TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ቦዴፓ

የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ቦዴፓ) በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ልኮልናል።

ፓርቲው በላከልን መግለጫ እስካሁን ትጥቃቸውን ያልፈቱ የጉህዴን ታጣቂዎች በመተከል ዞን ማንዱራ ወረዳ ግልገል በለስ ከተማ ሰኔ 30 ቀን 2015 ዓ/ም በፈፀሙት ጥቃት በርካታ ንፁኃን ዜጎች መገደላቸውና በርካቶች መቁሰላቸውን ገልጿል።

ድረጊቱ በየትኛውም መመዘኛ ተቀባይነት የለለው አስነዋሪና አሳፋሪ መሆኑን በመግለፅ አውግዟል።

በንፁሀን ዜጎች  ላይ ይህን የመሰለ ወንጀል የፈጸሙ አካላት በአፋጣኝ ለህግ እንዲቀርቡ ፓርቲው አጥብቆ ጠይቋል።
 
ከዚህ በተጨማሪ እነዚህ የታጣቂ  ቡድን አባላት በመተከል እና ከማሽ ዞኖች  ትጥቅ ሳይፈቱ በከተሞችና በገጠር ቀበሌዎች በመንግስት ሎጀስትክስ  እየተንቀሳቀሱ በሰላማዊ ዜጎች ላይ ስጋት እየፈጠሩ ይገኛሉ ሲል አሳውቋል።

ፓርቲው ወቅታዊ የሆነውን ክልላዊ ሁኔታን በማስመልከት ፦

- የመተከልን ህዝብ ማህበራዊ  እረፍት በመንሳት ቀጠናውን የጦረነት ማዕከል ለማድረግ የሚሰሩ አካላት ከድርጊታቸው እንድቆጠቡ ፤ አረሶ አደሩን ለማስራብ በማለም የእርሻና የምርት ወቅት በመጠበቅ የሚደረግ አመራር ፈጠር  ግድያ በእጅጉ እንደሚያወግዝ ገልጿል።

- ጥቅምት 9 ቀን 2015 ዓ/ም ከጉህዴን ጋር የክልሉ መንግስት በደረሰው ስምምነት መሰረት የታጠቁ የጉህዴን ኃይሎች ተሃድሶ ስልጠና ከወሰዱ በኃላ ትጥቅ ፈተው ወደ ህብረተሰቡ ይቀላቀላሉ ቢባልም ትጥቅ ሳይፈቱ ማህበረሰቡ ውስጥ የሚያደረጉት እንቅስቃሴ በተለይም የመንግስት የፀጥታ አካላትን ሚና #ተክተው የሚያደረጉት እንቅስቀሴ በአስቸኳይ እንዲቆምና ትጥቅ በአስቸኳይ እንዲፈቱ አሳስቧል።

- በመተከል ዞን ውስጥ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ አጀንዳቸውን በኃይል ለማስፈጸም የሚታትሩ #የውስጥ እና #የውጭ ሃይሎች ከድረጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስቧል።

- ሰሞኑን በግልገል በለስ ከተማ በዜጎች ላይ የተፈፀመውን ዘግናኝ ግድያና ከድርጊቱ ጀርባ ያሉ አካላትን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን፣ የክልሉና  የፌደራል ፖሊስ በማጣራት አጥፊዎችን ለህግ እንዲያቀርቡና ለህዝቡ ይፋ እንዲያደረጉ ጠይቋል።

- የክልሉ መንግስት በሰላም ውስጥ ልማትን ማሰብና መፈፀም የማይችሉ፣ በግጭት ውስጥ በህዝብ ደም በስልጣን ላይ ለመኖር የሚፈልጉ ሀሳብና ውጤት አልባ ጊዜ ያለፈባቸው አመራሮችን በአስቸኴይ በማጥራት እንዲያስተካክል ፓርቲው አሳስቧል።

(ከቦዴፓ የተላከው ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ይነበብ

ትምህርት ሚኒስቴር በሀገሪቱ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ተግባራዊ ማድረግ ከጀመራቸው ስራዎች አንዱ የሆነ የተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ከነገ ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ/ም ይጀምራል።

በዚህ ፈተና ወቅት ከተማሪዎች እና ከፈታኞች ምን እጠበቃል ?

