TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#MoE

የትምህርት ሚኒስቴር ፤ የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና " ላልተገደበ ጊዜ " እንደሚሰጥ አሳውቋል።

የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን የሚያገኙት ፈተናውን ወስደው ብቁ መሆናቸው ሲረጋገጥ ብቻ ነው ተብሏል።

ተማሪዎች ፈተናውን ደጋግመው መውሰድ የሚችሉበት ዕድል መመቻቸቱን በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ጥራትና ብቃት ማሻሻያ ዴስክ ኃላፊ ሰይድ መሀመድ ለኢፕድ ተናግረዋል።

የዩኒቨርሲቲ ቆይታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎች በየስድስት ወሩ ፈተናውን የሚወስዱበት ዕድል እንዳለ ኃላፊው ጠቁመዋል።

የመንግስት ዩኒቨርሲቲ ተመራቂዎች ለአንድ ጊዜ ብቻ የፈተና ወጪያቸው እንደሚሸፈንላቸው ገልጸዋል።

በመንግሥትና በግል ተቋማት ላይ የሚሰጡ ከ300 በላይ የመጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ፕሮግራሞች እንዳሉ ያነሱት ኃላፊው፤ በየትምህርት መስኩ እየተደረገ በአስር ዙር ፈተናው ለመስጠት ታቅዷል።

#ኢፕድ

More : @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" የባጃጅ አሽከርካሪዎች በቅርቡ ወደ ሥራቸው ይመለሳሉ " - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ

የባጃጅ አሽከርካሪዎች በቅርቡ ወደ ሥራቸው እንደሚመለሱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ ማስታወቁን ኢፕድ ዘግቧል።

ይህ የተገለፀው የቢሮው ኃላፊ አቶ ምትኩ አስማረ በቅርቡ እየተነሣ ካለው የባጃጅ አገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ በሰጡት መግለጫ ነው።

የከተማ አስተዳደሩ የባጃጅ አገልግሎትን የተሻለ ለማድረግ የአሠራር ማስተካከያ እያደረገ ነው ያሉት ኃላፊው ይህ ተግባራዊ እስከሚሆን ድረስ የባጃጅ አሽከርካሪዎች እና ተጠቃሚዎች በትዕግሥት እንዲጠብቁ አሳስበዋል።

የባጃጅ ትራንስፓርት መንግሥት የትራንስፖርት አገልግሎትን ማድረስ በማይችልበት የከተማ ዳርቻዎች፣ የጋራ መኖሪያ ቤቶች አካባቢ አገልግሎት መሰጠት እንደተጀመረ አስታውሰው፣ አሁን ላይ አገልግሎቱ እየተስፋፋ ሄዶ በከተማይቱ ውስጥ ከሚገኙ 11 ክፍለ ከተሞች መካከል በስምንቱ አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኙ ጠቁመዋል።

ከተማ አስተዳደሩ አገልግሎቱን ወደ አሠራር ለማስገባት ባደረገው ጥረት 9 ሺህ 950 የባጃጅ አገልግሎት ሰጪዎች በ123 ማኅበራት ተደራጅተው በስምንቱ ክፍለ ከተሞች ላይ እንደሚሠሩ የገለፁት ኃላፊው ብዛት ያላቸው ግን እንዳልተመዘገቡ ጠቁመዋል።

የከተማ አስተዳደሩ መሠራት ያለባቸውን ሥራዎች እንዳጠናቀቀ በቅርቡ ወደ ሥራ እንደሚመለሱ ተናግረዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ትራንስፖርት ቢሮ የባጃጅ ትራንስፖርት የአገልግሎት አስፈላጊነት በዝርዝር ተጠንቶ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ ከየካቲት 30/2015 ጀምሮ በከተማዋ በየትኛውም አከባቢ ላልተወሰነ ጊዜ የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት የታገደ መሆኑን መግለጹ ይታወሳል።

#ኢፕድ

@tikvahethiopia
#ጤፍ

የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ስለ #ጤፍ ...

