TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አቶ ሚሊዮን ማትዮስ...

የደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳደር አቶ #ሚሊዮን_ማቲዎስ:

• አሁን ባለው ሁኔታ እንደከዚህ ቀደሙ የሲዳማን የክልልነት ጥያቄ አፍኖ ለመቀጠል አዳጋች ነው፤

• የደቡብ ክልል ከአምስት ወደ አንድ ሲጠቃለል በዴሞክራሲያዊ መልኩ ህዝቦች ተወያይተውበት፤ ቋንቋዬንና ባህሌን ለማሳደግ ይመቸኛል በሚል አይደለም፤

• ደኢህዴን ህዝበ ውሳኔ እንዲካሄድ የወሰነው ዘላቂ ሰላምን ከማረጋገጥ አንፃር ህዝቦች ያዋጣል የሚሉትን ሃሳብ ማዳመጥ ተገቢ ሆኖ በመገኘቱም ጭምር ነው፤

• የሲዳማ ክልል መሆን የክልሉን #አደረጃጀት ይቀይረዋል፤ አደረጃጀቱ ሲቀየር ደግሞ በጥናት ላይ ተመስርቶ የህዝቦች ትስስርና ጥቅም ጥናት ላይ የተመሰረተውን መነሻ ከህዝቦች ጋር ውይይትና ምክክር በማድርግ መፈፀም እንዳለበት ይታመናል፤

• ሃዋሳ ከተማን አሁንም ቢሆን የሲዳማ ዞን ዋና ከተማ ናት፡፡

#ሲዳማ_ክልል ከሆነ #ሃዋሳ የሲዳማ ክልል ዋና ከተማ ሆኖ ይቀጥላል ማለት ነው፤

• በሃዋሳ የሚኖሩ የተለየዩ ብሄር ብሄረሰቦችን በሚመለከት የሃገሪቱ ህግና ህገመንግስት በሚፈቅደው መሰረት ዜጎች የመኖር የመስራት መብታቸውን የሚያግድ ነገር ይኖራል ብለን አንገምትም።

Via EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia