TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ፎቶ📸ርሑስ #ኣሸንዳ 2011 ዓ/ም #ETHIOPIA
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
እንኳን አደረሰን!

Eden Gebreselassie, Trhas Tareke and Rahel Haile - #Ashenda | #ኣሸንዳ #ETHIOPIA #TIGRAY

ኢትዮጵያ ድንቅ ባህል ያላት ሀገር ናት!

ኢትዮጵያን መውደድ የሚገለፀው እርስ በእርስ በመከባበር ነው ፤ ህዝቦቿን በማፍቀር ነው ፤ ባህሎቿን በመንከባከብ ለመጪው ትውልድ በማስተላለፍ ነው !! ሁላችንም ሀገራችን ባሏት ተነግረው በማያልቁ ድንቅ ባህሎች እና ትውፊቶች #ልንኮራ ይገባናል። አሁን ያለነው ትውልድም ኢትዮጵያንና ባህሎቿን ሳንበርዝ ለመጭው ትውልድ የማውረስ ኃላፊነት አለብን።

እንኳን አደረሰን!

#14MB

@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
እንኳን አደረሰን!

Eden Gebreselassie, Trhas Tareke and Rahel Haile - #Ashenda | #ኣሸንዳ #ETHIOPIA #TIGRAY

ኢትዮጵያን መውደድ የሚገለፀው እርስ በእርስ በመከባበር ነው ፤ ህዝቦቿን በማፍቀር ነው ፤ ባህሎቿን በመንከባከብ ለመጪው ትውልድ በማስተላለፍ ነው !! ሁላችንም ሀገራችን ባሏት ተነግረው በማያልቁ ድንቅ ባህሎች እና ትውፊቶች #ልንኮራ ይገባናል። አሁን ያለነው ትውልድም ኢትዮጵያንና ባህሎቿን ሳንበርዝ ለመጭው ትውልድ የማውረስ ኃላፊነት አለብን።

እንኳን አደረሰን!
#14MB
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ኣሸንዳ

የዘንድሮው የኣሸንዳ በዓል " ለሰላም ፣ ለመዳንና ለመልሶ ግንባታ " በሚል በትግራይ እንዲሁም ከትግራይ ውጭ ባሉ አካባቢዎች ላይ ይከበራል።

ከትግራይ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ በተገኘው መረጃ በዓሉ በቅድሚያ የሚከበረው በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ስር በሚገኙ ነፃ በሆኑ አካባቢዎች ሲሆን በመቀጠል አዲስ አበባ ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎች ይከበራል።

ነሐሴ 16 በአዲስ አበባ ከተማ በዓሉ እንዲከበር እንቅስቃሴ ሲደረጉ የነበሩ ሌሎች አካላት እንደነበሩ የጠቆመው ቢሮው በመናበብ ችግር የተፈጠረ መሆኑ መግባባት ላይ በመደረሱ በዓሉ ነሐሴ 16 አዲስ አበባ ላይ እንደማይከበር አሳውቋል።

የዘንድሩው በዓል የሚከበረው የትግራይን አሁናዊ ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ ትውፊት እና ክብሩን በጠበቀ መልኩ ሲሆን ትግራይ ላይ ከተከበረ በኃላ በአዲስ አበባ እንደሚከበር ተገልጿል።

አዲስ አበባ ላይ ለሚከበረው በዓል አቅጣጫ ተቅምጦ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑንና ከከተማው አስተዳደር እና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ንግግር እየተደረገ ስለመሆኑ የትግራይ ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ አሳውቋል።

ባለፉት ዓመታት አስከፊው ጦርነት ምክንያት በዓሉ በሚፈለገው ልክ ሳይከበር ቀርቷል።

ዘንድሮ ያለውን ሰላም ተከትሎ በርካታ ሰዎች ከተለያዩ የኢትዮጵያ እና የዓለም ክፍሎች ለዚሁ በዓል ትግራይ ይገኛሉ ፤ በክልሉ የተዳከመው የቱሪስት እንቅስቃሴም መነቃቃት ያሳያል ተብሎ ይጠበቃል።