" አጠቃላይ የኑሮ ውድነቱን በተመለከተ የኛን መስሪያ ቤት #አይመለከትም " - ወ/ሮ በላይነሽ ረጋሳ (የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር)

🗣 ወ/ሮ አረጉ ጥፍጤ፦

" የጤፍ ዋጋ በጣም ጨምሯል፤ በወፍጮ ቤቶች ጤፍ የለም። በአንዳንድ ወፍጮ ቤቶች ቢገኝም እንደጤፉ ዓይነት እስከ 8 ሺ 500 መቶ ብር ድረስ እየተሸጠ ይገኛል።

25 ኪሎ ጤፍ በሁለት ሺህ ብር ገዝቻለሁ ነገር ግን ዋጋው በዚህ ሁኔታ የሚቀጥል ከሆነ ጤፍ ገዝቼ እንጀራ የምበላ አይመስለኝም።

በዜህ ዋጋ ለመግዛት እንኳን ምርቱን ማግኘት አልተቻለም ፤ ስለሆነ መንግሥት ጉዳዩን ትኩረት ሰጥቶ ሊያየው ይገባል። "

🗣 አቶ መሀመድ ጀማል ፦

" በገበያው ላይ በቂ ጤፍ ባለመኖሩ ኅብረተሰቡ ሳያልቅ እንግዛ እየተባባለ ነው።

በወፍጮ ቤት ተቀጥሬ መስራት ከጀመርኩ አምስት ዓመት አልፎኛል። ነገር ግን የጤፍ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ በመጨመሩ ምክንያት ቤተሰቤን ለማስተዳደር እንደዚህ የተቸገርኩበት ወቅት የለም።

ይህ ጉዳይ ሥር ሳይሰድ የሚመለከታቸው የመንግሥት ተወካዮች ችግሩን በአስቸኳይ ሊፈቱት ይገባል።

🗣 አቶ አብርሃም ዳኜ ፦

" ኅብረተሰቡ ለዕለት ፍጆታ የሚውሉ ምርቶችን በአቅራቢያው በተመጣጣኝ ዋጋ ሊያገኝ ይገባል፤ እየታየ ያለው የገበያ ዋጋ ግን የሚቀመስ አልሆነም።

በተለይ ዝቅተኛ ገቢ ያለው ማኅበረሰብ የዋጋ ጭማሪውን መቋቋም አልቻለም።

የዋጋ ጭማሪ ለዕለት ተዕለት በሚውሉ ምርቶች ላይ መደረግ የለበትም። የአገር ውስጥ ምርቶች ላይ የሚደረገው የዋጋ ጭማሪ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ያሉ የማኅበረሰብ ክፍሎችን መሠረት ያደረገ አይደለም።

መንግሥት ለዕለት ተዕለት ፍጆታዎች የዋጋ ተመን አውጥቶ ሕግ የሚተላለፉ አካላት ላይ አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ ይጠበቅበታል። "

🗣 በልደታ ክ/ከተማ የወፍጮ ቤት ባለቤት አቶ ሰለሞን ባይሳ (ስማቸው የተቀየረ) ፦

" የጤፍ አቅርቦት ችግር እና የዋጋ ጭማሪው ከኅብረተሰቡ ጋር ያለመተማመን ሁኔታ ውስጥ ከቶኛል። ወፍጮ ቤቴን ለአራት ቀን አልከፈትኩም።

ለኅብረተሰቡ የምሸጠው ጤፍ ስለሌለ ኅብረተሰቡ ጤፍ የደበቅኩ እየመሰለው ነው። ስለሆነም ከኅብረተሰቡ ጋር ላለመጋጨት ጥቂት ጤፍ ያላቸው ነጋዴዎችን ተለማምጬ ለኅብረተሰቡ ጤፍ አምጥቻለሁ።

የኅብረተሰቡ አቅም እና የገበያው ሁኔታም የሚጣጣም አይደለም። ስለዚህ መንግሥት ጉዳዩን በትኩረት ሊያስብበት ይገባል። "

🗣 የእህል በረንዳ ነጋዴ የሆኑት አቶ አማን ይሁን (ስማቸው የተቀየረ) ፦

" መንግሥት የንግድ ዘርፉን እንዲቆጣጠሩ ኃላፊነት የሰጣቸውን አካላት በዘርፉ ምን እየሠሩ እንደሆነ መመርመር ያለበት ሲሆን በኬላዎች አካባቢ እየተሠራ ያለውን ኢኮኖሚያዊ አሻጥር ከሥር ነቅሎ ማጥፋት አለበት።

ወቅቱ ከፍተኛ ምርት ያለበት እና ኢትዮጵያ ሰላም የሆነችበት ወቅት ነው። በዚህ ወቅት በተለየ ሁኔታ የእህል ዋጋ እንደ ሰማይ እየራቀ በመምጣቱ ዜጎችን ይበልጥ እያስጨነቀ ነው።

