TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
#Update

የእስራኤል እና የፍልስጤም ሃማስ ጉዳይ ወዴት ያመራ ይሆን ?

በእስራኤል እና በፍልስጤም ሃማስ መካከል እየተካሄደ ያለው ጦርነት እየተባባሰ መጥቷል።

ሀገራት የተለያዩ አቋማቸውን እያንፀባረቁ ይገኛሉ።

#ኢራን ፍልስጤም እና እየሩሳሌም ነፃ እስኪወጡ " ከፍልስጤም ተዋጊዎች ጎን ነኝ " ብላለች። #አሜሪካ በበኩሏ ከእስራኤል ጎን እንደሆነች ገልጻ የማያወላዳ ድጋፏን እንደምታደርግ አሳውቃለች።

የሁለቱ ሀገራት ጎረቤቶች ሁኔታውን በእንክሮ እየተከታተሉ በተጠንቀቅ ላይ ይገኛሉ።

ይህ ሁኔታ በዚህ ከቀጠለ ዓለም አቀፍ ይዞታን ሳይዝ እንደማይቀር ተሰግቷል።

ከመሸ የተሰሙ አዳዲስ መረጃዎች ምንድናቸው ?

- እስራኤል ጋዛ ላይ እየወሰደች ባለው የአፀፋ እርምጃ 232 ፍልስጤማውያን ሲገደሉ፣ 1697 ቆስለዋል ፤ በርካቶች ለህይወታቸውን የሚያሰጋ ጉዳት ላይ ናቸው።

- ሃማስ ባካሄደው ወታደራዊ ኦፕሬሽን የተገደሉ እስራኤላውያን ቁጥር ወደ 200 ማሻቀቡ ተሰምቷል።

- እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ውስጥ የኃይል አቅርቦት በማቋረጧ ሆስፒታሎች ተጎጂዎችን ለማከም እየተፈተኑ ይገኛሉ ተብሏል። በጋዛ ኤሌክትሪክ እንዲቋረጥ ያዘዘው የእስራኤል ኢነርጂ ሚኒስቴር ነው።

- ፍልስጤም ፤ አንድ የ13 ዓመት ልጅን ጨምሮ 4 ፍልስጤማውያን በ " ዌስት ባንክ ' በእስራኤል ወታደሮች መገደላቸውን አሳውቃለች።

- የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላ ኻሚኒ አማካሪ ያህያ ራሂም ሳፋቪ " የፍልስጤም ተዋጊዎች በእስራኤል ላይ ከዓመታት በኋላ ትልቁን ጥቃት በማድረሳችሁ እንኳን ደስ አላችሁ " ብለዋል።  " የፍልስጤም ተዋጊዎችን እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን። " ያሉት አማካሪው " ፍልስጤም እና እየሩሳሌም ነፃ እስኪወጡ ድረስ ከፍልስጤም ተዋጊዎች ጎን እንቆማለን። " ብለዋል። ኢራን የሃማስን ኦፕሬሽን " የሚያኮራ " ብላለች።

- ሃማስ በእስራኤል ላይ ከፈትኩ ያለውን ኦፕሬሽን ተከትሎ ከኢራን፣ ቴህራን ከፍተኛ የሆነ ደስታን የሚገልጹ ቪድዮዎች ወጥተዋል። በቪድዮዎቹ ቴህራን ውስጥ ርችት ሲተኮስ እና ሰዎች ደስታቸውን ሲገልጹ ይታያል (ቪድዮ ከላይ ተያይዟል)።

- አሜሪካ በዚህ ወቅት ከእስራኤል መንግሥት እና ህዝብ ጋር መሆኗን በመግለፅ የማያወላዳ ድጋፏን እንደምታደርግ አሳውቃለች። የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ተኩስ እንዲቆም ጠይቃለች። ቱርክ በንፁሃን ሞት ማዘኗን ገልጻ ግጭቱ ወደ ቀጠናው ሳይስፋፋ እንዲበርድ ድጋፏን እንደምታደርግ አሳውቃለች።

- NATO አጋሬ ናት ባለው እስራኤል ላይ የተፈፀመው የአሸባሪዎች ጥቃት መሆኑን ገልጾ ከተጎጂዎች ጋር እንደሚቆም እስራኤልን እራሷን የመከላከል መብት እንዳላት ገልጿል።

