TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የሰራተኞች ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ። ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰራተኞች የተሰጠው ፈተና #ውጤት ይፋ ሆኗል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተዘጋጀው እና ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰራተኞች ሲሰጥ የነበረው ፈተናን በሚመለከት በዛሬው ዕለት መግለጫ ተሰጥቷል። በዚህ መግለጫም ፤ የቴክኒክና ባህሪ ብቃት ፈተናው የወሰዱት የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች፣…
#AddisAbaba #Exam

ለአዲስ አበባ አስተዳደር አመራሮች ፣ ባለሞያዎች / ሠራተኞች የተሰጠውን የቴክኒክ እና ባህሪ ብቃት ፈተና የማለፊያ ነጥብ አምጥተው ያለፉ #የክዋኔ_ክህሎት ስልጠና ይሰጣቸዋል ተብሏል።

የማለፊያ ነጥብ ማምጣት ሳይችሉ ቀርተው #ያላለፉት ደግሞ #የአቅም_ግንባታ_ስልጠና እንደሚሰጣቸው ተጠቁሟል።

በተጨማሪ የማለፊያ ውጤት ያላመጡት ዝቅ ብለው እንደሚመደቡ ፤ አሁን ላይ #ስንብት የሚባል ነገር እንደሌለ ፤ ስንብት የሚፈፀመው መጨርሻ ላይ ሁሉ ነገር ከተጠናቀቀና ሌላ አማራጭ ከጠፋ ብቻ መሆኑ ተነግሯል።

የፈተናው ውጤት፦

👉 የቴክኒክና የባህሪ ብቃት ምዘና ፈተናውን የወሰዱ አመራሮች፣ ባለሙያዎች / ሠራተኞች አጠቃላይ ቁጥር 15 ሺህ 151

ፈተናውን የወሰዱት አመራሮች ቁጥር 4 ሺህ 213 ፤ የፈተውን ማለፊያ ውጤት ያመጡት 1 ሺህ 422 ፤ ፈተናውን ያላለፉ አመራሮች 2,791 ፤ በአጠቃላይ ፈተናውን ያለፉት 34 በመቶ አመራሮች ብቻ ናቸው።

NB. አመራሮች ለማለፍ ከ60 በመቶ በላይ ማምጣት ይጠበቅባቸው ነበር።

ፈተና የወሰዱ የሠራተኞች ቁጥር 10 ሺህ 257 ፤ ፈተናውን ያለፉት 5 ሺህ 95 ናቸው። 5,162 ሠራተኞች አላለፉም። ያለፉት 50 በመቶ የሚሆኑት ናቸው።

NB. ሰራተኞች ለማለፍ ከ50 በመቶ በላይ ማምጣት ይጠበቅባቸው ነበር።

#AAU #KotebeUniversityofEducation

@tikvahethiopia