ስለሆነም ይህንን ጉዳይ መንግሥት ትኩረት ሰጥቶ መፍታት አለበት።

🗣 የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ወ/ሮ በላይነሽ ረጋሳ ፦

" አጠቃላይ የኑሮ ውድነቱን በተመለከተ የኛን መስሪያ ቤት #አይመለከትም። ጉዳዩ ዘርፈ ብዙ ተዋንያን ያሉት ነው።

ዋጋ ባልወጣበት ነገር ላይ ኃላፊነት መውሰድ አይቻልም።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አሁን ለተፈጠረው የጤፍ ዋጋ ኃላፊነት 'ማንዴት' የለውም። የንግድ ሥርዓቱን በተመለከተ አጥንተን በቀጣይ ምላሽ የምንሰጥበት ይሆናል።

🗣 የአዲስአበባ ከተማ ንግድ ቢሮ ፦

" በከተማ አስተዳደሩ በኩል ግብረኃይል ተቋቁሟል የተደረሰበትን በቀጣይ እናሳውቃለን "

#ኢፕድ

@tikvahethiopia
#MoE

" የመውጫ ፈተናውን በተደጋጋሚ ወስዶ ማለፍ ያልቻለ ተማሪ ከዲግሪ በታች ባሉ ደረጃዎች ምዘና ወስዶ መቀጠል እንዲችል የሚያደርግ የብቃት ማረጋገጫ ማዕቀፍ እየተዘጋጀ ነው " - ትምህርት ሚኒስቴር

250 ሺ ለሚጠጉ የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

በመጪው #ሐምሌ_ወር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ለሚመረቁ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት እየተጠናቀቅ እንደሚገኝ በሚኒስቴሩ የከፍተኛ ትምህርት ጥራትና ብቃት ማሻሻያ ዴስክ ኃላፊ ሰይድ መሐመድ ለኢፕድ ተናግረዋል፡፡

የትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተናውን በተሳካ ሁኔታ ለመስጠት ከመንግሥት እና ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በቅርበት እየሠራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

የመውጫ ፈተናውን ወስደው ማለፍ ያልቻሉ ተማሪዎች ደጋግመው መፈተን የሚችሉበት ዕድል መኖሩን ኃላፊው አመልክተዋል።

ፈተናውን በተደጋጋሚ ወስዶ ማለፍ ያልቻለ ተማሪ ከዲግሪ በታች ባሉ ደረጃዎች ምዘና ወስዶ መቀጠል እንዲችል የሚያደርግ የብቃት ማረጋገጫ ማዕቀፍ በትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን በመዘጋጀት ላይ ይገኛል ብለዋል።

ይሁን እንጂ ተፈታኙ ለዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ዝግጁ ነኝ ብሎ ባሰበ ጊዜ ፈተናውን መውሰድና ማለፍ ከቻለ የዲግሪ ማረጋገጫ ማግኘት እንደሚችል ገልጸዋል።

የመውጫ ፈተናው በ #ኦንላይን እንደሚሰጥ ያመለከቱት ኃላፊው፤ ለዚህ ያመች ዘንድም የሶፍትዌር ማዘጋጀትን ጨምሮ ፈተናውን በስኬት መስጠት የሚያስችሉ ሥራዎች በመሠራት ላይ ናቸው ብለዋል።

ተማሪዎች ዋናውን ፈተና ከመፈተናቸው በፊት ሞዴል ፈተናዎች እንደሚወስዱ ጠቅሰዋል፡፡ 

#ኢፕድ

@tikvahuniversity @tikvahethiopia
#ETHIOPIA

" የድርቅና ጎርፍ አደጋዎች በቀጣዮቹ ሳምንታትም #ተባብሠው ሊቀጥሉ ይችላሉ " - የሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት

በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች እየተከሠቱ ያሉት የድርቅና የጎርፍ አደጋዎች በቀጣዮቹ ሳምንታትም #ተባብሠው_ሊቀጥሉ እንደሚችሉ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታውቋል።

የኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳሬክተር አቶ ክንፈ ኃ/ማሪያም በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ62ኛ በኢትዮጵያ ለ42ኛ ጊዜ በሚከበረው የሚቲዎሮሎጂ ቀን ላይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ነው ይህ የተሰማው።

አቶ ክንፈ " በተቋሙ የተሠሩ ጥናቶች የሚያሳዩት #የድርቅ እና #የጎርፍ አደጋዎች በሀገሪቱ በቀጣይም በይበልጥ ተጠናክረው ይከሰታሉ " ብለዋል።

