TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#COVID19 #SafeHands #JawarMohammed

እጃችንን በመታጠብ ራሳችንን ፣ ቤተሰባችንን እና ህዝባችንን ከኮሮና ቫይረስ [COVID-19] እንጠብቅ /Harka keenya saamumaan dhiqachuun kornavaayrasii irraa if haa eegnu/

📹3 MB
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Election2012 በኮቪድ19 ምክንያት ቀጣዩን ምርጫ ለማካሄድ አስቸጋሪ በመሆኑ መንግስት አራት የመፍትሄ አማራጮችን አቀረበ። “ኮቪድ19 ምርጫን ማራዘም እና የህግ አማራጮች” በሚል ርዕስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት መንግስት ከተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ውይይት እያካሄደ ነው። ኢትዮጵያ በህገ መንግስቱ መሰረት እስከ ነሃሴ ወር ማለቂያ ድረስ አጠቃላይ ምርጫ የማካሄድ ግዴታ ቢኖርባትም…
#JawarMohammed

"አራቱም አማራጮች አያዋጡም" - አቶ ጃዋር መሀመድ

መንግስት በኮቪድ-19 ምክንያት ቀጣዩን ምርጫ ለማካሄድ አስቸጋሪ በመሆኑ ያቀረባቸው አራት የመፍትሄ አማራጮች ዙሪያ ከወዲሁ አስተያየት እየተሰጡ ነው።

የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ አባል የሆኑት ፖለቲከኛው አቶ ጃዋር መሀመድ 'አራቱም አማራጮች አያዋጡም' ሲሉ በይፋዊ የፌስቡክ ገፃቸው ሀሳባቸውን ገልፀዋል።

'አራቱም አማራጮች ህጋዊ መሰረት የላቸውም፤ መፍትሄው ህጋዊ ሳይዎን ፖሊቲካዊ ስምምነት መፍጠር ነው' ሲሉም ገልፀዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#JawarMohammed

አቶ ጃዋር መሀመድ በዛሬው የፍርድ ቤት ውሎ ከተናገሩት ፦

"መኖሪያ ቤቴ ውስጥ ከ100ሺህ ብር በላይ ፣ ወርቅ ፣ የእጅ ሰዓት እና በሽልማት ያገኘኋቸው የተለያዩ ሜዳሊያዎች ፖሊስ ወስዶ የራሱ ንብረት አድርጎታል። ለምንድነው የምዘረፈው ?

ከእኔ ጋር ለአንድ ቀን ሻይ የጠጡ ሰዎች የባንክ ሂሳባቸው ታግዷል ፤ አሁን ስልጣን ላይ ካሉ ባለስልጣናት ጋር ግን አብሮ ሻይ መጠጣት ብቻ ሳይሆን፣ ብዙ ነገር አብሬያቸሁ ሰርቻለሁ። እግዱ እውነተኛ ከሆነ ለምን የእነሱ የባንክ ሂሳብ አልታገደም?"

አቶ በቀለ ገርባ በዛሬው የፍርድ ቤት ውሎ የተናገሩት ፦

"እኔ ለ37 ዓመታት ያህል የመንግሥት ሰራተኛ ሆኜ የሰራሁ ሰው ነኝ። ይህን ያክል ዓመት የሰራ ሰው እንዴት አሮጌ መኪና ይኖረዋል ማለት ትክክል አይደለም።

ወደ አዳማ እና ነቀምቴ በሄድኩ ጊዜም ሕዝቡ ምን ዓይነት አቀባበል እንዳደረገልኝ ታውቃላችሁ። ወደ ውጪ በሄድኩ ጊዜም መኪና ተሸልሜ ነበር። ይህችን አሮጌ መኪና ንብረት አፈራ ተብሎ ማገዱ ትክክል አይደለም"

ተጨማሪ : https://telegra.ph/BBC-10-27 (BBC)

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#JawarMohammed #BekeleGerba

በእስር ላይ የሚገኙት አቶ ጀዋር መሐመድና አቶ በቀለ ገርባ የደህንነት ስጋት አለን በሚል ምክንያት ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቀሩ።

የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት የልደታ ምድብ ችሎት የተከሳሾች የንብረት እግድ ላይ ውሳኔ ለመስጠት ነበር ለዛሬ ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው።