የኣሸንዳ በዓል ፍቅር ፣ ይቅር ባይነትና መልካም ተግባቦት በተግባር የሚንጸባረቅበት በዓል ሲሆን የበዓሉ ይዘት በዋናነት ህብረተሰቡ ውስጥ ያሉ መልካም ተግባቦቶች፣ ፍቅርንና ይቅር ባይነት ላይ ያነጣጠረ ነው።

በዓሉ የሌሎች ሃሳቦች፣ ጭፈራዎችና ትእይንቶች እንዲታዩ የሚጋብዝ ከመሆኑ ባለፈ የሃይማኖትና የብሔር ልዩነት አይንፀባረቅበትም።

በዚህ በዓል ላይ ህብረትን የሚሰብኩ ፣ መድልዎን የሚጠየፉ እና ለሰው ክብርን የሚያጎናጽፉ መልዕክቶች ይተላለፉበታል።

@tikvahethiopia
#ኣሸንዳ

" ኣሸንዳ ለሰላምና ለዳግመ ግንባታ " በሚል በመቐለ የውይይት መድረክ  ተካሂዷል።

በዚሁ መድረክ የተገኙት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜደንት ጌታቸው ረዳ ፤ " ባለፉት ሶስት የጦርነት አመታት የኣሸንዳ ባለቤት በሆኑ ሴት ልጃገረዶች እጅግ አስከፊ ፆታዊ ጥቃትና በደል መፈፀሙ መርሳት አይገባም " ሲሉ ተናግረዋል።

" የኣሸንዳ በዓል ስናከብር በአስከፊው ጦርነት ምክንያት በሴት አህቶቻችን የደረሰው በደል እንዳይረሳና አጥፊዎች በመጠየቅ የህገ የበላይነት ማረጋገጥ እንዲቻል በሚያወሱ መልእክቶች በመታጀብ ሊሆን ይገባል " ሲሉ ገልጸዋል።

" ቱባ ባህሎቻችን ተውበን ስናከብር በጦርነቱ ምክንያት ጥቃት የደረሳቸው ሴቶች በማገዝ ፣ ከቄያቸው የተፈናቀሉ ወገኖች በማስታወስ ሊሆን ይገባል ያሉት " ፕረዚደንት ጌታቸው " የኣሸንዳ ልጆች በወረራ የተያዙ መሬቶች በሰላም ስምምነቱ መሰረት በሰላማዊ መንገድ እንዲመለሱ እየተደረገ ያለውን ትግል በመደገፍ በዓላቸው ማድመቅ አለባቸው " ብለዋል።

" ባለፉት ሶስት አመታት በተካሄደው ዘግናኝ ጦርነት ምክንያት በዓሉ በአደባባይ መከበር አልቻለም"  ያሉት  ደግሞ የክልሉ የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ ዶ/ር አፅብሃ ገ/እግዚአብሔር  ናቸው።

ዶ/ር አፅብሃ ፤ የአሸንዳ ክብሮችን በማጉላት በአሉ ለአንድነት ፣ ለልማት ፣ ለሰላምና ዴሞክራሲ ማጠናከሪያ ሊውል ይገባዋል።

በውይይት መድረኩ  " የአሸንዳ ክብሮች ከፍትህ ፤ ከተጠያቂነትና ከስነ-ልቦናዊ ማገገም አንፃር " በሚል ርእስ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀረቡ ዶ/ር ትካቦ ገ/ስላሴ ደግሞ " በዓሉ ሴቶች ተውበው በዘፈንና ጭፈራ የሚያከብሩት የነፃነት መግለጫ ነው " ብለዋል።

" ኣሸንዳ በዓለም ከሚከበሩት የሴቶች የአደባባይ በዓላት የሚመደብ በራሳቸውና በሌላው ማህበረስብ የደስታ ስሜት የመፍጠር አቅምና አቀራርብ ያለው ነው " ያሉት ዶ/ር ትካቦ " በዓሉ ከመጤ ልምድ በመጠበቅ ለአገር ውስጥና ለውጭ ቱሪስቶች መስህብ ማዋል ይገባል " ብለዋል።