[ ከተፈታኞች የሚጠበቅ ]

- ተፈታኞች ወደ መፈተኛ ክፍላቸው ሲመጡ ማንኛውም አይነት ስልክ፣ ስማርት ሰዓት ፣ ታብሌት ፣ ላፕቶፕና ... ወዘተ ተመሳሳይ ኤክትሮኒክ ቁሳቁስ መያዝ በፍፁም የተከለከለ ነው።  (ይዞ የተገኘ ፈተናው /ውጤቱ ተሰርዞበት በቀጣይ ጊዜ እንዲቀመጥ ይደርጋል)

- ፈተና ከመጀመሩ ከ30 ደቂቃ በፊት መፈተኛ ክፍል መገኘት አለባቸው።

- ተፈታኞች ለፈተና ሲመጡ ID መያዝ ያለባቸው ሲሆን User Name እና Password lower-case and upper-case ፊደላትን ለይተው በጥንቃቄ መያዝ አለባቸው።

- ተፈታኞች ፈተና ከተጀመረ በኃላ ከ30 ደቂቃ በፊት ከፈተናው ክፍል መውጣት የለባቸውም።

- ተፈታኞች ፤ ፈተናውን የሚያስፈትኑ መምህራን በሚያሳዩት ቦታ ብቻ መቀመጥ አለባቸው።

- ሁሉም ተፈታኝ እንዲቀመጥ የተመደበበት የራሱ ኮምፒውተር ላይ ብቻ ተቀምጦ መክፈትና መጠቀም አለበት።

- በፈተና ክፍል ውስጥ መነጋገርም ሆነ ከቦታ ቦታ መዘዋወር በፍፁም የተከለከለ ነው። እንዲሁም ማንኛውም ተፈታኝ ከጎኑ ያለውን ተማሪ ኮምፒውተር በፍፁም ማየት የለበትም።

- ምንም ዓይነት ወረቀት ወደ መፈተኛ ክፍል ይዞ መምጣት አይቻልም።

- ተፈታኞች በምንም አይነት ሁኔታ መኮርጅም ሆነ ማስኮርጅ ተግባር ላይ ቢሳተፉ እርምጃ ይወሰድባቸዋል።

- ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች ለፈተናው ፈታኝ መምህራን እና ለአስተባባሪዎች መታዘዝ ያለባቸው ሲሆን የፈተናው ደንብና ስርዓት ተገዢ መሆን ይጠበቅባቸዋል።

NB. ሁሉም ተፈታኞች ወደ ፈተና መፈተኛ ክፍል ተፈትሸው እንዲገቡ የሚደረግ ሲሆን ማንኛውም ተፈታኝ ከፀጥታ ኃይሉ ጋር በፍተሻ ወቅት ይሁን ሥርዓት ለማስያዝ በሚደረግ እንቅስቃሴ እንቅፋት ሆኖ ከተገኘ ከመፈተኛ አከባቢ እንዲገለል ተደርጎ በቀጣዩ የመውጫ ፈተና መስጫ ወቅት እንዲቀመጥ ይፈቀድለታል።

[ ከፈታኝ መምህራን የሚጠበቅ ]

- የተፈታኝ ተማሪዎችን ID በአግባቡ በማረጋገጥ ወደ ክፍል እንዲገቡ ማደረግ ይጠበቅባቸዋል።

- ተፈታኝ ተማሪዎችን በሥም ዝርዝራቸው መሠረት ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል።

- ፈታኝ መምራህን የተፈታኝ ተማሪዎችን አቴንዳንሰ ይወስዳሉ ፤ ተማሪዎችን ፊርማ ያስፈርማሉ።

- በፈተና ክፍል ውስጥ ደምጽ እንዳይሰማ፣ ተማሪዎች ከቦታ ቦታ እንዳይዘዋወሩ ተገቢውን ቁጥጥር ማድረግ አለባቸው።

- የፈተናው አጠቃለይ ሂደት በትኩረት መከታተል አለባቸው።

- በህመም ምክንያት ተማሪዎች ከመተኛ ክፍል መውጣት ቢፈልጉ ከሱፐርቨዘር ጋር በመነጋገር አስፈላጊውን እርዳታ ያደርጋሉ።

- ተማሪዎች በጎናቸው ያለውን ሌላ ኮምፒውተር እንዳይመለከቱ መቆጣጠር አለባቸው።

- ተማሪዎች ፈተናው ከተጀመረ ከ30 ደቂቃ በፊት እንዳይወጡ መቆጣጠር ይጠበቅባቸዋል።

- ሲኮርጅ ወይም ሲያስኮርጅ የተገኘ ማንኛውም ተማሪ ከመፈተኛ ክፍል እንዲወጣ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።