ይሁን እንጂ ከተከሳሾች መካከል አቶ ጀዋር መሐመድ እና አቶ በቀለ ገርባ ፍርድ ቤት አልተገኙም።

ፍርድ ቤቱም አቶ ጀዋር መሐመድ እና አቶ በቀለ ገርባ ለምን ፍርድ ቤት እንዳልቀረቡ በጠየቀበት ወቅት፤ የማረሚያ ቤቱ አስተዳደር ተከሳሾቹ የደህንነት ስጋት አለብን በሚል ምክንያት አለመቅረታቸውን ለፍርድ ቤቱ አስታውቋል።

በእነ አቶ ጀዋር መሐመድ የክስ መዝገብ ውስጥ የተከሰሱት አቶ ሐምዛ ቦረና፤ "አቶ ጀዋር እና አቶ በቀለ 'አገሪቱ አሁን ያለችበት ተጨባጭ ሁኔታ ላይ ከፍተኛ ስጋት ስላለን በዚህ ቀጠሮ መገኘት አንችልም' ብለዋል" ሲሉ ለፍርድ ቤቱ ተናግረዋል።

"አሁን ባለው ሁኔታ አይደለም ጉዳት ይቅርና ሙከራ [የግድያ] ቢደረግብን አገሪቱ ወደ ከፋ አደጋ ውስጥ ስለሚያስገባት ለአገሪቱ በማሰብ ወደ ፍርድ ቤት ከሚደረግ ጉዞ እራሳችንን ቆጥበናል" ስለማለታቸው አቶ ሐምዛ ቦረና ለፍርድ ቤቱ ተናግረዋል።

ከዚህ በተጨማሪም አሁን አገሪቱ ውጥረት ውስጥ እያለች በንብረት ጉዳይ ላይ ለመከራከር ፍርድ ቤት መመላለስ 'ለእኛ ሃፍረት' ነው በሚል ምክንያት ፍርድ ቤት አለመቅረባቸውን አቶ ሐምዛ፤ አቶ ጀዋር እና አቶ በቀለን ወክለው ለፍርድ ቤቱ ተናግረዋል።

ፍርድ ቤቱ በንብረት እግዱ ላይ ውሳኔ ለመስጠት ለሕዳር 15 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥተዋል። (BBC)

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የፖለቲከኞቹ የረሃብ አድማ ፦

- እነአቶ ጃዋር መሀመድ በረሃብ አድማ ዛሬ 18ኛ ቀናቸውን መያዛቸው

- የፖለቲከኞቹ የጤና ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ

- እነዶ/ር ኢሊሊ ጀማል ባለው ሁኔታ ተገደው ክትትል ማቆማቸው

- ጠበቃ ከድር ቡሎ በተደጋጋሚ ውስኔ የተሰጠበት የፍርድ ቤት ትዕዛዝ መጣሱን መግለፃቸው

- ICRC አባላት ፖለቲከኞቹ ያሉበትን ሁኔታ መጎብኘታቸው

- አቶ በቀለ ገርባ ወደግል የህክምና ተቋማ እንዳይወሰዱ መከልከላቸው

- ስንት ቀን ያለምግብ መቆየት ይቻላል ? የዶ/ር ኢሊሊ ጀማል ምላሽ

https://telegra.ph/JawarMohammed-02-14
TIKVAH-ETHIOPIA
የፖለቲከኞቹ የረሃብ አድማ ፦ - እነአቶ ጃዋር መሀመድ በረሃብ አድማ ዛሬ 18ኛ ቀናቸውን መያዛቸው - የፖለቲከኞቹ የጤና ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ - እነዶ/ር ኢሊሊ ጀማል ባለው ሁኔታ ተገደው ክትትል ማቆማቸው - ጠበቃ ከድር ቡሎ በተደጋጋሚ ውስኔ የተሰጠበት የፍርድ ቤት ትዕዛዝ መጣሱን መግለፃቸው - ICRC አባላት ፖለቲከኞቹ ያሉበትን ሁኔታ መጎብኘታቸው - አቶ በቀለ ገርባ ወደግል የህክምና…
#Update

ዛሬ የካቲት 8 የነአቶ ጃዋር መሃመድ ጠበቆች በረሃብ አድማ ላይ የሚገኙ እስረኞች የህክምና ጉዳይ አስመልክቶ ጉዳዩን ለሚያየው የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ችሎት አቤቱታ አቅርበው ነበር።