የበዓሉ ባለቤቶች የሆኑ ሴት ልጃገረዶች የታደሙበት የውይይት መድረኩ ፣ የመቐለ ዩኒቨርስቲ ፣ የባህልና ቱሪዝም ቢሮና የትግራይ ቴሌቪዥን በመተባበር እንዳዘጋጁት የቲክቫህ ሪፓርተር ከቦታው ዘግቧል።

@tikvahethiopia
#ኣሸንዳ #መቐለ

በመቐለ የኣሸንዳ በዓል ያለፀጥታ ችግር በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉ ተገልጿል።

ዘንድሮ የተገኘውን ሰላም ተከትሎ በርካታ ቁጥር ያለው ዜጋ በኣሸንዳ በዓል ላይ ለመካፈል ትግራይ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።

የመቐለ ከተማ ወንጀል መከላከል ኃላፊ ኮማንደር ሰለሞን በላይ ለትግራይ ቴሌቪዥን በሰጡት ቃል ፤ የዘንድሮውን የኣሸንዳ በዓል ለማክበር ከተለያዩ የሀገር ውስጥ እና ከውጭ ሀገራት የሚመጡ ታዳሚዎችን ደህንነት ለማስጠበቅ እና ያለምንም የፀጥታ ስጋት በዓሉን እንዲያሳልፉ ዝግጅቶች ሁሉ መጠናቀቁን ገልጸዋል።

ኮማንደር ሰለሞን ፤ " የዘንድሮውን በዓል ለማክበር የሀገር እና የክልል ሁኔታን የሚመጥን እቅድ ተዘጋጅቷል ፤ ለበዓሉ የሚመጥን የፀጥታ አካላትም ዝግጅታቸውን ጨርሰው እየተጠባበቁ ይገኛሉ " ብለዋል።

በዓሉ ሲከበር የትግራይ ህዝብ በጦርነት ምክንያት የማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ስነልቦናዊ ቀውስ በደረሰበት ወቅት ቢሆንም የተገኘውን የሰላም ጭላንጭል በመጠቀም ባህላዊ ትውፊቱን ለማስቀጠል ሁሉም የበኩሉን ሚና እንዲጫወት ለክልሉ ቴሌቪዥን በሰጡት ቃል ጥሪ አቅርበዋል።

@tikvahethiopia
#ኣሸንዳ

የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር የ #ኣሸንዳ በዓል ሲከበር እና ሲዘከር የተጀመረውን ሰላምን በማጠናከር እንዲሆን ጥሪ አቅርቧል።

ይህን ጥሪ ያቀረበው ዛሬ የኣሸንዳ በዓል ምክንያት በማድረግ በሰጠው መግለጫ ነው።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ ፤ " ኣሸንዳ ፣ ማርያ ፣ ዓይኒ ዋሪ የነፃነት የእኩልነት ተምሳሌት ፤ የሴቶች የአብሮነትና የአንድነት ምልክት በመሆን ፤ የትግራይ ክብርና እሴቶች በቅብብሎሽ የትውልዶች ማስተሳሰርያ ገመድ እንዲሆኑ የራሱ አስተዋፅኦ አድርገዋል እያደረገም ይገኛል " ብሏል።

ባለፉት አመታት በነበረው ጦርነት ምክንያት የትግራይ ሴቶች እንደ አሸንዳ የመሰሉ የአደባባይ በአላት በደስታና ፌስታ ሊያከብሩት ይቅርና ፀሃይ ወጥታ ሳለች ጨልሞባቸው ደግሞ ለመተረትክ የሚከብድ ግፍ እንደደረሰባቸው ገልጿል።

" ይሁን እንጂ ግፉ እንዲቆም በፅናት በመታገላችሁ እና በማታገላችሁ ቢያንስ አሁን ለተደረሰው ደረጃ ለመድረስ መተኪያ የሌለው ተግባር ፈፅማቹሃል " ያለው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፤ " አስተዳደሩና ህዝቡ በናንተ ኩራት ይሰማዋል " ብሏል።

