TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን‼️

የከተራና የጥምቀት በዓላት #በሰላም ተከብረው መጠናቀቃቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።

በሀገራችን በርከታ ህዝብ ወደ አደባባይ በመውጣት ከሚያከብራቸው ሃይማኖታዊ በዓላት መካከል የከተራና የጥምቀት በዓላት ይገኙበታል፡፡

እጅግ በርካታ ቁጥር ያላቸው የሃይማኖቱ ተከታዮች ፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ፣ መቀመጫቸውን ኢትዮጵያ ውስጥ ያደረጉ የውጭ ሀገራት ዲፕሎማቶች እና የተለያዩ ሀገራት ቱሪስቶች የታደሙበት በአዲስ አበባ ልዩ ልዩ ስፍራዎች በተለይም በጃን ሜዳ የተከበሩት የከተራና የጥምቀት በዓላት በሰላም መከበራቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

በዓላቱ  በሰላም እንዲከበሩ ህብረተሰቡ እና በዋናነት የከተማ  ወጣቶች ላደረጉት ቀና ትብብር ኮሚሽኑ ምስጋና አቅርቧል፡፡

በተጨማሪም  በነገው ዕለት  በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ዘንድ  የሚከበረው የቃና ዘገሊላ በዓል በሰላም እንዲከበር ህብረተሰቡ የተለመደ ትብብሩን #አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ መቅረቡን ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

ምንጭ፦ fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ ፦ ነሲሓ የበጎ አድራጎትና የልማት ድርጅት (NCDO) በደብረ ብርሃን መጠለያ ካምፕ ውስጥ ለሚገኙ የወለጋ ተፈናቃዮች ድጋፍ አደረገ።

ድርጅቱ ፤ የዒደ አል አድሐ በዓልን በማስመልከት በሁለት ዙር ድጋፍ ያደረገ ሲሆን ፤ በመጀመሪያው ዙር 19 በሬዎችን ፣ በሁለተኛ ዙር 10 በሬዎችንና 100 በጎችን በደምሩ 1.8 ሚሊዮን ብር ገደማ የሚገመት ድጋፍ አድርጓል።

ድርጅቱ ለወደፊቱም በሚችለው ሁሉ እገዛውን ለሚሹ የማኅበረሰብ ክፍሎች የሚያደርገውን ድጋፍ #አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቋል።

Credit : NCDO

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " በአንዋር መስጂድ የነበሩ በቁጥር እጅግ በርካታ ሰዎች በሰላም እንዲወጡ ተደርጓል " - የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሱልጣን አማን ኤባ እና የበላይ አመራሮች በአንዋር መስጂድ ከደረሱበት ጊዜ ጀምሮ ከፍተኛ የማረጋጋት ስራ በመስራት አንድ ሸሂድ (መስዋእት) የሆነ ሙስሊም እና ጉዳት የደረሰባቸውን ወደ ሆስፒታል…
መንግሥት ምን አለ ?

መንግሥት በታላቁ አንዋር መስጂድ " ሃይማኖትን ሽፋን በማድረግ ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን ለማፍረስ " የሚንቀሳቀሱ #የሴራ_ቡድኖች የሰላቱን ሰላማዊ ሥነ-ሥርዓት ለማስከበር በተሰማሩ የፀጥታ አካላት ላይ ጉዳት በማድረስ በተነሳ ረብሻ የሰው ህይወት መጥፋቱን እና ጉዳት መድረሱን ገለፀ።

የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ-ኃይል ዛሬ ምሽት መግለጫ ሰጥቷል።

በመግለጫው ፤ ዛሬ ግንቦት 25 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ በሁሉም ክፍለ ከተሞች በሚገኙ መስጅዶች የተካሄደው የጁምአ ሶላት በሰላም ተጠናቋል ብሏል።

በታላቁ አንዋር መስጅድ የጁምዓ ሶላት በሰላም ተጠናቆ ህዝብ ሙስሊሙ እየተመለሰ ባለበት ሁኔታ ሀይማኖትን ሽፋን በማድረግ " ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን ለማፍረስ " የሚንቀሳቀሱ #የሴራ_ቡድኖች የሰላቱን ሰላማዊ ሥነ-ሥርዓት ለማስከበር በተሰማሩ የፀጥታ አካላት ላይ ጉዳት ለማድረስ በተነሳ ረብሻ የሦስት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በተወሰኑ ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት ደርሷል ብሏል።

በንብረት ላይም እስከ አሁን ግምቱ ያልተወቀ ኪሳራ ደርሷል ያለው ግብረኃይሉ ለፀጥታ ሥራ በተሰማሩ 63 የፖሊስ አመራር እና አባላት ላይ ቀላል እና ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱን ገልጿል።

ግብረ ኃይሉ " ፀረ-ሰላም ኃይሎች " ሲል የጠራቸው አካላት የእምነቱ ተከታዮች በህጋዊ መንገድ ያቀረቡትን ጥያቄ በመጥለፍ የራሳቸውን እኩይ ዓላማ ለማሳካት ረብሻውን ወደ ሌሎች አካባቢዎች ለማዛመት ያደረጉት ጥረት የፀጥታ ኃይሉ፣ ህዝበ ሙስሊሙ እና የሀይማኖቱ አባቶች በጋራ በመሆን ባደረጉት ርብርብ መቆጣጠር ተችሏል ብሏል።

ግብረ-ኃይሉ ፤ የከተማውን ብሎም የሀገሪቱን ሠላምና ደህንነት ለማስከበር የጀመረውን ህግ የማስከበር ሥራ #አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።

የደረሰውን አጠቃላይ ጉዳት እና በህገ-ወጥ ተግባሩ ላይ የተሳተፉ " ፀረ-ሰላም ኃይሎች " ላይ የጀመረውን ምርመራም በመቀጠል በቀጣይ ውጤቱን ለህዝቡ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል።

@tikvahethiopia