- የፍልስጤም ፕሬዝዳንት ማህሙድ አባስ የፍልስጤም ህዝብ ከ " ሰፋሪዎች እና ወራሪ ወታደሮች ሽብር " እራሱን የመከላከል መብት አለው ብለዋል።

- የእስራኤል ትምህርት ሚኒስቴር ነገ በመላው ሀገሪቱ ትምህርት እንዲዘጋ መወሰኑ ታውቋል።

በእስራኤል እና ሃማስ መካከል ወታደራዊ ግጭቱ የተነሳው ሃማስ ድንገተኛ እና ባለፉት በርካታ አመታት ታይቶ የማይታወቅ የተቀናጀ ኦፕሬሽን እስራኤል ላይ ከጀመረ በኃላ ነው።

ሃማስ ጦርነቱ " ከወራሪ ጋር የሚደረግ ጦርነት ነው " ብሏል። ፍልስጤማውያን ባለፉት አስርት ዓመታት ውስጥ ለደረሰባቸው ግፍ ሁሉ ምላሽ ነው ሲልም ገልጿል።

የእስራኤል ሀገር መከላከያ ሚንስቴር " ሃማስ ከባድ ስህተት ሰርቷል ፤ ለዚህም የከፋ ዋጋ እንደሚከፍል እና ለውጤቱም ሙሉ ኃላፊነቱን ይወስዳል " ካለ በኃላ የአየር ጥቃቶችን ጨምሮ የአፀፋ እርምጃዎችን እየወሰደ ይገኛል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
#Update

• የሞቱ እስራኤላውያን ከ700 በላይ ሆነዋል። ከ350 በላይ ፍልሥጤማውያንም ህይወታቸው ጠፍቷል።

#ኢራን ፍልስጤምን ደግፋ ስትቆም ፤ #አሜሪካ ከእስራኤል ጎን መሆኗን አረጋግጣ ወታደራዊ ድጋፍ ማድረግ እንደምትጀምር አሳውቃለች።

በእስራኤል ጦርና በፍልስጤሙ ሃማስ መካከል ጦርነቱ ዛሬም ተባብሶ መቀጠሉን ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። በተለይም እስራኤል ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች ብርቱ ውጊያ እየተካሄደ ነው ተብሏል።

በጦርነቱ እስራኤል ውስጥ ከ700 በላይ #እስራኤላውያን መገደላቸው ተሰምቷል።

እስራኤል ተከፍቶብኛል ላለችው ጦርነት እየወሰደች ባለችው የአፀፋ እርምጃ በጋዛ ሰርጥ ከ350 በላይ #ፍልጤማውያን ተገድለዋል።

በአጠቃላይ ባለፉት ሰዓታት ብቻ እስካሁን ይፋ በተደረገው ከ1 ሺህ በላይ ሰዎች ሞተዋል።

በሺዎች የሚቆጠሩ ተጎድተዋል።

ጋዛ ውስጥ መሰረተልማቶች ፣ ህንፃዎች እንዳልነበሩ ሆነዋል፣ የኤሌክትሪክ ፣ የነዳጅና የፍጆታ እቃዎች አቅርቦት ተቋርጧል ፤ ያለው ሁኔታ እጅግ የከፋ ነው ተብሏል። ሰብዓዊ እርዳታ የሚገባበት መንገድ እንኳን የለም።

ይህ በእንዲህ እንዳለ እስራኤል የሊባኖሱ ሂዝቦላህ ከፍቶብኛል ላለችው ተኩስ በሊባኖስ በከባድ መሳሪያ የታገዘ ጥቃት ፈፅማለች።

ሂዝቦላም እስራኤል ላይ ተኩስ ስለመክፈቱ ኃላፊነቱን ወስዷል።

ተኩሱ የተከፈተው እስራኤል፣ ሊባኖስ እና ሶሪያ በሚወዛገቡበት ግዛት እና ሶስቱንም ሃገራት በሚያገናኛቸው የዶቭ ተራራ አካባቢ ነው።

እስራኤል የሊባኖስ ታጣቂ ሂዝቦላህ በውጊያው ውስጥ ጣልቃ እንዳይገባ አስጠንቅቃለች።

ሃማስ ፤ እስራኤል በወረራ ከያዘቻቸው ግዛቶች ለመጠራረግ ፍልስጥኤማውያን እንዲሁም ሌሎች አረቦች ትግሉን እንዲቀላቀሉ ጥሪ አቅርቧል።