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎትም እነአቶ ጀዋር መሀመድ በግል ሀኪሞቻቸው እንዲሁም በፈለጉት የግል ህክምና ተቋም መታከም እንደሚችሉ አፅንኦት ሰጥቶ ትዕዛዝ አስተላልፏል።

ከቀናት በፊት አቶ በቀለ እያደረጉት በሚገኘው የረሃብ አድማ ምክንያት በጠና ታመው ወደ ህክምና ተቋም ሊወሰዱ ሲሉ እንዳይሄዱ ማረሚያ ቤቱ "ከላይ በመጣ" ትዕዛዝ ከልክሎ እንደነበር የህክምና ክትትል የሚያደርጉላቸው ዶ/ር ኢሊሊ ጀማል መግለፃቸው ይታወሳል።

በተጨማሪ ሀኪሞቻቸው ባለው ሁኔታ ተገደው ለእነአቶ ጃዋር የሚያደርጉትን የህክምና ክትትል ማቋረጣቸውን እንደገለፁ ይታወቃል።

https://telegra.ph/JawarMohammed-02-15
#JawarMohammed

አቶ ጃዋር መሀመድ (የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ምክትል ሊቀመንበር) ከእስር ከተፈቱ በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ " ኡቡንቱ ቲቪ " ለተሰኘ የማህበራዊ መገናኛ Exclusive ቃለ ምልልስ ሰጥተዋል።

በዚሁ ቃለ ምምልስ ወቅት አቶ ጃዋር ከተጠየቁት ጥያቄዎች አንዱ እሳቸውን በተመለከተ ሲናፈሱ የነበሩ አሉባልታዎችን እንዲያጠሩ ነው " አቶ ጃዋር ከገዢው ፓርቲ ጋር መስራት ጀምሯል፣ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ተገናኝቷል የተፈታውም ለዚህ ነው ፤ አሁንም እየሰራ ያለው የመንግስትን ስራ ነው " ስለሚባሉት ጉዳዮች ግልፅ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

አቶ ጃዋር መሀመድ ፦

" እኔም ሰማቸዋለሁ አሉባልታዎቹን ። እኔ ከማንም ጋር የግል ቁርሾ የለኝም። የታሰርኩትም ቢሆን በፖለቲካ ልዩነት እንጂ በግል ፀብ አይደለም።

ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር አልተገናኘንም፤ ሊያገኘኝ ከፈለገ ግን ሁሌም ዝግጁ ነኝ። ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ብቻ ሳይሆን / ከዐቢይ ጋር ብቻ ሳይሆን ከመሮም ጋር፣ ከደብረፅዮንም ጋር ከሁሉም በአሁን ወቅት በሀገራችን ባለው ግጭት ውስጥ እየተሳተፉ ካሉ ኃይሎች ጋር ተገናኝቶ ሀገራችንን ከጦርነት አስወጥቶ ወደ ሰላም እና ልማት ለመመለስ እድሉ ከተገኘ ከማናቸውም ጋር ለመስራት፣ ከማናቸውም ጋር ለመተባበር ፣ ከማናቸውም ጋር ለመነጋገር በማንኛውም ቦታ እና ሁኔታ ለመነጋገር ዝግጁ ነኝ።

እኔ ማልፈቅደው ግን ከማናቸውም ጋር አብሬ ጦርነት ማፋፋም አልፈልግም፤ ከማናቸውም ጋር።

ሁሉም በጦርነት ውስጥ እየተሳተፉ ያሉ ይሁኑ በጦርነት ውስጥ እያልተሳተፉ ያሉ ምሁራን እና ሊህቃን ወደ ሰላም ጠረጴዛ መምጣት አለባቸው ብዬ አምናለሁ፤ ከአንዳቸውም ጋር ግላዊ ጠብ የለኝም።

ስለዚህ ገዥው ፓርቲ ሀገር እየገዛ ነው ያለው ፤ ሀገር እያስተዳደረ ነው ያለው ፣ ሀገሪቷ ለገባችበት ችግር ትልቁን ድርሻ የሚወስደው ገዢው ፓርቲ ነው፤ እንደመሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ነው ፤ ወደመፍትሄ የምንገባ ከሆነ የእነሱ ተሳትፎ፣ የእነሱ ፍቃደኝነት ወሳኝ ነው።

