TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
ሸዋሮቢት ውስጥ የሰውም ሆነ የባጃጅ እንቅስቃሴ ላይ ገደብ ተጥሏል። የከተማው አስተዳደር ፤ ለከተማው ሰላምና ጸጥታ ሲባል ማንኛውም የባጃጅና የሰው እንቅስቃሴ ከምሽቱ 12 ስዓት ጀምሮ የተከለከለ ነው ሲል አሳውቋል። ለተላለፈው ትዕዛዝ ሁሉም ትብብር እንዲያደርግ ከተማ አስተዳደሩ ጥሪ አቅርቧል። ከሰሞኑን በዚሁ ቀጠና ዳግም ግጭት ተቀስቅሶ በርካቶች የደህንነት ስጋት ላይ ወድቀዋል። @tikvahethiopia
ፎቶ ፦ የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር ፤ " ሰሞኑን በሸዋሮቢት እና በጅሌ ጥሙጋ ወረዳ አዋሳኝ አካባቢዎች በተደረገ ጦርነት በርካታ የሰው ህይወት ጠፍቷል፤ ንብረትም ውድሟል " ሲል አሳውቋል።

የንብረት ውድመት የደረሰባቸው የከተማው የ05 ቀበሌ ነዋሪዎች #በመንግስት_ቸልተኝነት እና #የላላ_ህግ የማስከበር ተግባሩ የተነሳ በየአመቱ ለሰው ህይወት መጥፋትና ንብረት ውድመት ምክንያት መሆኑን ገልጸዋል።

ነዋሪዎቹ ፤ ውፍጮ ቤቶችና የንግድ ሱቆች ሙሉ በመሉ መውደማቸውን በመግለጽ መንግስት በዚህ ቀጠና ያለውን ጦርነትና የተደራጀ ቡድን ወይም  ኃይል በማጥራት የመንግስት ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል ብለዋል።

ከሰሞኑን በደረሰው ጥቃት በርካታ ሰው ህይወት የጠፋ ሲሆን የህዝብ መገልገያ ትምህርት ቤቶች ፣ ወፍጮ ቤቶች ፣ የጤና ክሊኒኮች ፣ ሱቆች ፣ የቀበሌ አስተዳደር ቢሮዎች ፣ የግለሰብ ቤቶች ወድመዋል።

ነዋሪዎች የሚመለከተው የበላይ የመንግስት አካል ልዪ ትኩረት ሰጥቶ ህይወታችንን ሊታደግ ይገባል ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

Photo Credit : የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር

@tikvahethiopia