" የሚደርሰውን አደጋ ለመቋቋም የተጠናከረ የአየር ሁኔታ መከታተል ፣ መተንበይ እና ቅድሚያ ማስጠንቀቂያ ሥርዓትን መገንባትና ማዘመንን ይገባል " ያሉት ምክትል ዳይሬክተሩ " እየተከሰተ ያለውን የአየር ንብረት መዛባት ቀድሞ ለመተንበይ የሚያስችል ብሔራዊ የአየር ጠባይ አገልግሎት ማዕቀፍ በሀገሪቱ ተዘርግቷል ፤ ይህ ተጠናክሮ ወደ ሙሉ ትግበራ እንዲገባ የባለድርሻ አካላት ርብርብ ያስፈልገዋል " ብለዋል።

አቶ ክንፈ ፤ በሀገሪቱ ለማኅበራዊ እና ለኢኮኖሚ መሠረት የሆኑ የግብርና፣ የውሀ፣ የኢነርጂና የአደጋ ሥጋት ቅነሳ መርሐ ግብሮች በአየር ንብረት መዛባት ተፅዕኖ ስር መሆናቸውን ገልፀው በእነሱ ላይ የሚደርሠውን የአየር ንብረት መዛባት አደጋ ለመቀነስ ተቋሙ ጥናትና ክትትል የማድረግ ሥራ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

" በአየር ንብረት መዛባት የሚመጡ አደጋዎችን ማለትም ጎርፍ፣ ድርቅና የመሳሰሉትን ለመቀነስ ተቋሙ ክትትልና ጥናት በማድረግ ኅብረተሰቡን ከአደጋ ለመከላከል እየሠራ ነው " ሲሉ የገለፁት አቶ ክንፈ ፥ በአየር ንብረት መዛባት የሚደርሰውን የተለያየ አደጋ በዘላቂነት ለመቋቋም ተቋሙ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሠራ መሆኑን ባለድርሻ አካላትም በአጋርነት እየሰሩ ስለመሆናቸው ተናግረዋል።

#ኢፕድ

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

" ከ75 ሺ በላይ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎችን የሚኒስትሪ ፈተና ለማስፈተን ዝግጅት እየተደረገ ነው " - የአ/አ ትምህርት ቢሮ

ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ በሚሰጠውን የ6ኛ ክፍል የሚኒስትሪ ፈተና ተማሪዎችን ለማስፈተን የዝግጅት ሥራዎችን እየሠራ መሆኑን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አስታውቋቃ።

የቢሮው የፈተና ዝግጅት እና አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ዲናኦል ጫላ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የሠጡት ቃል ፦

- በአዲስ አበባ ከተማ በግል እና በመንግሥት ትምህርት ቤቶች በትምህርት ገበታ ላይ የሚገኙ ከ75 ሺህ በላይ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለማስፈተን ዝግጅት እየተደረገ ነው።

- ከቢሮ እስከ ትምህርት ቤቶች ድረስ ተማሪዎቹን ለፈተና የማዘጋጀት ሥራ እየተሠራ ይገኛል።

- ተማሪዎች የሚኒስትሪ ፈተና ከመፈተናቸው አስቀድሞ የተለያዩ ደረጃቸውን የጠበቁ ሞዴል ፈተናዎችን በማዘጋጀት በወሩ እንዲወስዱ ተደርጓል። ለፈተናው የተለያዩ አጋዥ መጽሐፍትንም አንብበው እንዲዘጋጁ እና እንዲፈተኑ እየተደረገ ነው።

- በአማርኛ ቋንቋ የሚፈተኑ አራት እንዲሁም በአፋን ኦሮሞ የሚፈተኑ አምስት የትምህርት ዓይነት ፈተናዎች የሚወስዱ ይሆናል። በዚህ መሠረትም ፦
👉 የሒሳብ፣
👉 የአካባቢ ሳይንስ፣
👉 አማርኛ፣
👉 አፋን ኦሮሞ እና እንግሊዝኛ የትምህርት ዓይነቶች ይሰጣሉ።

- ምዝገባው የሚካሄደው በኦንላይን ሲሆን የተመዘገቡ ተማሪዎች የተመዘገቡበትን የስም እና ዕድሜ ስህተት እንዳይኖር ማረጋገጥ እና ማስተካከል ይችላሉ።

- በየክላስተሩ ላሉ ትምህርት ቤቶች ወጥ በሆነ መልኩ ስልጠና በመስጠት ትምህርት ቤቶች ራሳቸው ፈተናዎችን እንዲያወጡ እና እንዲፈተኑ ይደርጋል።