- ፈተናው ከጀመረ ከ15 ደቂቃ በኃላ የሚመጣ ተማሪ እንዲገባ ማድረግ የላባቸውም።

- የፈተና አፈጻጸም ሪፖርት ለሱፐርቨዘር ማቅረብ ይጠብቅባቸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ነው የሰበሰበው።

ለመላው ተፈታኞች መልካም ፈተና ይሆን ዘንድ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይመኛል !

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

ቦረና ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ከያቤሎ ወደ ሻሸመኔ ሲያቀና ይርጋጨፌ ላይ በደረሰው የመኪና መገልበጥ አደጋ የሞቱ ተማሪዎቹ 2 (ሴቶች) መሆናቸውን አሳውቋል።

የዩኒቨርሲቲው የተማሪዎች ህብረት ቀደም ብሎ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መልዕክት ሶስት ሴቶች እና ሁለት ወንዶች በአደጋው ህይወታቸው መላፉን አሳውቆ ነበር።

ህብረቱ ፤ ቀደም ብሎ የደረሰው መረጃ 5 ተማሪዎቹ ህይወታቸው እንዳለፈ የሚገልፅ ሲሆን በኃላ በተደረገው የማጣራት ስራ ሶስቱ የተቋሙ ተማሪዎች እንዳልሆኑ ታውቋል።

የቦረና ዩኒቨርሲቲ በደረሰው አሳዛኝ አደጋ ወደ ቤተሰቦቻቸው የሚመለሱ 2 ሴት ተማሪዎቹ ህይወታቸው እንዳለፈና 12 ተማሪዎቹ እንደተጎዱ አስረድቷል።

በደረሰው አደጋ ጥልቅ ሀዘን እንደተሰማው የገለፀው ዩኒቨርሲቲው፤ ለሟች ቤተሰቦች መፅናናት ለተጎዱት ፈጣን ምሕረትን ተመኝቷል።

በሌላ በኩል ፤ ዛሬ በደረሰው አደጋ ከሞቱ 9 ሰዎች መካከል የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) አመራር አባሉ አቶ ሃምዛ ቦረና ወላጅ እናት ይገኙበታል።

ዘግይቶ የደረሰ ፦ ዛሬ ከሟቾች መካከል አንዲት ሴት የሪፍትቫሊ ዩኒቨርሲቲ አዳማ ካምፓስ ተማሪ እንደምትገኝበት ጓደኞቿ አሳውቀውናል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ይነበብ ትምህርት ሚኒስቴር በሀገሪቱ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ተግባራዊ ማድረግ ከጀመራቸው ስራዎች አንዱ የሆነ የተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ከነገ ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ/ም ይጀምራል። በዚህ ፈተና ወቅት ከተማሪዎች እና ከፈታኞች ምን እጠበቃል ? [ ከተፈታኞች የሚጠበቅ ] - ተፈታኞች ወደ መፈተኛ ክፍላቸው ሲመጡ ማንኛውም አይነት ስልክ፣ ስማርት ሰዓት ፣ ታብሌት ፣ ላፕቶፕና ... ወዘተ…
#ይነበብ2

የመውጫ ፈተና በሚሰጥባቸው ቀናት ከሚኖሩ ዲስፕሊንና እና ፕሮቶኮል መካከል ፦

- ከተፈቀደላቸው የዩኒቨርስቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ ለእለቱና ለዛ ፈተና ከተመደቡ አስተባባሪዎች፣ ለፈተናው ከተመደቡ ፈታኞች ውጭ የትኛውም አካል ወደ መፈተኛ ክፍል መግባት በጥብቅ የተከለከለ ነው።

- ፈተናው በኦንላይን ስለሚሰጥ የአይሲቲ ሙያተኞች በመፈተኛ ክፍሎች አቅራቢያ በመሆን ድጋፍ ይሰጣሉ፡፡

- የፀጥታ ሃይል ወደ መፈተኛ ክፍል እንዲገባ አስገዳጅ ሁኔታ ከተፈጠረ በማንኛውም ጊዜ ሊገባ ይችላል፡፡

- የዩኒቨርስቲ የበላይ ኃላፊዎችን ጨምሮ የትኛውም አካል በምንም ሁኔታ ስልክ፣ ስማርት ዋች፣ ታብሌት እና ተመሳሳይ ቁሶችን ይዞ ወደ መፈተኛ ክፍል መግባት አይችልም፡፡