እስራኤል ያለጥርጥር በበርካታ ግንባሮች ሊከፈት የሚችል ጦርነት ሊኖር እንደሚችል ነው እየታያት ያለው ተብሏል።

ምናልባትም ጦርነቱ የከፋ የሚሆነው ከፍተኛ ኃይል ያለውን የሊባኖሱን ታጣቂ ቡድን ሂዝቦላ መሳብ ከቻለ እንደሆነ ተነግሯል።

በእስራኤል እና የፍልስጤም ሃማስ ጦርነት ሀገራት የተለያዩ አቋማቸውን እያንፀባረቁ ሲሆን ኢራን የሃማስን ጥቃት ደግፋ ቆማለች።

ኢራን " የፍልስጤምን ሕጋዊ የመከላከል መብት እደግፋለሁ " ብላለች።

አሜሪካ በበኩሏ ከእስራኤል ጎን እንደሆነች በተደጋጋሚ እያረጋገጠች ነው ፤ ወታደራዊ ድጋፍም ለማድረግ እየተዘጋጀች መሆኑ ተሰምቷል። የአሜሪካ መከላከያ ድጋፉን ከዛሬ ጀምሮ የሚልክ ሲሆን በመጪዎቹ ቀናት ይደርሳል ተብሏል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የእስራኤል ጦር ከፍተኛ በሆነ ሁኔታ ወታደሮቹን እያሰማራ ሲሆን በጋዛ ላይ ተከታታይ የአየር ጥቃቶችን ከማድረግ በተጨማሪ የምድር ላይ ዘመቻ ለማድረግ ማቀዱን ተሰምቷል።

መረጃው ከቢቢሲ እና አልጀዚራን ጨምሮ ከሌሎች ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን የተገኘ ነው።

More - @BirlikEthiopia

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ኢራን

የኢራን ፕሬዝዳንት የሆኑት ኢብራሂም ራኢሲ ሲጓዙበት የነበረ ሄሊኮፕተር " #በአደገኛ_ሁኔታ " መሬት ላይ ማራፉን የኢራን መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

የሀገሪቱ ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ሂሊኮፕተሩ በአደገኛ ሁኔታ አርፎበታል ወደተባለበት ስፍራ ላይ አስቸጋሪ የአየር ሁኔታ እንዳለ ገልጿል።

የነፍስ አድን ሠራተኞች ወደ ቦታው ለመድረስ ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ ሲል አሳውቋል።

ፕሬዝዳንቱ ሀገራቸው ከአዘርባጀን ጋር በምትዋሰንበት አካባቢ የተገነቡ ሁለት ግድቦችን መርቀው ከከፈቱ በኋላ ወደ ሰሜን ምዕራቧ የአገሪቱ ከተማ ታብሪዝ እያመሩ ነበር።

ሄሊኮፕተሩ አርፎበታል በተባለው ስፍራ ላይ ባለው ከባድ ጭጋግ ምክንያት የነፍስ ማዳን ፍለጋ ሥራው አስቸጋሪ እንደሆነ ተነግሯል።

Credit - FARS

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#IRAN🇮🇷 የኢራኑ ፕሬዝዳንት እና አብረዋቸው የነበሩ ከፍተኛ ባለስልጣናት (የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩን ጨምሮ) እየተፈለጉ ነው። ህዝቡ መሪዎቹ ምንም ሳይሆኑ በህይወት ተርፈው ይመለሱ ዘንድ ፈጣሪውን እየለመነ ይገኛል። ፕ/ት ኢብራሂም ራኢሲ እና ሌሎች ባለስልጣናት ኢራን ከአዘርባጀን ጋር በምትዋሰንበት አካባቢ ላይ የተገነቡ 2 ግድቦችን መርቀው ከከፈቱ በኋላ በሂሊኮፕተር ወደ ታብሪዝ ከተማ ሲያመሩ ነው…
#ኢራን

የኢራን ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራይሲ ተሳፍረውባት በነበረው ሄሊኮፕተር በደረሰው አደጋ ህይወታቸው አልፏል።

ይህንንም የሀገሪቱ የመንግሥት አረጋግጧል።

ከሳቸው በተጨማሪ በሂሊኮፕተር ውስጥ አብረው የነበሩት የአገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆሴይን አሚር አብዶላሂያን እና ሌሎች በርካታ ሰዎች ሞተዋል።

