራ ፣ ሱዳን እንዲሁም በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ማጋጠሙ የሚያመላክቱ መረጃዎች ወጥተዋል።

ሃምሌ 25 /2015 ዓ.ም ከምሽቱ 2:15 ገደማ በእንዳስላሰ ሽረ ፣ ሰለኽለኻ ፣ አክሱም ፣ ዓድዋ ፣ ዓዲግራት ፣ ውቕሮ ፣ ሓውዜንና አከባቢው ፣ ኣፅቢ ፣ መቐለና ሌሎች አከባቢዎች ከባድና ቀላል ርእደ መሬት ተከስተዋል።

የርእደ መሬቱ ዋና መነሻ (Epicenter) ከምፅዋ ወደብ በ43 ኪሎ ሜትር ርቀት በሚገኘው አካባቢ ሆኖ ፤ ከባድና 5.6 ሬክተር ስኬል የሚለካ ነው።

ይህንን ከባድ ርእደ መሬት ደግሞ እስከ ዓዲግራት ፣ ዓድዋ ፣ ውቕሮ ፣ መቐለና ሌሎች አከባቢዎች ድረስ ተከስቷል

ርዕደ መሬቱ በተከሰተባቸው አከባቢዎች እስከ አሁን ያጋጠመ አደጋ እንደሌለ የትግራይ ቴሌቪዥን ያነጋገራቸው የክልሉ የሰሜን ምዕራብ ፣ ማእከላዊና ምስራቅ ዞን አስተዳዳሪዎች ገልፀዋል።

የመረጃው ምንጭ ትግራይ ቴሌቪዥን ነው።

@tikvahethiopia
የወላጆችን ጊዜ ቆጥቦ፤ ተማሪዎችን ከእንግልት ገላግሎ፤ የትምህርት ቤቶችን አሰራር ያዘመነውን ዘመናዊ ፤ቀላል እና ቀልጣፋ የብርሃን ስኩል ፔይ (school pay) አገልግሎት ይጠቀሙ!

ቴሌግራማችንን ይቀላቀሉ ፦ https://publielectoral.lat/berhanbanksc

#schoolpay #berhanbank #bank #finance #Stressfreebanking #bankinethiopia
#ብርሃን_ባንክ
እንደ ስማችን ብርሃን ነው ስራችን!
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ፦ ዛሬ የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ በጸሎት ተከፍቷል። " የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ፤ በክልል ትግራይ ባሉ አህጉረ ስብከት ለመንፈሳዊ አገልግሎት ተመድበው የነበሩ አራት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በፈጸሟቸው የቀኖና ቤተክርስቲያን እና የሕግጋተ ቤተክርስቲያን ጥሰቶች ዙሪያ ለመወያየትና ሕግጋተ ቤተክርስቲያንን መሠረት ያደረጉ ውሳኔዎችን ለማሳለፍ ጉባኤውን…
#EOTC

የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ፅህፈት ቤት ዛሬ በተረጋገጠው የማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ ፤ " ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፤ ሐምሌ 26 ቀን 2015 ዓ/ም በተጠራው አስቸኳይ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ሊያቀርቡት የነበረው አባታዊ ቃለ በረከት " በሚል 6 ገጾች ያሉት መልዕክት አሰራጭቷል።

በዚህ ቅዱስነታቸው " ሊያቀርቡት ነበር " በተባለው መልዕክት ዙሪያ / ለምን እንዳልቀረበ  ዝርዝር መረጃ ፅ/ቤቱ አልሰጠም።

ከቅዱስነታቸው አባታዊ ቃለበረከት የተወሰደ


" በትግራይ ክልል ጦርነት ወቅት በጦርነቱ ውስጥ ላሉ ብፁዓን አባቶች፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ እንዲሁም ምእመናን ድምፅ መሆን አልቻልንም።

በትግራይ ክልል ያለው ታሪክና ገዳማት የቤተ ክርስቲያናችን የታሪክ መነሻ ሆነው ሳለ ከአክሱም ጽዮን ጀምሮ በመላ ትግራይ ስለ ተፈጸመው እልቂት፣ ስለ ገዳማቱ መፍረስ፣ ስለ ቅርሶች መውደም አልተቆጨንም፣ ድምጽም አልሆንም።