ስለዚህ እንደ ፖለቲካ ፓርቲ አመራርም እንደ እዚህች ሀገር ዜጋም በሰላም ጉዳይ ላይ የሀገራችንን እጣፈንታ ወደፊት ማስተካከል ላይ ከገዢው ፓርቲም ጋር ሆነ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ሆነ፣ የተለያዩ ድርጅቶች ከሚመሩ ቅድም እንዳልኩት ከደብረፅዮን ሆነ ፣ ከፃድቃን ሆነው፣ ከመሮም ሆነ፣ ከገመቹ ሆነ፣ ከተፈራ ማሞ ሆነ ፣ ከይልቃል ከፋለ ጋርም ሆነ ከማንኛውም ጋር ለመስራት ዝግጁ ነኝ፤ የሀገራችን አመራርም ለዚህ መዘጋጀት መቻል አለበት።

ሀገራችን ያለችበት ሁኔታ ለምን ከእከሌ ጋር ተነጋገርክ፣ እከሌ ሳይጣን ነው እከሌ መልአክ ነው በማለት እንደማያዋጣ ላለፉት 4 ፣ ላለፉት 2 ዓመታት ግልፅ ሆኗል።

ስለዚህ አሁንም ደግሜ የምለው ከማንኛውም የፖለቲካ ኃይል ጋር ፣ ከማንኛውም የፖለቲካ አመራር ጋር ህዝባችንን አሁን ከገባበት መቀመቅ እና ሰቆቃ ለማውጣት መስራት ያስፈልጋል።

እዚህ ላይ ግልፅ ማድረግ የምፈልገው ከማኛውም ኃይል ጋር እንሰራለን እንደ ድርጅትም እንደ ግለሰብም እንደ አመራርም፤ ሀገራችንን እና ህዝባችንን ወደ ሰላም መንገድ ወደ ልማት እንዲመለሱ ባለኝ እውቀት እና ባለኝ ተሰሚነት መጥቀም እፈልጋለሁ።

ነገር ግን ለማንም ድርጅት ሆነ ግለሰብ መጠቀሚያ መሆን አልፈልግም ፤ ለማንም የጦር ማገዶ መሆን አልፈልግም ፣ የማንንም አንባገነናዊ አካሄድን፤ የማንም ጦረኛ አካሄድን መደገፍ አልፈልግም።

ወደ ሰላም መምጣት ከሚፈልግ አካል ጋር ለመስራት ዝግጁ ነኝ፣ ይሄ ደግሞ ኩነኔ አይደለም ይሄ ትክክለኛ ነው ብዬ የማምነው ፤ ስለዚህ ጦርነቱ መቆም አለበት ጦርነት ቆሞ ወደ ድርድር መምጣት አለብን ቴክኒካል ነገሮች መነሳት አለባቸው ስለዚህ ለመነጋገር ጋሬጣ ሆነው ያሉ ነገሮች ተሰባብረው ድልድይ ተመስርቶ ሁላችንም ወደመነጋገር መግባት አስፈላጊ ነው። "

@tikvahethiopia
#JawarMohammed

ኦፌኮ በብሄራዊ ምክክር ላይ አልሳተፍም ብሏል ?

አቶ ጃዋር መሀመድ (ምክትል ሊቀመንበር) ፦

" ትንሽ የግንዛቤ ችግር አለ። እኛ እንደ ኦፌኮ አንሳተፍም አይደለም ያልነው ቅድመ ሁኔታዎችን ነው ያስቀምጥነው። ብሄራዊ መግባባት (National Dialogue) የኦፌኮ አጀንዳ ነው።

... ስለዚህ ኦፌኮ የብሄራዊ ድርድርን ወይም የብሄራዊ መግባባትን አይፈልግም የሚለው የተሳሳተ አመለካከት ነው፤ እንፈልጋለን፤ አሁንም ቢሆን እንፈልጋለን ፤ አሁንም ቢሆን ለሀገራችን የሚጠቅመው እሱ ነው ብለን ነው የምናምነው።

