TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ሀዋሳ-ወቅታዊ ጉዳይ⬇️

ያልተጣራ ወሬ በህዝቦች መካከል ጥርጣሬ እንዲፈጠር ያደርጋል።

ከተማችን ሀዋሳ በርካታ ብሄሮችና ብሄረሰቦች #ተቻችለው እና #ተከባብረው የሚኖሩባት እንደሆነ ማንም የሚያውቀው ሀቅ ነው።

ይሁንና በቅርቡ በከተማው የተከሰተውን የፀጥታ ችግር መነሻ በማድረግ በከተማው ነዋሪዎቾ መካከል #ጥርጣሬ እና #አለመደማመጥ እንድፈጠር እንዲሁም ለዘመናት የከተማችን እሴቶች የሆኑት መከባበርና መቻቻል እንድሸረሸሩ እኩይ አላማ ያላቸው ግለሰቦች የተለያዪ የውሸት መረጃዎችን በማህበራዊ ገፅ ላይ እየለቀቁ እንዳሉ መረጃዎች ያሳያሉ።

ለአብነትም በ13/12/2010 በሀዋሳ ከተማ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን የጫነ ተሽከሪካሪ ተይዟል ተብሎ የተለቀቀው #የሀሰት ወሬ እንደሆነ #ከፓሊስ የተገኘ መረጃ ያሳያል።

#እውነታው የተያዘው ተሽከሪካሪ 15 ቦንዳ በህገ ወጥ መልኩ /ኮንትሮባንድ/ የገባ እቃ የጫነ እንደሆነ የተረጋገጠ ሲሆን ሌላው በህገ ወጥ መልኩ የተገነቡ ቤቶችን ለማፍረስ የተንቀሳቀሱ ፖሊሶች ተገደሉ ተብሎ የተለቀቀው ፎቶግራፍ የጥፋት ሀይሎች አቀነባብረው የለቀቊት
#የሀሰት_መረጃ እንደሆነ ለመጠቆም እንወዳለን።

በመጨረሻም የከተማችን #ፀጥታ እና #ሰላም እንዳይደፈርስ እንዲሁም በከተማው ህዝብ መካከል ጥርጣሬና አለመተማመን እንዳይፈጠር በዚህ በውሸት መረጃ ህብረተሰቡን በስጋት ላይ የሚትጥሉ አካላት #ከእኩይ ዲርጊታችሁ እንድትታቀቡ እያለ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር #ያሳስባል

የከተማችን ህዝብ በማህበራዊ ገፅ የፌክ አካውንት የከፈቱ አካላት በየጊዜው በሚያሰራጬት #የአሉባልታ ወሬ #እንዳይሸበር እናስታውቃለን።

©አቶ ደስታ ዶጊሶ #ሼር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ‼️

ማሳሰቢያ፦

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የ2011 ዓ.ም የመደበኛ ተማሪዎች ቅበላ ከጥቅምት 10 እስከ 14/2011 ዓ.ም ድረስ ማካሄዱ ይታወሳል፡፡

ዩኒቨርሲቲው የምዝገባ ስርዓቱን አጠናቆ መደበኛ የመማር ማስተማር ሂደት ውስጥ የገባ ሲሆን ለሠላማዊ የመማር ማስተማር መስፈን ከውጫዊና ውስጣዊ ባለድረሻ አካላት ጋር በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል፡፡

ነገር ግን ዩኒቨርሲቲው በሚገኝበት አካባቢ ምንም አይነት የፀጥታ እና የደህንነት ስጋት ሳይኖር ተማሪዎችን ሆን ብሎ ለማወክና በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ውስጥ #ረብሻ እንደተከሰተ ተደርጎ በማህበራዊ ድረ ገፅ #እየተወራ ይገኛል፡፡

በመሆኑም ይህ መሰረተ ቢስ #ወሬ እንደ ሆነ ታውቆ ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች አንዳች #ስጋት እንዳይገባቸሁ ተቋሙ #ያሳስባል፡፡

መደበኛ የመማር ማስተማር ስራው ሳይስተጓጎል ተጠናክሮ እንዲቀጥል ባለድርሻ አካላት የተለመደ ትብብራቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ እና አስፈላጊውን ትብብር ሁሉ እንዲያደርጉ ዩኒቨርሲቲው ያሳስባል፡፡

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ
ጥቅምት 23/2011 ዓ.ም.
@tsegabwolde @tikvahethiopia