- በአዲሱ ሥርዓት ትምህርት በየምዕራፉ ማጠናቀቂያ ላይ ለተማሪዎች ፈተና ይሰጣል። ለዚህም አንደኛ ምዕራፍ የሚባለው ከአንደኛ እስከ ስድስተኛ ክፍል ያለው የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ሲሆን ሁለተኛ ምዕራፍ የሚባለው ከሰባት እስከ ስምንተኛ ክፍል ነው።

- የመጀመሪያ ምዕራፍ የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች የሚያጠናቅቁት ስድስተኛ ክፍል ላይ ስለሆነ የሚኒስትሪ ፈተናው ተማሪዎች ከታች ጀምረው ራሳቸውን እያነጹ እንዲመጡ የሚያደርግ ነው። የትምህርት ጥራትን ከማረጋገጥ አንጻር ከፍተኛ ጥቅም አለው።

- የመማሪያ መጽሐፍት በሚፈለገው ልክ ሀገር ውስጥ አለመገኘት እና በውጭ ምንዛሪ እጥረት ምክንያት ከውጭ የሚመጡ መጽሐፍት የመዘግየት ሁኔታ አለ።

- የሚኒስትሪ ፈተና የሚሰጥበት ቀናት የሚወሰነው በአገር አቀፍ ደረጃ ቢሆንም እንደ ቢሮ #ከሰኔ አጋማሽ በኋላ ለመስጠት ዝግጁ ነን።

#ኢፕድ

@tikvahethiopia
#አሁን

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ስብሰባው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እያካሄደ ነው።

የም/ ቤቱ አባላት ጥያቄዎችን እየቀረቡ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለቀረቡላቸው ጠያቄዎች ምላሽ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።

እስካሁን ፦

- ከኦነግ ሸኔ፣
- ከአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ፣
- ከሰሜኑ የሰላም ስምምነት፣
- ከዜጎች መፈናቀልና ግድያ፣
- ወደ አዲስ አበባ እንዳይገቡ ስለተከለከሉ ዜጎች፣
- አርሶ አደሩ ምርቱን ለመሸጥ ከመቸገሩ ጋር በተያያዘ፣
- ወደ አዲስ አበባ ምርት እንዳይገባ ከመከልከሉ ጋር፣
- ከክልሎች የርስ በርስ መናበብ አለመቻል፣
- የሱዳን ወታደሮች ወረው የያዙትን የኢትዮጵያ መሬትና ያወደሟቸውን ንብረቶች የተመለከቱ ጥያቄዎች ቀርበዋል።

አሁንም የምክር ቤቱ አባላት ጥያቄዎችን በማቅረብ ላይ ናቸው። 

#ኢፕድ

@tikvahethiopia
#ቦንጋ

ኢትዮጵያ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ በቡና ሳይንስ ትምህርት መስክ የተማሩ ተማሪዎች ሊመረቁ ነው።

የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፤ በ2015 የትምህርት ዘመን መጨረሻ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ 37 ተማሪዎችን በ " ቡና ሳይንስ " የትምህርት መስክ ያስተማራቸውን ተማሪዎች እንደሚያስመርቅ አሳውቋል።

ዩኒቨርሲቲው የቡና ምርት ኢትዮጵያ ትልቁ የውጭ ምንዛሬ የምታገኝበት ሸቀጥ በመሆኑ በ2015 ዓ.ም መጨረሻ 37 ተማሪዎችን በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በቡና ሳይንስ የትምህርት መስክ ይመረቃሉ ብሏል።

ኢትዮጵያ ቡናን ለዓለም ያበረከተች ሀገር ብትሆንም እስካሁን ድረስ የቡና ትምህርት መስክ ብቁ ባለሙያዎችን ማፍራት አዳጋች ሆኖ ነበር ያለው ተቋሙ የዩኒቨርሲቲው ሴኔት የቡና ሳይንስ ትምህርት ክፍል እራሱን ችሎ በ2012 ዓ.ም እንዲከፈት ማድረጉን አስታውሷል ።

በቡና ምርት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመመርመር ከዘርፉ ተጠቃሚ ለመሆን ቡናን በትምህርትና ምርምር አስደግፎ ለመምራት ዩኒቨርሲቲው በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ የቡና ሳይንስና ቴክኖሎጂ ትምህርት ክፍል በማቋቋም ነው ተማሪዎችን እያስተማረ የሚገኘው።

በሚቀጥለው ዓመት በሁለተኛ ዲግሪ በቡና ሳይንስ ተማሪዎች የሚመረቁ ሲሆን፤ ዩኒቨርሲቲው በቀጣይ ጊዜትም የቡና ሳይንስ ትምህርት መስክን በዶክትሬት ዲግሪ ደረጃ ማስተማር እንደሚጀምር ዶክተር ጴጥሮስ ጠቁመዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ካለው 200 ሄክታር መሬት ውስጥ በ150 ሄክታሩ ላይ የግብርና ምርቶችን እያከናወነ መሆኑን ገልጿል።