ነገር ግን ብሄራዊ መግባባት ሲባል ፕሮሰስ አለው ፤ ብሄራዊ መግባባት በሁለት ደረጃ ነው በአንድ ሀገር ውስጥ ሊካሄድ የሚችለው።

አንዱ የፖለቲካ ልዩነቶች ወደ ጦርነት እንዳያመሩ የቅድመ ጦርነት ንግግር የሚባል ነው የፖለቲካ ልዩነቶች ፣ የፖለቲካ ሽኩቻዎች ሀገርን እና የፖለቲካ ኃይሎችን ወደ ጦርነት እንዳያስገቡ በንግግር እና በድርድር ለመፍታት የሚደረግ ብሄራዊ መግባባት አንድ አለ፤ ያ ሳይደረግ እድል አምልጦ ሀገር ወደ ጦርነት ከገባች በኃላ ደግሞ ጦርነት ቆሞ ከጦርነት በኃላ ለጦርነት መንስኤ የሆኑ ጉዳዮችም ሆኑ በጦርነት የተፈጠሩ ክስተቶች ለሌላ ጦርነት እንዳይጋብዙ ከስር መሰረቱ ለመፍታት የሚደረግ ክንውን ነው ፤ ይሄን መገንዘብ አስፈላጊ ነው።

ብሄራዊ መግባባት በጦርነት መካከል ሊካሄድ አይችልም። ሀገራችን በጦርነት መሀከል ነች፤ 2019/20 መጀመሪያ አካባቢ ቢሆን 2019/18 ጥሩ ጊዜ የነበረው ለውጡ እንደመጣ የመጀመሪያ ወራት መጀመር ነበረበት ያ አምልጧል አሁን ጦርነት ውስጥ ነው ያለነው።

ብሄራዊ መግባባት ሲባል የመጀመሪያው criteria ሁሉንም ያሳተፈ መሆን አለበት።

በተለይ ጦርነት ከተገባ ፣ ከሁሉም የበለጠ ብሄራዊ መግባባት ውስጥ መግባት እና መሳተፍ ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገባው በጦርነት ውስጥ የተሳተፉት ቡድኖች ናቸው። ጦርነት እየተካሄደ እነዚህ በጦርነት የተሳተፉ ቡድኖች ማሳተፍ አልቻልም። Legally ሆነ በ Security wise ማሳተፍ አይቻልም። ይህ ስለሆነ ዋናው እኛ ቅድመ ሁኔታ ያስቀመጥነው ብሄራዊ መግባባት ጥሩ ነው መንግስት ረጅም ጊዜ አልሰማም ብሎ አሁን የብሄራዊ መግባባት ማለቱ ጥሩ ነው ደስ ብሎናል ነገር ግን ይሄን ነገር በአግባቡ እንስራው ስለዚህ ጦርነት ይቁም ፤ ጦረኞቹ ሙሉ በሙሉ ይታረቁ አይደለም እያልን ያለነው ብሄራዊ መግባባቱ ላይ ሊታረቁ ይችላሉ ነገር ግን active fighting እንዲቆም ማድረግ በሰሜንም ፣ በትግራይ ድምበርም ፣ በቤኒሻንጉልም፣ በኦሮሚያም በተለያየ አካባቢ እየተደረገ ያለው ጦርነት መጀመሪያ መቆም አለበት... "

#ያንብቡ ➡️ https://telegra.ph/Jawar-Mohammed-05-27
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " Galatoomaa Tour " የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጃዋር መሐመድ ጀርመን ይገኛሉ። ዛሬ በጀርመን ኑርንበርግ በነበረ ህዝባዊ ስበስባ በእስር ላይ በቆዩባቸው ጊዜያት ለሳቸው እና አብረዋቸው ለታሰሩ ሰዎች ከእስር እንዲለቀቁ ደጋፊዎቻቸው አድርገዋል ላሉት ጥረት ምስጋና አቅርበዋል። የእነ አቶ ጃዋር መሐመድ የአውሮፓ እና አሜሪካ ጉዞ አንደኛው አላማ ምስጋና…
#JawarMohammed

አቶ ጃዋር መሐመድ (የኦፌኮ ም/ሊቀመንበር) በዛሬው የጀርመኑ ህዝባዊ ስብሰባ ወቅት ካነሷቸው ነጥቦች ጥቂቶቹ ፦

➡️ አቶ ጃዋር አጠቃላይ ኢትዮጵያም ሆነ ኦሮሚያ በብዙ ውጥንቅጥ ውስጥ መሆናቸውን ገልፀው ፤ ከዚህ ውጥንቅጥ ተወጥቶ #ሰላም እንዲሰፍን የማድረግ ጥረት መጀመራቸውን ገልፀዋል።

