TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Amhara

በአማራ ክልል ከመንግሥት የፀጥታ ኃይል ጋር የትጥቅ ትግል እያደረጉ የሚገኙት እና ታጥቀው የሚንቀሳቀሱት እነ ምሬ ወዳጆን ጨምሮ 27 ተከሳሾች #የጋዜጣ_ጥሪ እንዲደረግላቸው እና እንዲቀርቡ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ መስጠቱ ተሰማ።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ የህገ መንግስትና በህገ መንግስት ስርዓት ላይ የሚፈጸሙ የወንጀል ጉዳዮችን የሚመለከተው ችሎት ፤ በሽብር ወንጀል በተከሰሱት እነ ዶክተር ወንደሰን አሰፋ መዝገብ ተካተው ያልቀረቡ ተከሳሾች የጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግላቸውና ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ማዘዙን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

የጋዜጣ ጥሪ ይደረግላቸውና ይምጡ የተባሉት በአሁን ሰዓት ነፍጥ አንግበው በአማራ ክልል እየተንቀሳቀሱ የሚገኙት ምሬ ወዳጆን ጨምሮ 27 ተከሳሾች ናቸው።

እነ ዶክተር ወንደሰን አሰፋ እና መስከረም አበራን ጨምሮ 23 ተከሳሾች በአማራ ክልል ካለው ሁኔታ ጋር በተያያዘ ታስረውና " በሽብር ወንጀል " ተከሰው የፍርድ ሂደታቸው እየታየ እንደሆነ ይወቃል።

@tikvahethiopia