#ኢፕድ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba " አዲስ ተሽከርካሪዎች ገበያ ላይ የሚሸጡበት ዋጋ እና የሚቆርጡት ደረሰኝ ሰፊ ልዩነት እንዳለው በጥናት አረጋግጠናል " - የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ከአሽከርካሪ ተሽከርካሪ ፍቃድና ቁጥጥር ባለስልጠን ጋር በመሆን በተሽከርካሪዎች ግብይትና አሰራር ዙሪያ ትላንት መግለጫ ሰጥቶ ነበር። በመግለጫው የተሽከርካሪዎች ግብይት መሬት ላይ ያለው…
#ይወረሳሉ !

" በሕገወጥ መንገድ የገቡ መኪናዎች #ይወረሳሉ " - የአዲስ አበባ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፍቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን

ካለፉት ዘጠኝ ዓመታት ጀምሮ በሕገወጥ መንገድ የገቡ ተሽከርካሪዎች ላይ ርምጃ እንደሚወሰድ የአዲስ አበባ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፍቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን አስታውቋል።

በሕገወጥ መንገድ ገብተዋል የተባሉ መኪናዎችን የመለየት ሥራ መሰራት ከተጀመረ አንድ ወር ሆኖታል ተብሏል።

ባለሥልጣኑ ከአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ጋር በጋራ በመሆን ባደረገው ጥናት በባለሥልጣኑ የሚመዘገበው የገንዘብ መጠን እና ለገቢዎች ቢሮ የሚቆረጠው ደረሰኝ ተመሳሳይ ያለመሆን ሁኔታዎች መኖራቸው አመላክቷል።

በዚህም በተለይ የአዲስ ተሽከርካሪዎች ዋጋ የሚቆረጥበት ደረሰኝና ገዢዎች ለመኪናው የሚከፍሉት ዋጋ ሰፊ ልዩነት ያለው መሆኑ ተረጋግጧል።

መንግሥት ከተሽከርካሪዎች ግዥና ሽያጭ ማግኘት የሚገባውን የታክስ ገቢ እያገኘ አይደለም ያለው ባለስልጣን መ/ቤቱ ይህንን እና መሰል ችግሮችን ለመቅረፍ ካለፉት ዘጠኝ ዓመታት ጀምሮ በሕገወጥ መንገድ የገቡ መኪናዎችን የመለየት ሥራ ተጀምሯል ብሏል።

ተቋሙ በተለያዩ ጊዜያት ሁለት አይነት ሕገወጥ ተግባራት እንደሚያጋጥሙት ገልጿል እነዚህም ፦
- ከክልል በዝውውር የሚመጡ መኪናዎች ላይና
- በተጭበረበረ ሰነድ የተመዘገቡ መኪናዎች ናቸው።

ይህንን ለመከላከል የሚያግዝ ዘመናዊ ሥርዓት የመኪናዎቹን ሕጋዊነት የማጣራት ሥራ እየተሠራ መሆኑን አሳውቋል።

የማጣራት ሥራው የሚሠራው ካለፉት ዘጠኝ ዓመታት ጀምሮ ሲሆን ከዚህ በፊት አንድ የመኪና ሻጭ በስሙ የነበረውን መኪና ለሌላ ሰው ሲያስተላልፍ የማጣራት ሥራ እንዳልተሠራ እና በዚህም መንግሥት ማግኘት የሚገባውን ታክስ እንዳላገኘ ተገልጿል።

አሁን ግን ከጉሙሩክ ኮሚሽን ጋር በጋራ በመሆን አዲስ ሥርዓት መዘርጋት ተችሏል ተብሏል።

ሥርዓቱም መንግሥት ከተሽከርካሪዎች ማግኘት የሚገባውን ታክስ እንዲያገኝ ከማድረግ ባለፈ መኪና ገዢዎች እንዳይጭበረበሩ እና መንግሥት ሕገወጥነትን ለመከላከል የሚያደርገውን ጥረት የሚያጠናክር እንደሆነ ተገልጿል።

በሂደቱም በሕገወጥ መንገድ የገቡ መኪናዎች #እንደሚወረሱ ባለስልጣን መ/ቤቱ አሳውቋል።

የአዲስ አበባ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፍቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን ፤ የአዲስ መኪና ገዢዎች የሚከፍሉት ዋጋ በደረሰኙ ላይ መጠቀሱን በማረጋገጥ ሊገዙ ይገባል ብሏል።

