TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ዶክተር_ተወልደብርሃን_ገብረእግዚአብሔር

የአካባቢ ጉዳይ ተመራማሪ ዶ/ር ተወልደ ብርሃን ገብረ እግዚአብሔር በ83 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

ዶክተር ተወልደ ብርሃን ገብረ እግዚአብሔር  ማን ነበሩ ?

- ከአባታቸው ቄስ ገብረ እግዚአብሔር ዮሐንስ እና ከእናታቸው ወ/ሮ መዓዛ ወልደመድህን በትግራይ ክልል፣ ዓድዋ  ርባገረድ መንደር በ1932 ዓ/ም ነው የተወለዱት።

- የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በንግስተ ሳባ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በዊንጌት ተምረዋል፤ 1959 ከፍተኛ ውጤት አምጥተው ወደ ቀዳማይ ኃላይለስላሴ ዩኒቨርሲቲ  / በኃላ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ገብተው ትምህርታቸውን ተከታትለዋል።

- በአካባቢ ጉዳይ ላይ ለዓለም የሚጠቅም ተጠቃሽ ሥራዎችን ሰርተዋል።

- በብዝሐ ሕይወት ፣ በማሕበረሰብ (የአርሶ አደሮችን መብት) ማስከበር እና በዘረመል ምሕንድስና በሚመረት እህል ላይ ያደረጓቸው ምርምሮች በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅናና ሽልማት አስገኝቶላቸዋል።

- ካገኟቸው ከዓለም አቀፍ ሽልማታቸው መካከል " የአማራጭ የኖቤል ሽልማት " እና " የምድራችን ጀግና " በሚል ሲንጋፖር ላይ በፈረንጆቹ 2006 ላይ የተሸለሙት ይጠቀሳሉ።

- ሕይወታቸው እስከአለፈበት ድረስም አዲስ አበባ ይኖሩ እንደነበር።

- ዶ/ር ተወልደብርሃን በተወለዱ በ83 ዓመታቸው ባደረባቸው ህመም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

- ዶክተር ተወልደ ብርሃን የሦስት ሴቶች ልጆች አባት ነበሩ፡፡ እንዲሁም ከ60 በላይ ሌሎች ልጆችን አሳድገዋል፡፡

Credit : #ኤፍቢሲ #ኤኤምሲ

@tikvahethiopia