TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA #KENYA ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገር ኬንያ ጋር በሰላምና የደህንነት ጉዳዮች ለመተባበር ተስማምታለች። ዛሬ የኢፌዲሪ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና የኬንያ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ሮበርት ኪቢቹ ኬንያ፣ ናይሮቢ ውስጥ ተወያይተዋል። ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ከኬንያ አቻቸው ጄኔራል ሮበርት ኪቢቹ ጋር ባደረጉት ምክክር ሁለቱ አገሮች…
#Ethiopia #SouthSudan

በጄኔራል አበባው ታደሰ የተመራ ልዑክ ቡድን በደቡብ ሱዳን የሥራ ጉብኝት እያካሄደ ነው።

የኢትዮጵያ የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጀኔራል አበባው የሚመሩት ልዑክ በደቡብ ሱዳን ጁባ የስራ ጉብኝት እያደረገ ይገኛል።

በዚህ የስራ ጉብኝት ጀነራል አበባው ታደሰ ከደቡብ ሱዳን አቻቸው ሉ/ጄኔራል ቶይ ቻኒይ ሬይት ጋር ውይይት አድርገዋል።

በሎጂስቲክስ እና በአቅም ግንባታ ጉዳዮች ለደቡብ ሱዳን ድጋፍ ለማድረግና ተሞክሮ ለማጋራት እንዲሁም የሁለቱ አገራት #የድንበር_አካባቢ ፀጥታና ደህንነትን ለማረጋገጥ በትብብር ለመሥራት ከስምምነት መደረሱ ተገልጿል።

ትላንትና የኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ፤ በናይሮቢ ከኬንያ አቻቸው ከጄኔራል ሮበርት ኪቢቹ ጋር ውይይት ካደረጉ በኃላ ሁለቱ ሀገራት በሰላም እና የደህንነት ጉዳዮች ላይ ለመተባበር ስምምነት ማድረጋቸው አይዘነጋም።

@tikvahethiopia