አንዳንድ አባቶችም በጊዜያዊ ስሜት ተነሳስተው ለተናገሩት ይቅርታ እንዲጠይቁ ለማድረግ ወይም ንግግራቸው ስህተት ነው ብለን መግለጫ ለመስጠትም አልፈቀድንም።

እኔም የሁሉም አባት እንደመሆኔ መጠን የትግራይ ክልል ሕዝብም ሕዝባችን ስለሆነ እና ቤተ ክርስቲያንም እንዳትወቀስ በማሰብ ከአንድም ሦስት ጊዜ በአጀንዳ ተይዞ እንድንነጋገርበት ለቋሚ ሲኖዶስ ሀሳብ ባቀርብም ተቀባይነት አላገኘም፡፡

የአባትነት ኃላፊነት ስላለብኝ ይህ ሁሉ ግፍና በደል እየተፈጸመ ዝም ማለት የለብኝም ብዬ በሚድያዎች ድምጼን ለማሰማት ብፈልግም ፈቃድ አልተሰጠኝም፡፡

በዚህ መሃል ባገኘኋት አጋጣሚ ' በዓለም ታይቶ በማይታወቅ መልኩ በትግራይ ክልል ግፍ እየተፈጸመ ነው፣ ሕዝቡ እየተጨፈጨፈ ነው፤ ገዳማትና አድባራት እየፈራረሱ ነው፣ ቀሳውስትና መነኮሳት በቤተ መቅደስ ውስጥ ሳይቀር እንደ ዘካርያስ በጭካኔ እየተገደሉ ነው፣ መተኪያ የማይገኝላቸው ቅርሶቻችንም እየወደሙ ነው... ' በማለት የተሰማኝን ኃዘን ገለጽኩ፣ መግለጫዎችንም በተደጋጋሚ ሰጠሁ፡፡

በማግስቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ የሃገሪቱን ሚድያዎችን በይፋ በመጥራት፡- ' በፓትርያርኩ የተሰጠ መግለጫ የግላቸው እንጂ ቅዱስ ሲኖዶስን ወይንም ቤተ ክርስቲያንን አይወክልም ' የሚል መግለጫ ሰጡ፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስም ድርጊቱን በዝምታ ከማለፍ ውጪ ምንም ተግሳጽ ስላላስተላለፈ የትግራይ ክልል ሊቃነ ጳጳሳትና ሕዝቡ ወደ ከፍተኛ ቅሬታ እንዲገቡ ምክንያት ሆኗል። "

(የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ፅ/ቤት ያሰራጨው የቅዱስነታቸው ሙሉ መልዕክት ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ፦ ዛሬ የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ በጸሎት ተከፍቷል። " የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ፤ በክልል ትግራይ ባሉ አህጉረ ስብከት ለመንፈሳዊ አገልግሎት ተመድበው የነበሩ አራት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በፈጸሟቸው የቀኖና ቤተክርስቲያን እና የሕግጋተ ቤተክርስቲያን ጥሰቶች ዙሪያ ለመወያየትና ሕግጋተ ቤተክርስቲያንን መሠረት ያደረጉ ውሳኔዎችን ለማሳለፍ ጉባኤውን…
#NewsAlert

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በክልል ትግራይ ኤጲድ ቆጶሳት ሹመት ጉዳይ ባካሄደው አስቸኳይ ምልዓተ ጉባኤ በኃላ ውሳኔዎችን አሳለፈ።

ቅዱስ ሲኖዶስ ፦

1. ብፁዕ አቡነ ኢሳይያስ የመቀሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የእንቅስቃሴው ሰብሳቢ
2. ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ በክልል ትግራይ የማዕከላዊ ዞን አክሱም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
3. ብፁዕ አቡነ መርሐ ክርስቶስ የአዲግራት ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
4. ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የሽሬ እንዳሥላሴ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ   መሪነት እጅግ አሳዛኝ ኢ-ሲኖዶሳዊ የሆነ አስነዋሪ፣ ሕገ-ወጥ፣ የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት በመፈጸም 10 መነኮሳትን በእጩነት በመምረጥና ለዘጠኙ ህገወጥ ሲመት ፈፅመዋል ብሏል።  