ሮይተርስ በአደጋው ፕሬዚዳንቱ ሲጓዙባት የነበረችው ሄሊኮፕተር #ሙሉ_በሙሉ መቃጠሏን " አንድ የኢራን ባለስልጣንን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።

" የፕሬዜዳንት ኢብራሂም ራይሲ ሄሊኮፕተር በአደጋው ሙሉ በሙሉ ተቃጥላለች። በሚያሳዝን ሁኔታ ሁሉም ተሳፋሪዎች ሳይሞቱ አልቀሩም " ብለዋል ስማቸው ያልተጠቀሰው ባለስልጣን።

#ሮይተርስ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በኢራን የሂሊኮፕተር አደጋ የሞቱት እነማን ናችው ? - የኢራን ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ራይሲ - የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆሴን አሚር አብዶላሂያን - የተብሪዝ መስጂድ ኢማም አያቶላህ አልሃሸሚ - የምስራቅ አዘርባጃን ግዛት አስተዳዳሪ ማሊክ ራህማቲ - የፕሬዝዳንቱ ጥበቃ ኃላፊ ማሄዲ ሙሳቪ - የሄሊኮፕተሩ አብራሪ፣ - የሂሌኮፕተሩ ረዳት አብራሪ - ቦዲጋርድ - የበረራ አስተናጋጅ በትላንቱ የሂሊኮፕተር…
#ኢራን

" ...አሜሪካ በአቪየሽን ዘርፍ ላይ የጣለችው ማዕቀብ ለአደጋው መንስዔ ነው " - ሙሐመድ ጃቫር ዛሪፍ

የኢራን የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሙሃመድ ጃቫር ዛሪፍ ፣ የኢራን ፕሬዝዳንት እና ሌሎች ከፍተኛ የኢራን ባለስልጣናት ላይ ለደረሰው የሄሊኮፕተር አደጋ አሜሪካን ተጠያቂ አድርገዋል።

ሙሃመድ ጃቫር ዛሪፍ ፣ " #አሜሪካ በአቪየሽን ዘርፍ የጣለችው ማዕቀብ ለአደጋው መንስዔ ነው " ብለዋል፡፡

ከኢራን ብሄራዊ ቴሌቪዥን ጋር ቆይታ ደረጉት ዛሪፍ ፣ " ማዕቀቡ ኢራን #አዳዲስ የአቪየሽን ምርቶችን መግዛት እንዳትችል አድርጓታል " ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ጥሩ የሚባል ግንኙነት እንደሌላት ይታወቃል።

ትላንት የኢራን ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ራይሲ እና ሌሎች ባለልስጣናት ግድቦችን መርቀው ከከፈቱ በኋላ ወደ ታብሪዝ እያመሩ ሳሉ የነበሩበት ሂሊኮፕተር ከተራራ ጋር ተጋጭቶ ሁሉም ህይወታቸው አልፏል።

አደጋው በደረሰበት አካባቢ ላይ እጅግ አስቸጋሪ የአየር ሁኔታ እንደነበርም ተገልጿል።

More ➡️ @thiqaheth
#ኢራን

ኢራን በአስገድዶ መድፈር ወንጀል ጥፋተኛ የተባለን ወንጀለኛ በስቅላት ገድላለች።

በማዕከላዊ ኢራን " ዝድ ክልል "አስገድዶ መድፈር መፈጸሙ በፍርድ ቤት የተረጋገጠበት ግለሰብ ሞት ተቀጥቷል።

ግለሰቡ " በጥንቆላ ይተዳደራል " የተባለ ሲሆን ወደሱ የሚመጡ ሴቶችን በማታለል አስገድዶ ሲደፍር እንደነበር ተገልጿል፡፡

ከ12 በላይ የክስ መዝገቦች የተከፈቱበት ይህ ሰው አሱን ጨምሮ ከነ ረዳቱ ጥፋተኛ ሆነው ተገኝተው በሞት ፍርድ እንዲቀጡ ውሳኔ ተላልፎባቸዋል፡፡

በፍርድ ቤቱ ውሳኔ መሰረትም ጥፋተኛ የተባሉት ሰዎች ታንቀው እንዲገደሉ ተደርጓል።

ኢራን በአስገድዶ መድፈር ወንጀል ጥፋተኛ በተባሉ ወንጀለኞች ላይ ከባድ ቅጣት ከሚጥሉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት።

መረጃው የአን አይን ኒውስ / አል አረቢያ ነው።

@tikvahethiopia