- የአይሲቲ ሙያተኞች በመፈተኛ ክፍሎች የሚስጡት ድጋፍ ከትምህርት ሚኒስቴር ባልደረቦች ወይም ከዩኒቨርስቲው አመራር ድጋፍና አመራር ማግኘትን ስለሚያካትት በልዩ ሁኔታ በዩኒቨርስቲው ተመዝግቦ የሚያዝና የሚታወቅ ቁጥር ያለው ስልክ ይዘው ወደ መፈተኛ አዳራሽ እንዲገቡ ሊፈቀድ ይችላል፡፡

- በአንዳንድ ፕሮግራሞች #ካልኩሌተር ማምጣት ይፈቀዳል፡፡ በተጨማሪም በአንዳንድ ፕሮግራሞች ለማስልያ የሚረዳ ንፁህ ወረቀት በዩኒቨርሰቲዎች በኩል ሊፈቀድ ይችላል፡፡ ይህም ሆኖ ስልክ፣ ስማርት ዋች፤ ታብሌት እና ተመሳሳይ ቁሶችን እንደ ካልኩሌተር መጠቀም ፈፅሞ አይፈቀደም፡፡ ሥራ ላይ የሚውሉ ካልኩሌተሮች የተራቀቁና ፕሮግራ መብል እንዳይሆነ ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል፡፡

- በማንኛውም ወቅት ከተፈቀደላቸውና ለድጋፍ ከተመደቡ የአይ.ሲ.ቲ ባለሙያዎች በስተቀር የተፈታኙን መፈተኛ ኮምፒውተር መንካት በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡

(ተጨማሪ ከላይ ያንብቡ)

በድጋሚ መልካም ፈተና !

@tikvahethiopia
#coop

👉🏼 @coopbankoromia
የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክን የቴሌግራም ቻነል በመቀላቀል የሚከተሉትን ያግኙ!
- የባንክ መረጃዎች
- የፋይናንስ ግንዛቤ
- የባንኩን የሥራ ማስታወቂያዎች 🔎
- የውድድር ተሳትፎና ስጦታዎች 🎁
t.me/coopbankoromia
#ኤክሶደስ

በኤክሶደስ የፊዚዮቴራፒ ስፔሻሊቲ ክሊኒክ የምንሰጣቸው የህክምና አገልግሎቶች ፦
- ለአንገት፣ ለትክሻ፣ ለወገብ ህመም ፣ ከዲስክ መንሸራተት ጋር በተያያዘ ለሚመጣ   ችግር
- ለማዞር ወይንም ሚዛን የመጠበቅ ችግር፣ ለፊት መጣመም፣ ከስትሮክ በኋላ ለሚመጣ ግማሽ የሰውነት ክፍል መዛል
- ለስፖርታዊ ጉዳቶች፣ ከህፃናት የእድገት ውስንነት ጋር በተያያዘ ለሚከሰቱ የእንቅስቃሴ ችግሮች
- በአጠቃላይ ከነርቭ፣ ከጡንቻ፣ ከመገጣጠሚያ ጋር በተገናኘ ለሚከሰቱ ችግሮች መፍትሄ ያግኙ ይዳኑ!

የስራ ሰዓት ዘወትር ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ከጠዋቱ 2:30 እስከ #ምሽት 1:00 ሰዓት፤ አድራሻችን 22 ከመክሊት ህንፃ ፊት ለፊት ባሮ ህንፃ ላይ እንገኛለን። ስልክ ቁጥር 0979099909/ 0911039377
  √በቴሌግራም ቻናላችን ጠቃሚ መረጃ ያግኙ
https://publielectoral.lat/ExodPhysioClinic
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የሚመራ የልዑካን ቡድን ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም ወደ ትግራይ ርዕሰ ከተማ መቐለ ይጓዛል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ባስተላለፈው ውሳኔ መሰረት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የሚመራ 13 አባላት ያሉት የልዑካን ቡድን ሐምሌ…
#መቐለ