➡️ አቶ ጃዋር ለጀመሩት ሰላም የማስፈን ጥረት በሀገር ውስጥ እና በውጭ ያሉ ደጋፊዎቻቸው አብረዋቸው ሆነው ጦርነት እንዲቆም ፣ ሰላም እንዲሰበክ፣ ሰላም እንዲፈጠረ በአንድ እና ሁለት ክልል የተወሰነ ሳይሆን በመላው ሀገሪቱ ሰላም እንዲፈጠር ድጋፋቸውን እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

➡️ ኢትዮጵያ ሰላም እንድትሆን በመሰረታዊነት ኦሮሚያ ውስጥ ያለው ችግር ከመሰረቱ መፈታት አለበት የሚል እምነት እንዳላቸው ገልፀው ለዚህም ጦርነት በማቆም ሁሉም ወደ ሰላም የሚመለስበት እድል እንዲፈጠር እሻለሁ ብለዋል።

Credit- መረጃው ስብሰባውን በአካል የተካፈለው የዶቼቨለ ሬድዮ ጣቢያ ጋዜጠኛ ታምራት ዲንሳ ነው ያጋራው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Oromia ከቀናት በፊት ከኦሮሚያ ክልል መንግስትና መንግስት " ሸኔ " እያለ የሚጠራው እራሱን የ " ኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት " ከሚለው ቡድን የሰላም ድምጾች ተሰምተዋል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ከሰሞኑ በተካሄደው የጨፌ ኦሮሚያ መደበኛ ስብሰባ ላይ ፦ " በዚህ በተከበረው ጨፌው ፊት በክልላችን ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ አካላት ማለትም ኦነግ ሸኔ በእርቅ ወደ ሰላማዊ መንገድ ተመልሶ…
#JawarMohammed

የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (OFC) ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጃዋር መሀመድ የኦሮሚያን የሰላም ጉዳይ በተመለከተ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ያሰፈሩት ሃሳብ ፦

" የኦሮሚያ የሰላም ጉዳይ መስመር እየያዘ ይመስላል።

የሰላም ሂደቱ ከሽማግሌዎች አልፏል ፤ ይህ ዕድል በ2011 ዓ.ም ላይ ያመለጠ ነው።

መንግስት በውጪ አደራዳሪዎች ላይ ያለውን ጥርጣሬ ማንሳት አለበት ፤ ለቴክኒክ፣ ለሎጅስቲክስ እንዲሁም ለህጋዊና ለጋራ ትምምን ሲባል የውጭ አካላት ድርድሩን እንዲመሩት ያስፈልጋል።

የፖለቲካ አመራሩ፣ ምሁራኑ እና አጠቃላይ ህብረተሰቡ ለሁለቱም ወገኖች አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ ለዚህ ተስፋ በፍጥነት ተግባራዊ መሆን የበኩሉን መወጣት አለበት።

በአሁን ሰዓት ሰላምን ከማስፈን እና ህዝባችንን ከከባድ ጥፋት ከማዳን የተሻለ ነገር የለም። "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#OROMIA #Peace

" . . . እርቁ በምንፈልገው ፍጥነት አለመምጣቱ ቢያሳዝንም ተስፋ መቁረጥ ግን አያስፈልግም " - አቶ ጃዋር መሀመድ

አቶ ጃዋር መሀመድ የኢፌዴሪ መንግሥትና የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (OLA) በታንዛኒያ ዳሬሰላም ያደረጉት የሁለተኛው ዙር ድርድር ያለ ስምምነት ከተበተነ በኃላ ድርድሩን በተመለከተ ሰፋ ያለ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

አቶ ጃዋር መሀመድ ምን አሉ ?