ይህንን ማድረግ ለገዢው በርካታ ጠቀሜታ የሚያስገኝ ከመሆኑ ባለፈ የሚሰበሰበው ገቢ ለከተማዋ መሠረተ ልማት የሚውል በመሆኑ በኃላፊነት ሊታይ እንደሚገባ አሳስቧል።

#ኢፕድ

@tikvahethiopia
#Update

የ2015 ዓ.ም ብሔራዊ የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና ለመውሰድ ከ869 ሺህ በላይ ተፈታኞች በኦንላይን መመዝገባቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል፡፡

ለ2ኛ ጊዜ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚሰጠውን አገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ 869 ሺህ 765 ተፈታኞች በኦንላይን መመዝገባቸውን በአገልግሎቱ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወንደወሰን ኢየሱስወርቅ ለኢፕድ ተናግረዋል፡፡

ከተመዘገቡት ውስጥ 503,812 ተማሪዎች የሶሻል ሳይንስ እና 365,954 የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች መሆናቸውን ኃላፊው ገልጸዋል።

የፈተና አስፈጻሚዎች፣ ሱፐርቫይዘሮች እና የፈተና ጣቢያ ኃላፊዎች ምልመላ ቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል፡፡

የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ከፍል ማጠቃለያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ 30/2015 ዓ.ም በሁለት ዙር እንደሚሰጥ ይታወቃል፡፡ #ኢፕድ

More : @tikvahuniversity

@tikvahethiopia
#ጉጂ

ላለፉት ስምንት ዓመታት የጉጂ አባገዳ በመሆን ያገለገሉት አባ ገዳ ጂሎ ማንዶ ለአዲሱ አባገዳ የ " ባሊ " ስልጣን የማስረከብ መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው።

በአሁኑ ወቅት በርካታ ህዝብ በአዶላ ከተማ አቅራቢያ " ሜኤ ቦኮ አርዳ ጂላ " በተሰኘው ስፍራ በባህላዊ ትውፊት መሰረት የሚከናወነውን 75ኛውን የስልጣን ርክክብ መርሐ ግብር ለመታደም ተሰባስቧል።

የአበገዳ ስልጣን ርክክብና ተተኪ አበገዳ የመመረጡ ሂደት እጅግ ሚስጥራዊ ከሚባሉት ክንውኖች መካከል አንዱ ሲሆን፤ ተተኪውን አባገዳ የሚታወቀው በመጨረሻው የዕለቱ መርሐ ግብር መቋጫ ላይ ብቻ ነው። #ኢፕድ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ መንግስት ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች/startups እንዲያብቡ በርካታ የፖሊሲ ለውጦችን ለማድረግ መወሰኑ ተሰማ። ከነዚህም መካከል ፦ - ከስራ ፈቃድ፣ - ከግብር፣ - ከቢሮ ኪራይ፣ - ከፋይናንስ አቅርቦት፣ - ከጉምሩክ አሰራር ጋር በተያያዘ ወሳኝ ለውጥ የሚደረግባቸው ይሆናሉ ተብሏል። ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ በተገኙበት ዛሬ ይፋ የተደረጉ ለውጦች በተለይ ስራ ፈጣሪዎች ከውጭ ለሚኖራቸው…
' ስታርት አፕ '

በኢትዮጵያ ለ ‘ስታርት አፕ’ ዘርፍ ዕድገት መሠረት የሚጥሉ የተለያዩ የሕግና የፋይናንስ አሠራር ማሻሻያዎች መደረጋቸውን የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አሳውቀዋል።

ምንድነው የተደረጉት ማሻሻያዎች / የተዘረጉት አዳዲስ አሰራሮችስ ምንድናቸው ?

- የፈጠራ ሃሳብ ያላቸው ወጣቶች ሃሳባቸውን ወደ ተግባር ለማዋል በሚፈልጉበት ወቅት ያለምንም የንግድ ቤት ኪራይ ውል ሥራ መጀመር ይችላሉ።

- ማንኛውም የውጭ ሀገር ፈንድ ያገኘ ስታርት አፕ ሙሉ በሙሉ የውጭ ምንዛሪውን ለሚፈልገው ሥራ ማዋል ይችላል።

- አዲስ ፈጠራ ያላቸውና ሥራቸው ወደ ገቢ መቀየር የሚችሉ ወጣቶች በውጭ ሀገራት ለተለያዩ አገልግሎቶች ክፍያ በሚጠየቁበት ወቅት በባንኮች በኩል መንግሥት በሚያመቻቸው አሠራር ክፍያ መፈጸም የሚችሉበት አማራጭ ይመቻቻል።

