TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
2:30 ይጀመራል ተብሎ 5:30 የተጀመረው ስብሰባ...
-----------------------------------------------------------
መሪዎች የሰዓት #ቀጠሮን በማክበር #ለወጣቶች አርአያ ሊሆኑ እንደሚገባ ተቀዳሚ ሙፍቲ ዑመር እድሪስ ጠየቁ። ተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጂ ዑመር ይህን ያሉት ሁለት ሰዓት ከሰላሳ ደቂቃ ይጀመራል ተብሎ ከረፋዱ አምስት ሰዓት በተጀመረው የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ሰባተኛ መደበኛ ጉባዔ ላይ ነው። ለጋዜጠኞች የተሰጠው የመግቢያ ካርድ ላይ “ሰዓት ይከበር” የሚል ማስጠንቀቂያ አዘል መልዕክት ሰፍሯል። ለዚህም ይመስላል ጋዜጠኞችና ተሳታፊዎች በሰዓቱ ታድመዋል፤ ይሁንና የክብር እንግዶቹ በወቅቱ ሊገኙ ባለመቻላቸው ጉባኤው በሰዓቱ ሊጀመር አልቻለም። የዘገየበትን ምክንያት የገለጸ፣ #ይቅርታ የጠየቀም ሆነ ኃላፊነት የወሰደ አካልም የለም። በጉባኤው የከተማዋ ምክትል ከንቲባና የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች ጉዳይ ሚኒስትርን ጨምሮ ከፌዴራልና ከከተማ አስተዳደሩ የተወጣጡ እንግዶችና የማህበሩ አባላት ታድመዋል። ተቀዳሚ ሙፍቲ ዑመር በዚሁ ጊዜ በተለያዩ ቦታዎች የሚካሄዱ ስብሰባዎች በተባሉበት ጊዜ #እንደማይጀመሩ ነው የገለጹት። በተባለበት ሰዓት በመገኘት ቀጠሮ በማክበር መሪዎች ለወጣቶች አርአያ ሊሆኑ እንደሚገባ በመግለጽ አገር፣ ሰላምና አንድነት የጋራ በመሆኑ ወጣቶች አንድነትን በተግባር በማሳየት ሰላምን ሊጠብቁ እንደሚገባም ገልጸዋል።

Via #ENA
🗞ቀን 15/10/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia