TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
#Update

🗣 " ጦርነት ላይ ነን ፤ ጦርነቱንም እናሸንፋለን " - የእስራኤል ጠ/ሚ

🗣 " የከፈትነው ወታደራዊ ዘመቻ #ፍልስጤማውያን ባለፉት አስርት ዓመታት ውስጥ ለደረሰባቸው ግፍ ሁሉ ምላሽ ነው " - ሃማስ

#በእስራኤል እና #ሃማስ መካከል ግጭቱ መባበሱ ተገልጿል።

- የእስራኤል ጠ/ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ለሕዝባቸው " የእስራኤል ህዝብ ሆይ ፤ ጦርነት ላይ ነን ፤ ይህን ጦርነትም እናሸንፋለን " ብለዋል።

- የእስራኤል ሀገር መከላከያ ሚንስቴር " ሃማስ ከባድ ስህተት ሰርቷል ፤ ለዚህም የከፋ ዋጋ እንደሚከፍል እና ለውጤቱም ሁሉ ኃላፊነቱን ይወስዳል " ብሏል።

- ፈረንሳይ ፣ ዩኬ ፣ ጀርመን ፣ ጣሊያን ፣ አውሮፓ ህብረት ሃማስ የፈፀመውን ጥቃት አውግዘው ከእስራኤል ጎን እንቆማለን ፤ እራሷን የመከላከል መብት አላት ብለዋል።

- በሃማስ ጥቃት በትንሹ 22 እስራኤላውያን መገደላቸው ተነግሯል።

- በምስራቅ እየሩሳሌም አካባቢ በእስራኤል ፖሊስ እና ፍልስጤማውያን መካከል ግጭት መቀስቀሱ ተሰምቷል።

- ሃማስ ዛሬ ያለው ሁኔታ ከወራሪ ጋር የሚደረግ ጦርነት ነው ብሏል። የከፈተው ወታደራዊ ዘመቻ ፍልስጤማውያን ባለፉት አስርት ዓመታት ውስጥ ለደረሰባቸው ግፍ ሁሉ ምላሽ ነው ሲል ገልጿል።

- #ሂዝቦላህ ሃማስን #አወድሶ ቀጥተኛ ግንኙነት እያደረገ መሆኑን ገልጿል።

- ሃማስ እስካሁን 7000 ሮኬት ማስወንጨፉን ገልጿል።

- ሃማስ እስራኤል ላይ እያካሄድኩ ነው ባለው ኦፕሬሽን በርከት ያሉ #የእስራኤል_ወታደሮችን መያዙን አሳውቋል።

@tikvahethiopia