TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል። ዶ/ር ለገሰ ፥ መንግስት ለያዘው ሀገራዊ ምክክርና ብሄራዊ መግባባት ለመፍጠር ሁሉን አካታች የሆነ ውይይት ማድረግ አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበታል ብለዋል። ይህን ሀገራዊ አንድነት ለማምጣትም ብዙ ተከታይ ያላቸውን እስረኞች ክስ ማቋረጥ ማስፈለጉን ነው የተናገሩት። በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት ፣ የተመቻቸ…
#DrLegesseTulu

የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትሩ ምን አሉ ?

ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ፦

" ... በኢትዮጵያ የሚስተዋሉ ችግሮችን ከስር መሰረቱ ለመፍታት የእስረኞችን ክስ ማቋረጥ አስፈልጓል።

የክሱ መቋረጥ ማህበራዊ ፣ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለመፍታት እና ዋስትና ያለው የዴሞክራሲ ስርዓት በመገንባት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስቀጠል ከማሰብ የመነጨ መሰረታዊ ጉዳይ ነው።

በእነ አቶ ጃዋር መሃመድና አቶ እስክንድር ነጋ ስር የነበሩ ተከሳሾች ክስ መቋረጥ በስራቸው በርካታ ተከታይ ያላቸው መሆናቸውን ከግንዛቤ በማስገባት ለብሔራዊ አካታች ምክክሩ ጉልህ ሚና እንዳላቸው በመገንዘብ ነው።

በሽብር ቡዱኑ መሪ ደብረፂዮን ገብረ ሚካኤል ስር ያሉ የክስ ሂደት መቋረጥ ከጤና እና እድሜ መግፋት ጋር የተያያዘ ነው።

ኢትዮጵያዊያን ክሳቸው የተቋረጡ ዜጎችን በሚመለከት ህዝብና መንግስትን በማጋጨት እራሳቸውን ደብቀው የሚያራግቡ አካላትን በቃቹህ በማለት ለዘላቂ ብሔራዊ ጥቅም ዘብ መሆን ይገባል "

#ኢዜአ

@tikvahethiopia