በዓሉ ሲከበር እና ሲዘከር የተጀመረው ሰላም በማጠናከር ፣ የህዝብ ጥያቄዎች እና ፍላጎቶች ፣ በሰላማዊና ፓለቲካዊ ትግል ለመመለስ በሚደረገው ትግል አሁንም እንደትናንት በፅናት እንደምትታገሉ በመታመመን ነው ብሏል።

" ያለው ሁኔታ ከባድ ነው " የሚለው አስተዳደሩ " ተፈናቃይ ወገኖች አጅግ በከፋ የኑሮ ሁኔታ ላይ ነው ያሉት ፣ በአማራና ኤርትራ ታጣቂ ሃይሎች ስር የሚገኝ ህዝባችን ማለቅያ የሌላቸው ግፎች እየተፈፀሙበት ነው ፣ በመቶ ሺዎች የሚቆጥር ህዝባችን በረሃብ አለንጋ እየተገረፈ ይገኛል " ብሏል።

የትግራይ ሴቶች ይህን የመሰለ ከባድ ሁኔታ ተቋቁማችሁ የአሸንዳ ፣ ማሪያ ፣ ዓይኒ ዋሪ በዓል ለማክበር መቻላችሁ መንፈሳዊ ጥንካሬአችሁ ብርቱና ከፍተኛ መሆኑ ማሳያና ማረጋገጫ ነው ሲል ገልጿል።

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ጥያቄዎች በሰላማዊና ፓለቲካዊ ትግል እንዲመለሱ እጅግ እልህ አስጨራሽ ትግል እያካሄደ መሆኑን ገልጾ " አሁንም ተፈናቃይ ወገኖች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ፣ በትግራይ መሬት የሚገኙ የአማራና የኤርትራ ታጣቂዎች ለቀው እንዲወጡ ፣ የተቋረጠው ሰብአዊ አርዳታ እንዲጀምር ፣ ወንጀለኞች በህግ እንዲጠየቁ ለማድረግ ያላሰለሰ ትግል አካሂዳለሁ " ብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በአዲስ አበባ የኣሸንዳ በዓል መቼ ይከበራል ? የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፤ የባህልና ቱሪዝም ቢሮ የ2015 ዓ.ም የአሸንዳ በአል አከባበር መርሃ ግብር ይፋ አድርጓል። በዚሁ መሰረት፤ በዓሉን #ነሃሴ_28 ቀን 2015 ዓ/ም በአዲስ አበባ ለማክበር እቅድ መያዙ ገልጿል። የሚደረግ የጊዜ ለውጥ ካለ አስቀድሞ የሚገለፅ መሆኑንም አስተዳደሩ አሳውቋል። የበዓሉ መርሀግብር ምን ይመስላል ? - ነሃሴ 13…
ፎቶ ፦ ዛሬ ነሃሴ 15 ቀን 2015 ዓ/ም የ #ኣሸንዳ በዓልን ምክንያት በማድረግ በመቐለ ከተማ የጎደና የካርኒቫል ትርኢትና ሰማእታት የሚያስታውስ የሻማ ማብራት ስነ-ስርዓት ተከናውኗል።

#ማስታወሻ ፦ ከ " ኣሸንዳ " አከባበር ጋር በተያያዘ በክልሉ ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ የወጣው መርሀ ግብር ከላይ ተያይዟል። በቢሮው ከተገለፀው ውጭ የሚካሄደ የአሸንዳ በዓል ዝግጅት እውቅና እንደሌለው ተነግሯል።

Photo Credit : Demtsi Weyane

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የዘንድሮው የኣሸንዳ ፣ ማርያ ዓይኒ ዋሪ በዓል እንዴት እየተከበረ ነው ? የኣሸንዳ ፣ ማርያ ዓይኒ ዋሪ በዓል ካለፉት ዓመታት እጅግ በተሻለ ድምቀት በትግራይ እንዲሁም በሌሎች አካባቢዎች በድምቀት እየተከበረ ይገኛል። በዓሉ በዋነኝነት ትግራይ ውስጥ እጅግ በደመቀ ሁኔታ በመከበር ላይ ነው። ከእሁድ ነሃሴ 13/2015 ዓ.ም ጀምሮ በይፋ መከበር የጀመረው በዓሉ ፤ ነሃሴ 13 ና 14 / 2015 ዓ.ም በዓዲግራት…
#ኣሸንዳ

