TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ፌደራል ፖሊስ⬇️

በሶማሌ ክልል በተከሰተው ቀውስ በአንድ ቀን 96 ሰዎች መገደላቸውን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል #ዘይኑ_ጀማል ለቢቢሲ ገልፀዋል።

ሰዎቹ የተገደሉት ቀውሱ በተነሳበት የመጀመርያው ቀን #ሐምሌ 27፣ 2010 ዓ. ም. ሲሆን፤ በሶማሌ ክልል ዋና ከተማ ጅግጅጋን ጨምሮ በክልሉ የተለያዩ ከተሞች #ግድያው መፈጸሙን ተናግረዋል።

ሰዎቹ የተገደሉት #በአሰቃቂ ሁኔታ መሆኑን ተናግረው፤ ሀይማኖትና ብሔርን ለይቶ የተሰነዘረ ጥቃት እንደሆነ አክለዋል።

"ከዘር #ጭፍጨፋ አይተናነስም" ብለዋል። መነሻው የክልሉ አመራሮች አቅደው፤ ተግባሩን የሚፈጽሙ ሰዎች አሰልጥነውና አሰማርተው መሆኑን ኮሚሽነሩ ገልጸዋል።

እስከ አሁን የክልሉን የቀድሞ ፕሬዘዳንት አቶ አብዲ ሞሀመድ ኡመርን ጨምሮ ሰባት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ተናግረዋል።

'ሄጎ' በመባል የሚታወቀው ቡድን በግድያው እጁ ስለመኖሩ ቢቢሲ ላቀረበላቸው ጥያቄ፤ "በዋናነት በግጭቱ ተሳትፈዋል የሚባሉት #ሄጎ በሚባለው ቡድን አባላት ናቸው። ሄጎ የሚባለውን #የፈጠሩ፣ እቅዱን ያቀነባበሩ የክልሉ የፖለቲካ #አመራሮች፣ የክልሉ የካቢኔ አባላትና ሌሎች የመንግስት ከፍተኛ #ባለስልጣኖችን በቁጥጥር ስር የማዋል ስራ እየሰራን ነው" ብለዋል።

ልዩ ፖሊስ በግድያው ተሳትፎ ስለመሆኑ ከቢቢሲ ለቀረበላቸው ጥያቄ "ማን በምን ደረጃ ተሳተፈ የሚለው ተጣርቶ ለህዝብ ይፋ ይደረጋል" ሲሉ ኮሚሽነሩ አስረድተዋል።

በጅግጅጋ የሚኖሩ የተለያዩ አካባቢዎች ተወላጆች ስጋት እንዳላቸው የሚናገሩት ጄኔራል ዘይኑ፤ የፌደራል ፖሊስና የመከላከያ ሰራዊት የክልልሉን ዋና ዋና ከተማዎች መቆጣጠሩ አንጻራዊ ሰላም ማስፈኑን ገልጸዋል።

በአሁን ወቅት አዲሱ የክልሉ ፕሬዘዳንት አቶ ሙስጠፋ ኡመር በተለያዩ አካባቢዎች እየተዘዋወሩ ህብረተሰቡን እየጎበኙ መሆኑን ተናግረዋል።

የተፈናቀሉ ሰዎችን ወደ አካባቢው መመለስ ቀጣዩ ስራ መሆኑን ተናግረው፤ በዚህ ረገድ የአካባቢው ማህበረሰብ እየተባበራቸው እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

ምንጭ፦ ቢቢሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
ኤርዶጋን ምን አሉ ?

የቱርክ ፕሬዝዳንት ሪሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን በእስራኤል እና ፍልስጤም ግጭት ዙሪያ ይህን ብለዋል ፦

- በሲቪሎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ወይም በሲቪል አካባቢዎች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ትክክል አይደለም፤ አንቀበለውም።

- በእስራኤል ግዛት በሰላማዊ ዜጎች ላይ የሚደርሰውን ግድያ እንቃወማለን።

- በጋዛ ውስጥ ንጹሃን  ያለየ ' #ጭፍጨፋ ' በፍጹም አንቀበልም።

- አሳፋሪ ዘዴዎችን በመጠቀም የሚካሄደው ግጭት ፣ ጦርነት ሳይሆን ' ጭፍጨፋ ' ነው።

- ማንኛውም አካል ፍልስጤማውያንን 🇵🇸 ለመቅጣት ዓላማ ካላቸው ውሳኔዎች መራቅ አለበት።

- ሽምግልና እና ፍትሃዊ ዳኝነትን ጨምሮ የምንችለውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ ነን።

በእስራኤል እና በፍልሥጤሙ ሃማስ መካከል ቅዳሜ የጀመረው ደም አሳፋሽ ግጭት ዛሬም ቀጥሎ የዋለ ሲሆን ሃማስ ወደ ቴላቪቭ እና ማዕከለኛው እስራኤል ሮኬቶችን ሲያስወነጭፍ ውሏል።

እስራኤል የምትወስደውን የአስፀፋ እርምጃ አጠናክራ ቀጥላለች። ሠራዊቷን ጋዛ ድንበር ላይ በማከማቸት ላይ እንደሆነችና የምድር ጥቃት ሊደረግ እንደሚችል እየተጠበቀ ይገኛል። የእስራኤል ጦር ቃል አቀባይም ወደ " ጋዛ ለመግባት ዝግጅት ላይ ነን " ማለታቸው ተዘግቧል።

በጦርነቱ ሌሎች ኃይሎች እንዳይሳተፉበት ተሰግቷል ፣ የሊባኖሱ ሄዝቦላህ " አሜሪካ እስራኤል የምትፈፅመው ጥቃት አጋር ናት " ያለ ሲሆን ለሚፈፀመው ግድያ፣ ወንጀል እና ጋዛ ላይ ለተደረገው ከበባ ተጠናቂነት አለባት ብሏል።

#አሜሪካ እና አጋሮቿ የ " ሂዝቦላህ " የታጠቀ ኃይልን " ከእስራኤል ጋር ጦርነት ውስጥ ለመግባት አትሞክር አርፈህ ተቀመጠ " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

የየመኑ " ሁቲ ኃይል " አሜሪካ በቀጥታ ጦርነቱ ላይ ወታደራዊ ተሳትፎ ካደረገች ከወንድሞቻችን (ሃማስ) ጋር በመሆን ጦርነቱን እንቀላቀላለን በሚሳኤል እና ድሮን እንዲሁም በሌሎች አመራጮች የታገዘ ጥቃት እስራኤል ላይ እንከፍታለን ሲሉ ዝተዋል።

More 👉 @BirlikEthiopia

https://publielectoral.lat/+LM-bJ8NzZMcxMjA8