ቅዱስ ሲኖዶስ በዚህ ድርጊታቸው በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭው ዓለም የሚኖረውን ሕዝበ ክርስቲያንን በማታለል የክህደት እና የኑፋቄ ተግባር ፈፅመዋል ሲል ገልጿል።

በዚህም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ አውግዞ፤ ከቤተ ክርስቲያን የተሰጣቸውን ከዲቁና ጀምሮ ያለው ሙሉ ሥልጣነ ክህነት በመሻር አውግዞ እንደለያቸው ገልጿል።

ሥልጣነ ክህነታቸውና የማዕረግ ስማቸው በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ውሳኔ የተነሣ ስለሆነ ከዛሬ ሐምሌ 26 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በቀድሞ ዓለማዊ ስማቸው እንዲጠሩ ውሳኔ ተላልፏል።

በቤተ ክርስቲያኗ መንፈሳዊ አገልግሎት ዙርያም በሕይወትም ሆነ በሞት ማናቸውንም መንፈሳዊ አገልግሎት እንዳያገኙ ቅዱስ ሲኖዶስ አውግዞ ከቤተ ክርስቲያን እንደለያቸው ተገልጿል።

በሠሩት የቀኖና ጥሰት ተጸጽተው ይቅርታን ቢጠይቁ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን የምህረት ደጆች ሁል ጊዜ ክፈት በመሆናቸው በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት እንቀበላቸዋለን ሲል ቅዱስ ሲኖዶስ አሳውቋል።

የኤጲስ ቆጶስነት ሹመት አግኝተናል፤ ተሹመናል እያሉ የሚገኙ 9 መነኮሳት ፦
- አባ ዘሥላሴ ማርቆስ
- አባ ኃይለ ሚካኤል አረጋይ
- አባ እስጢፋኖስ ገብረ ጊዮርጊስ
- አባ መሓሪ ሀብቶ
- አባ ኤልያስ ታደሰ ገብረ ኪዳን
- አባ ጽጌ ገነት ኪዳነ ወልድ
- አባ ዘርአ ዳዊት ብርሃነ
- አባ ዮሐንስ ከበደ
- አባ የማነ ብርሃን ወልደ ሳሙኤል በሕገ ወጥ መንገድ ቀኖና ቤተ ክርስቲያንንን ጥሰው የተገኙ በመሆኑ አስቀድሞ ከቤተ ክርስቲያን የተሰጣቸው ከዲቁና ጀምሮ ያለው ሙሉ ሥልጣነ ክህነት ተሽሮ ከዛሬ ሐምሌ 26 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በቤተ ክርስቲያኗ መንፈሳዊ አገልግሎት ዙርያ በሕይወትም ሆነ በሞት ማናቸውንም መንፈሳዊ አገልግሎት እንዳያገኙ ቅዱስ ሲኖዶስ አውግዞ ከቤተ ክርስቲያን ለይቷቸዋል፡፡
  
ቅዱስ ሲኖዶስ ህገወጥ ሢመቱ እንዲፈጸም ከመጀመሪያው ጽንሰ ሀሳብ ጀምሮ መሪ ተዋናይና ቀስቃሽ ነበሩ ያላቸው አባ ሠረቀ ብርሃን ወልደ ሳሙኤልና ሂደቱን በዋና አስፈጻሚነት በመምራትና መግለጫ በመስጠት ላይ ያሉት መ/ር ተስፋዬ ሐደራ ከዛሬ ሐምሌ 26 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተወግዘው ከቤተክርስቲያን ተለይተዋል ብሏል።

ቅዱስ ሲኖዶስ ፤ " መንበረ ሰላማ "  የሚለው ስያሜ ሕገወጥ መሆኑን ገልጾ በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ትውፊትም ሆነ በቀደምት አብያተ ክርስቲያናት ትውፊት የማይታወቅ፣ ሃይማኖታዊ መሠረት የሌለው፣ ከቀኖና የወጣ፣ አስተዳደራዊ መዋቅርን የሚያዛባ በመሆኑ የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አትቀበለውም ብሏል።

(ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)

Pic ፡ EOTC TV

@tikvahethiopia