የዘንድሮው የኣሸንዳ በዓል ወደ አለፍነው ጦርነት ያስገቡን ስህተቶች ላለመደግም ቃል የምንገባበት ነው ሲሉ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕረዚደንት ጌታቸው ረዳ ተናግረዋል።

" ባለፉት ሁለት ሶስት የጦርነት አመታት በትግራይ ሴቶች የደረሰው ግፍ አሰቃቂ ነው። " ያሉት አቶ ጌታቸው  " የትግራይ ሴቶች ሰላምና ስቃይ የትግራይ ህዝብ ሰላምና ስቃይ ነው። " ብለዋል።

" ከሶስት አመታት በፊት የአሸንዳ በዓል ከተጫወቱት ቆነጃጂት በጦርነት ምክንያት  አካላቸው የጎደሉ የተሰው አሉ " ያሉት ፕሬዜዳንቱ " ይህንን እንዳይደገም በሚደረገው ትግል የሴቶች ተሳትፎ ከፍተኛ ነው። " ሲሉ አስገንዝበዋል።

ሴቶች ተውበው የአሸንዳ በዓል ሲያከብሩ ኤችአይቪ ኤድስ የመሰሉ ተላላፊ በሽታዎች መዘንጋት እንደሌለባቸው አሳስበዋል።

" በዓሉ ተፋናቃይ ህዝባችን ወደ ቀድመው ቄየው የሚመለስበት ፣ ስቃይ ውስጥ የሚገኘው ህዝባችን ነፃ እንዲሚወጣ ገሃድ የሚሆንበት እንደሚሆን እንተማመናለን " ብለዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የሃሳብ ልዩነቱ ወደ ግጭት አያመራም " - አቶ ጌታቸው ረዳ ዓመታዊው የ2016 ዓ/ም የአሸንዳ በዓል ዛሬ ነሃሴ 16/2016 ዓ/ም በመላ ትግራይ መከበር ጀምሯል። በዓሉ እስከ ነሃሴ 24/2016 ዓ.ም አንደሚቀጥል የወጣው መርሃ ግብር ያመለክታል። በሌላ በኩል ፕሬዜዳንት ጌታቸው በ2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር የተገነባ የ10.2 ኪሎ ሜትር  የአስፋልት መንገድ ሲመርቁ ፤ የአሸንዳ አደባባይ ግንባታ መሰረተ…
#ኣሸንዳ

ከሰሞኑን በፖለቲካ ትኩሳት ውስጥ የከረመችው ትግራይ በደማቅ ሁኔታ የዘንድሮውን የኣሸንዳ በዓል እያከበረች ነው።

በዓሉን ለማክበር በርካታ እንግዶች ትግራይ ይገኛሉ።

በዓሉ እስከ ነሃሴ 24 ቀን 2016 ዓ/ም በተለያዩ ስነስርዓቶች እየተከበረ ይቀጥላል።

በትግራይ የተለያዩ አካባቢዎች ላይ የሚከበረው የኣሸንዳ በዓል ፍቅር፣ ይቅር ባይነትና መልካም ተግባቦት በተግባር የሚንጸባረቅበት በዓል ሲሆን በዓሉ በልጃገረዶች ይበልጥ ትኩረት ተሰጥቶት ይከበረል።

ልጃገረዶች አደባባይ ወጥተው ይህን በዓልን በድምቀት ያከብራሉ።

የበዓሉ ይዘት በዋናነት ህብረተሰቡ ውስጥ ያሉ መልካም ተግባቦቶች፣ ፍቅርንና ይቅር ባይነት ላይ ያነጣጠረ ነው።

የሌሎች ሃሳቦች፣ ጭፈራዎች እና ትእይንቶች እንዲታዩ የሚጋብዝ በዓል ከመሆኑም ባለፈ የሃይማኖትና የብሔር ልዩነት አይንፀባረቅበትም።

ፎቶ፦ ትግራይ ቲቪ (ኖርዘርን ስታር ሆቴል፣ መቐለ ነሐሴ 17)

#Ashenda #Tigray

@tikvahethiopia