- መንግስትንና የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (WBO-OLA) ለማስታረቅ የተደረገው 2ኛው ዙር ሙከራ አለመሳካቱ በህዝቡ ዘንድ ትልቅ ሀዘን የፈጠረ ነው።

- በሕዝቡ በኩል ቢያንስ ሁለቱም ወገኖች በዚህ ዙር የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ እንደሚደርሱ ተስፋ ተደርጎ ነበር። በተለይ የጦር አዛዦች ከጦር ሜዳ ለውይይት መምጣታቸው እርቀ ሰላሙን ያሳካል የሚል ተስፋ ፈጥሮ ነበር።

- ድርድሩ አለመሳካት እንደ ትልቅ ውድቀት ሲቀርብ እናያለን ነገር ግን ውይይቱ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ብዙ ርቀት ተጉዟል። እርቅ ከማያስፈልግበት ወይም ከማይቻልበት ደረጃ ተነስተን የሁለቱም ወገን አመራሮች ፊት ለፊት ተገናኝተው መወያየት ደረጃ ደርሰናል።

- ይህ እርቅ በምንፈልገው ፍጥነት አለመምጣቱ ቢያሳዝንም ተስፋ መቁረጥ ግን አያስፈልግም። ተስፋ ልንቆርጥም አንችልም። ሌላ መፍትሄ የለንምና። ስለዚህ የሰላም ድርድሩ እንደሚቀጥል ተስፋ እናደርጋለን።

🕊አቶ ጃዋር መሀመድ በሁለተኛው ዙር የሰላም ድርድር ላይ ከተሳተፉት አካላት እና ከተለያዩ ምንጮች ተረዳሁት ያሉትንና ለቀጣይ ዙር የሰላም ድርድር ያግዛሉ ያሏቸውን ሃሳባችን በዝርዝር አቅርበዋል።

➜ በሁለተኛው ዙር የሰላም ድርድር ሁለቱም ወገኖች በእውነት #እርቅ/#ሰላም ለመፍጠር ቁርጠኛ መሆናቸውን አረጋግጫለሁ።

በዚህ የተነሳ ሁለቱም ወገኖች ልክ እንደ ህዝቡ ይህ ምዕራፍ በእርቅ ስምምነቱ ይጠናቀቃል የሚል ተስፋ (expectation) ይዘው ነበር የቀረቡት።

ሁሉም ተሳታፊዎች (WBO / የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ፣ መንግስት እና አሸማጋዮች) በሰላም፣ በእርቅ ይጠናቀቃል የሚል ተስፋ ይዘው ስለሄዱ ግባቸው ላይ ባለመድረሳቸው የመናደድ ስሜት ውስጥ ገብተዋል። በዚህ ምክንያት ለቀጣዩ የሰላም ውይይት በር ከመክፈታቸው በፊት ተለያይተዋል።

➜ ሁለቱም ወገኖች በቅን ልቦና ለመታረቅ ቢሄዱም፣ አንዱ ከአንዱ የሚፈልገውን (demands/concessions) ለመስጠት እና ለመቀበል ሙሉ በሙሉ የተዘጋጁ አይመስሉም።

በመጀመሪያው ዙር እርስ በርሳቸው የሚፈልጉትን ነገር ተረድተው ተለያይተዋል። በሁለተኛው ዙር ደግሞ አንዳቸው ለሌላው መስጠት የማይችሉትን ያወቁ ይመስለኛል።

አሁንም ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ቁርጠኝነት ካላቸው፣ ቀጣዩ እርምጃ ሁለቱም ወገኖች ጥያቄዎቻቸውን ለማስተካከል (modifying demands) መዘጋጀት አለባቸው። ይህ ማለት እንዱ መቀበል የማይችላቸው ነገሮች ላይ በመግፋት መጋጨት መተው አለባቸው።

በሰላም ድርድር ውስጥ የሚፈልጉትን እና ይገባኛል ብለው የሚያስቡትን ሁሉ ማግኘት አይቻልም። ይገባኛል ብለው የሚያስቡትን ሁሉ ማጣትም አይቻልም። ሁለቱም ወገኖች ወደ መካከለኛው አቋም መምጣት ይጠበቅባቸዋል።

➜ የሰላም ድርድሩ ዋነኛው #እንቅፋት እየሆነ ያለው ዋና ምክንያት አንዱ ከአንዱ የሚፈልገው ነገር ላይ ተራርቀው ነው ብዬ አላስብም። ትልቁ እንቅፋት #አለመተማመን ነው። በሁለቱ ወገኖች በታሪክ ካለው ግንኙነት እና ከአገራችን የፖለቲካ ባህል አንፃር አለመተማመናቸው ይጠበቃል። የውጪው አካል ያስፈለገበትም ምክንያት ይሄ ችግር ስለተረዳ ነው። እነዚህ አስታራቂዎች የእርቅ ስምምነት ላይ መድረስ ብቻ ሳይሆን የስምምነቱ አፈጻጸምን ለማረጋገጥ ኃላፊነቱን እንደሚወስዱ ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ይህንን አሻሚ የሆነ ችግር ለማሻሻል ይጠቅማል።