በቅዱስ ፓትርያርኩ የሚመራ ልዑካን ቡድን መቐለ ገብቷል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ለክልል ትግራይ የሰብዐዊ ድጋፍ እንዲደረግና ቅዱስ ፓትርያርኩና ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በትግራይ ክልል ከሚገኙ ብፁዓን አባቶች ጋር የሰላም ውይይት እንዲያደረጉ ውሳኔ ማስተላለፉ ይታወሳል።

በዚህ መሰረት የልዑካን ቡድን ዛሬ ክልል ትግራይ መቐለ ከተማ ገብቷል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#መቐለ በቅዱስ ፓትርያርኩ የሚመራ ልዑካን ቡድን መቐለ ገብቷል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ለክልል ትግራይ የሰብዐዊ ድጋፍ እንዲደረግና ቅዱስ ፓትርያርኩና ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በትግራይ ክልል ከሚገኙ ብፁዓን አባቶች ጋር የሰላም ውይይት እንዲያደረጉ ውሳኔ ማስተላለፉ ይታወሳል። በዚህ መሰረት የልዑካን ቡድን ዛሬ ክልል ትግራይ መቐለ ከተማ ገብቷል። @tikvahethiopia
ፎቶ ፦ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና የሰላም ልኡካኑ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ከአቶ ጌታቸው ረዳ ጋር በመቐለ አሉላ አባ ነጋ ኤርፖርት ተገናኝተዋል።

Credit : EOTC TV

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና የሰላም ልኡካኑ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ከአቶ ጌታቸው ረዳ ጋር በመቐለ አሉላ አባ ነጋ ኤርፖርት ተገናኝተዋል። Credit : EOTC TV @tikvahethiopia
ልዑካን ቡድኑ በመቐለ የሚኖረው ቆይታ ምን ይመስላል ?

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የተመራ የኢትዮጵያ ኦሮቶዶክሳዊት ቤተክርስትያን ሲኖዶስ ልኡክ ዛሬ ጥዋት መቐለ ገብቷል።

ቆይታው ለሁለት ቀን ይሆናል። 

ለልዑኩ በመቐለ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፍያ አቀባበል ተደርጓል።

ቀጥሎ በመቐለ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስትያን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የተመራ ፀሎት ይከናወናል።

በመቀጠል ቅዱስ ፓትርያርኩ ወደ ትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፅህፈት ቤት በመጓዝ ከሲኖዶስ የተላከ ሰብአዊ እርዳታ ካስረከቡ በኋላ አጭር ውይይት ይካሄዳል።

ውይይቱ በጦርነቱ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የኢትዮጵያ እና የትግራይ አብያተ ክርስትያናት አባቶች አንድነት መቀጠልና ማጠናከር ላይ ያተኩራል።

ከውይይቱ በኋላ በጦትነቱ ምክንያት የተፈናቀሉ ወገኖች በተጠለሉበት በተለምዶ በመቐለ 70 ካሬ ተብሎ የሚጠራው ቦታ ጉብኝት ይካሄዳል።

ጉብኝቱ ተፈናቃዮቹ በቀጣይ እንዲቋቋሙ የኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስትያን አስተዋፅኦ ምን መሆን እንዳለበት የሚያመላክት ሆኖ አጭር ቡራኬና መግለጫ በቅዱስ ፓትርያርኩ ይቀርባል።

ቀጥሎ ከትግራይ ብፁአን አበውና የኦርቶዶክሳዊ ቤተክርስተያን አመራሮች ግንኙነትና ውይይት ይካሄዳል።

በቦታው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ሃይማኖታዊ አስተምህሮና ምክር ይሰጣል።

የዛሬ የሰኞ ሃምሌ 3 /2015 ዓ.ም ጉብኝት ማጠቃለያ በዚህ ይሆናል።

ነገ ማክሰኞ ሃምሌ 4 /2015 ዓ.ም ጥዋት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የጉብኝቱ ዓላማና ቆይታ የሚመለከት ለጊዚያዊ አስተዳደሩ አመራሮችና ለብፁአን አበው መግለጫ ያቀርባሉ።

መግለጫው ተከትሎ ውይይት ከተካሄደ በኋላ ጉብኝቱ ይጠናቀቃል።

ከጉብኝቱ ማጠቃለያ በኋላ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የሚመራው ልኡክ ወደ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፍያ ሽኝት ይደረግለታል።

መረጃው የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ አባል ነው።

@tikvahethiopia