TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ጥቆማ #ከጠቀማችሁ

የአዳማ ጉምሩክ ኮሚሽን ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ተወርሰው የሚገኙ 171 ተሽከርካሪዎችን በግልፅ ጨረታ ባሉበት ሁኔታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል። ተጨራቾች የጨረታ ሰንድ በመግዛት በጨረታው ላይ የሚወጡትን ተሽከርካሪዎች በአካል በመመልከት መጫረት ትችላላችሁ ተብሏል። ጨረታው በ26/02/2016 ዓ/ም ጥዋት 4 ሰዓት ላይ የጨረታ ሳጥኑ ተዘግቶ በዚሁ ቀን 4:15 ላይ የጨረታ ሳጥኑ ይከፈታል። ለተጨማሪ መረጃ በስልክ 0221118429 ላይ መወደል ይቻላል።

አዲስ አበባ ቃሊት ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት የተተው፣ የተወረሱ እና በኮንትሮባንድ ተይዘው የሚገኙ የተለያዩ የቤትና የጭነት ተሸከርካሪዎች ፦
- DUMP TRUCK፣
- IVECO FIAT፣
- TOYOTA HAILUX፣
- TOYOTA COROLLA፣
- TOYOTA  VITZ፣
- TOYOTA HAICE፣
- TOYOTA YARIS፣
- TOYOTA CHR፣
- HYUNDAI፣
- SUZUKI፣
- MISTUBUSHI ፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫዎችን፣ የሞባይል ክፍሎች፣ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን፣ የተለያዩ የተዘጋጁ አልባሳትና ጫማዎች፣ የውብት መጠበቂያ ዕቃዎች እና ሌሎች የተለያዩ ዕቃዎችን ባሉበት ሁኔታ በግልፅና በሃራጅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል። የተጠቀሱት ተሸከርካሪዎች የጨረታ ሰነድ ከቀን 20/02/2016 ዓ.ም ጀምሮ ማግኘት ይቻላል።

(ዝርዝር መረጃዎችን ከላይ በምስሉ ይመልከቱ)

  የገቢዎች ሚኒስቴር በታክስ ዕዳ የያዛቸውን ተሽከርካሪዎችና ሌሎች የተለያዩ ንብረቶች ለመሸጥ ይፈልጋል።

ከፎኔክስ ኢንደስትሪ ኃ/የ/የግ/ማህበር የተያዘ፦
- የኘላስቲክ ወንበር ማምረቻ ማሽን፣  የማሽኑ ማቀዝቀዣ (cooler)፣ የማሽኑ ጥሬ ዕቃዎችና ሌሎች ተጓዳኝ ዕቃዎች፣

ከተክለብርሃን አምባየ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር የተያዙ ፦
- የተለያዩ መጠን ያላቸው የመብራት አምፖሎች፣
- ፍሎረሰንቶች፣
- ፖውዛዎች እና የውሃ ተቀባሪና ተንጠልጣይ የተለያዩ ቧንቧዎች፣

🚘 ከቲ.አይ.ቢ ኬተሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማህ እና ኦክስፎርድ አማልጌትድ ኃ/የተ/ የግ/ማህበር የተያዙ የተለያየ ሞዴል ያላቸውን 3 ተሽከርካሪዎች ናቸው።

(ዝርዝር መረጃዎችን ከላይ በምስሉ ይመልከቱ)

#ጉምሩክኮሚሽን #አዲስዘመን #ገቢዎችሚኒስቴር

* ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት በጥቆማ መልክ የቀረበ።

@tikvahethiopia
#ከጠቀማችሁ

ከላይ በፎቶው የምትመለከቷቸው ተሽከርካሪዎች የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር በጨረታ ለመሸጥ ያቀረባቸው ናቸው።

የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የተለያዩ ፦
- ያገለገሉ ቀላል ተሽከርካሪዎች
- ያገለገሉ ከባድ ተሽክርካሪዎች ፤
- ቁርጥራጭ የመኪና አካላት (ስክራፕ) እና የተለያዩ ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶች (ስክራፕ) ንብረቶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።

ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ እስከ የካቲት 18 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ከጠዋቱ 03:00 እስክ 10:00 ሰዓት ድረስ አዲስ አበባ በሚገኘው የመከላከያ ሠራዊት መኮንኖች ከበብ በመገኘት የተሽከርካሪ ሰነድ የማይመለስ ብር 500 እና ቁርጥራጭ ብረታ ብረት (ስክራፕ) ሰነድ የማይመለስ ብር 200.00 በመክፈል መግዛት ይችላሉ።

ተጫራቾች እስከ የካቲት 18 ቀን 2016 ዓ/ም ባሉት ቀናቶች የሚሸጡትን ተሽከርካሪዎች ለማየት ኮፈን ተከፍቶ ስለሚቆይ ዘውትር በስራ ሰዓት ከጥዋቱ 3:09 እስከ 10:00 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን ቢሾፍቱ በሚገኘው አውቶሞቲቭ ካምፕ ጀርባ በመሄድ ሞያተኛ ይዞ መመልከት ይችላሉ።

ጨረታው የካቲት 18/2016 ከጥዋቱ 4:00 ሰዓት የሚዘጋ ሲሆን  በዚያው ቀን 4:30 ይከፈታል። የሁሉም ተሽከርካሪዎች ጨረታ የሚከፈተው በመከላከያ ሰራዊት መኮንኖች ክበብ ነው።

አሸናፊዎች ያሸነፉበትን ገንዘብ አጠቃለው ከከፈሉ በኃላ ተሽከርካሪዎቹን በ30 የስራ ቀናት ውስጥ ማንሳት ግዴታ አለባቸው።

ለስም ማዞሪያ ወጪ እና ብረታ ብረቶችን ከቦታው ለማንሳት የሚያስፈልግ ወጪ  ሙሉ በሙሉ በገዢዎቹ ነው የሚሸፈነው።

ቁርጥራጭ ብረቶችን ለመጫረት የሚፈልግ ተጫራች ከንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ብረታ ብርት የማቅለጥ ፍቃድ የተሰጠው ብቻ ነው ተብሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ምናልባት ለስራም ሆነ ለግል ጉዳያችሁ ከጠቀመ በሚል ነው ይህን መረጃ ያጋራው።

@tikvahethiopia