➜ ከውስጥ ከውጭ " እርቅ ሊመጣ ነው " ብለው እያዘኑ የነበሩት ወገኖች አሁን በመፍረሱ በደስታ እየፈነደቁ ነው። ሌላ ዙር ድርድር እንዳይደረግም እያሴሩ ነው። የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (OLA) እና የመንግስት አመራሮች አሁንም ጉዳዩን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የሚያስችል አቋም ካላቸው እነዚህ ፀረ-ሰላም ኃይሎች ወደ ውስጥ እንዳይገቡ ሁሉንም ክፍተቶች መዝጋት አለባቸው። በተጨማሪም የሚቀጥለውን ዙር እድሎች ከሚያጠብ ወይም ከሚያርቁ ድርጊቶች እና ቃላት መቆጠብ አለባቸው። ይህም የሚዲያ ፕሮፓጋንዳ እና የመስክ ውጊያን አለማባባስን ያካትታል።

➜ እኔ እስከተረዳሁት ድረስ ከ2ቱም ወገን ደጋፊዎች በኩል የነበረው የ " #ምታ - #ስበር - #አጥፋ " ዘመቻ ባለፉት አመታት በጣም መቀነሱን ነው። የእርቅ ሀሳብ መደገፍ እና ሰላም እንዲወርድ ያላቸው ምኞትም ከየትኛውም ጊዜ በላይ እያደገ መጥቷል።

➜ አሁንም የሁለተኛው ዙር ሙከራ ስላልተሳካ እርስ በርስ ጣት መቀሳሰር እና መደማማት ምንም ፋይዳ እንደሌለው መረዳት ያስፈልጋል። የሚጠቅመው የሚደግፉትን ወገኖች ወደ ድርድሩ እንዲመለሱ እና የሚጠበቅባቸውን እንዲሰጡ ማበረታታት እና ጫና ማድረግ ነው።

➜ በመጨረሻም ፤ ልብ ሊባል የሚገባው ነገር ይሄ የሰላም ድርድር የጦር ሜዳ ውጤቶች አይደለም።

ሁለት የሚዋጉ ወገኖች ለእርቅ ድርድር የሚቀመጡት በሁለት ሁኔታዎች ውስጥ ነው።

የመጀመሪያው ፦ በጦር ሜዳ ላይ አንደኛው የበለጠ የበላይነት አግኝቶ ወደ ድል ሲቃረብ እና ሌላኛው ወገን ሙሉ በሙሉ ከመሸነፉ በፊት ለመታረቅ ሲወስን ነው።

ሁለተኛው ፦ ከረዥም ጊዜ ጦርነት በኋላ ሁለቱም ወገኖች መሸናነፍ ካልቻሉ ነው። በWBO-OLA እና በመንግስት መካከል ያለው ጦርነት የመሸናነፍ ወይም የመድከም ደረጃ ላይ አልደረሰም። በአጭር ጊዜ ውስጥም እዚህ ደረጃ ላይ ይደርሳል ብዬ አላስብም። ይህ ውይይት የመጣው በህዝብ እና በአለም አቀፍ ማህበረሰብ ግፊት ነው።

በተለይም ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በሀገራችን ሰላም እንዲሰፍን ያሳየው ትኩረት ያልተጠበቀ እና ትልቅ እድል ነው።

የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ትኩረት በፍጥነት እየተቀየረ ነው። ስለዚህ ፤ ጉዳያችን ትኩረት ባገኘበት በዚህ ወቅት በፍጥነትና በብልሃት መጠቀም አስፈላጊ ነው። ይህንን እድል መጠቀም ካልቻልንና የሚባክን ከሆነ ለረጅም ጊዜ እንቆጫለን።

#JawarMohammed

Via https://publielectoral.lat/tikvahethAFAANOROMOO

#TikvahEthiopiaAFAANOROMOO

@tikvahethiopia