- በፈጠራ ላይ ለተመረኮዙ ቴክኖሎጂ መር ሥራ ፈጣሪዎች በጉምሩክ አሠራር ሂደት የሚያጋጥሙ ክፍያዎችን የሚቀንስና የጉምሩክ ድጋፍ የሚያገኙበት ማዕከል ይቋቋማል።

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል ፥ " ወጣቶች እንደሀገር የተመቻቸላቸውን ዕድል በመጠቀም ሃሳባቸውን አውጥተው ሥራ ላይ ማዋልና የተሻለ ገቢ ማግኘት አለባቸው " ብለዋል። #ኢፕድ

@tikvahethiopia
#ATTENTION🚨

" አንዳንድ ወጣት ሴቶች ከቫይረሱ በላይ #እርግዝናን_ይፈራሉ "

ስለኤች አይቪ/ኤድስ ስርጭት የሚሰጠው የግንዛቤ ፈጠራ ሥራ ከጊዜ ወደጊዜ እየተቀዛቀዘ መሆኑን በጤና ሚኒስቴር የኤች አይቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ገልጿል።

ችግሮች ከመባባሳቸው በፊት ትኩረት ሰጥቶ መሥራት እንደሚገባ አሳስቧል።

ቫይረሱ ኢትዮጵያ መግባቱ ከተረጋገጠበት ጊዜ አንስቶ በተሰራው እንቅስቃሴ ብዙ ለውጦች መመዝገባቸውን አስታውሷል።

ይሁን እንጂ የተመዘገቡት ለውጦች በተወሰነ ደረጃም ቢሆን መዘናጋት እንደፈጠሩ ፤ የሚዲያዎች ተሳትፎም መቀዛቀዙን ጠቁሟል።

በአሁኑ ወቅት ኤች አይ ቪ ቫይረስን በተመለከተ እየተሠሩ ያሉ ሥራዎች ትኩረት የሚሹና በይበልጥ ተጋላጭ የሆኑ የማኅበረሰብ ክፍሎች ላይ ብቻ ትኩረት ያደረጉ ናቸው ብሏል።

እነዚህም ፦
- ሴተኛ አዳሪዎች፣
- አደንዛዥ እፅ የሚጠቀሙ ሰዎች፣
- የረጅም ርቀት አሽከርካሪዎች፣
- አፍላ ወጣቶች በተለይ (ከማኅበራዊ ሚዲያ ጋር በተያያዘ)፣
- የቀን ሠራተኞች፣
- ከማኅበራዊ ችግሮች ጋር ተያይዞ ተጋላጭ የሆኑት እንደሆኑ አመልክቷል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ የስርጭት መጠኑ ከ1 በመቶ በላይ ቢሆንም ከቦታ ቦታ በፆታ፣ በኅብረተሰብ ክፍል፣ በገጠርና በከተማ ከፍተኛ ልዩነት አለው ብሏል።

በከተሞች ያለው ስርጭት በገጠር ካለው በሰባት እጥፍ እንደሚበልጥም ጠቁሟል።

ይህንን ልዩነት መሠረት ያደረገ አጠቃላይ ማኅበረሰቡን ተደራሽ የሚያደርግ የግንዛቤ ፈጠራ ሥራ እየተከናወነ አይደለም ብሏል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ፦
° የመጠጥ ቤቶች ፣
° የጫት ቤቶች
° በሺሻ ቤቶች መስፋፋት ሌላ ተግዳሮቶች እየሆኑ መምጣታቸውን ገልጿል።

" አንዳንድ ወጣት ሴቶች ከቫይረሱ በላይ እርግዝናን ይፈራሉ። የወጣቶች አዲስ የመያዝ ምጣኔ ጨመረ ባይባልም እየቀነሰ አይደለም፤ ይህ በራሱ ችግር ለመኖሩ አመላካች ነው "ም ብሏል።

በተለይ በወጣቶች በኩል ሁሉን አቀፍ ሥራ ባለመሠራቱ እንደ ሀገር ዋጋ ሊያስከፍሉ የሚችሉ አጋላጭ ባሕሪያት እየተስተዋሉ መሆኑን አመልክቷል።

የኤች አይ ቪ ቫይረስን በተመለከተ ጠንካራ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን እንደሀገር ማከናወን እንደሚጠበቅ አሳስቧል። #ኢፕድ

@tikvahethiopia