TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አዴፓ‼️

አዲስ አበባ የነዋሪዎቿ እንድትሆን እና አግላይ አመለካከቶች እንዲወገዱ በትኩረት እንደሚሠራ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አዴፓ) አስታውቋል፡፡

ድርጅቱ #በአዲስ_አበባ ከሚገኙ የአዴፓ አመራሮች ጋር ተወያይቷል፡፡ ዉይይቱን የመሩት የአዴፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ምግባሩ ከበደ ለአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት እንዳሉት አዲስ አበባ የነዋሪዎቿ እና የኢትዮጵያ መዲና እንጅ የማንም አይደለችም፡፡ አጀንዳውም ለዉጡን #የማይደግፉ ኃይሎች የሚጠነስሱት የፖለቲካ ሤራ መሆኑን ነው የተናገሩት፡፡ ‹‹ችግር የሚፈጥሩ ግለሰቦች ወይም አመራሮች ካሉም በማጣራት እና ከሚመለከተዉ አካል ጋር በመሆን ጉዳዩ ይፈታል›› ብለዋል አቶ ምግባሩ፡፡ በአዲስ አበባ ባለቤትነት ጉዳይ አዴፓ አቋሙ ጠንካራ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ እና የንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ ኢንጅነር እንዳወቅ አብጤ በበኩላቸዉ ‹‹አዲስ አበባ የራሷ መዋቀር እና አስተዳደር ያላት የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ከተማ እንጅ የማንም አይደለችም›› ብለዋል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ችግር ካለም በዉይይት እንደሚፈታና ችግር ፈጣሪዎችም እንደሚጠየቁ አረጋግጠዋል፡፡

በአዲስ አበባ የሚኖሩ የአዴፓ አመራሮችም አዲስ አበባ የሚኖረዉ የአማራ ሕዝብ መብትና ጥቅም እንዲከበር ጠንክረዉ እንደሚሠሩ ተናግረዋል፡፡

ምንጭ - አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሀሰት ነው‼️

በትላንትናው ዕለት #በአዲስ_አበባ ቦሌ ሚካኤል አካባቢ ተፈጥሮ የነበረው መጠነኛ #ግጭት የብሄር ነው፤ ቄሮ እና የአዲስ አበባ ወጣቶች ተጋጩ እየተባለ በማዕበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው ሀሰት ነው። በጉዳዩን በቅርብ የሚያውቅ የታክሲ ሹፌር የሆነ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባል የተፈጠረውን በዝርዝር አብራርቶልኛል። በማህበራዊ ሚዲያ ጉዳዩን አግዝፎ በከተማው ውስጥ እልቂት እና ነውጥ ለመፍጠር እንቅስቃሴዎች ታይተዋል። ውድ የTIKVAH-ETH ቤተሰቦች ትንሽ የምትመስለን ጉዳይ ነገ አድጋ ታጫርሰናለችና በማዕበራዊ ሚዲያዎች መረጃዎችን ለሌሎች ስታጋሩ በጥንቃቄ ይሁን።

•እውነተኛነቱን ተረጋግታችሁ አረጋግጡ
•በብዙ መልኩ አጣሩ!
•ከስሜታዊነት ይልቅ በምክንያታዊነት ላይ ተመስርታችሁ በብስለት ሁኔታዎችን አጢኑ!
•ስሜታዊነት ሀገሪቷን ለማፈራረስ ምክንያት ይሆናል እና የምፅፈውን እንጠንቀቅ!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከአዲስ አበባ...🔝

"እኛ #በአዲስ_አበባ የምንገኝ የግል #የህክምና ተማሪ እና #ዶክተሮች ነን በአሁን ሰአት #የስራም ሆነ የኢንተርንሺፕ እድል ባለማግኘታችን ፋና አካባቢ #ድምፃችንን እያሰማን እንገኛለን!"

ፎቶ: R(TIKVAH-ETHIOPIA)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ዘረኝነት ይብቃ"👆

#በአዲስ_አበባ ለመጀመሪያ ጊዜ በርካታ ሰዎች የተሳተፉበት የማስ ስፖርት በመስቀል አደባባይ እየተካሄደ ነው። ኢንጂነር #ታከለ_ኡማም ተሳታፊ ሆነዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሰበር_መረጃ

በነገው ዕለት #በአዲስ_አበባ ከተማ ሊካሄዱ የነበሩት የጠዋቱ የኦሎምፒክ ሳምንት የመክፈቻ ፕሮግራም እና የከሰዓቱ የስጦታ-ለአዲስአበባዬ ፕሮግራሞች ሙሉ በሙሉ #ተሰርዘዋል

Via Mayor Office AA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የጎርፍ እና የእሳት አደጋዎች #በአዲስ_አበባ

በአዲስ አበባ ከተማ #ቅዳሜና #እሁድ ሁለት የእሳት እንዲሁም ሶስት የጎርፍ አደጋዎች እንደተከሰቱ የእሳትና የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል፡፡ በአደጋዎቹ ሳብያም የሰው ሂወት አለመጥፋቱን የኮሚሽኑ የህዝብ ግኑኝነት ባለሙያው አቶ ሲለሺ ተስፋዬ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ራድዮ ገልጸዋል፡፡

የእሳት አደጋዎቹ የደረሱት በአዲስ ከታማ ክፍለ ከተማ መርካቶ በርበሬ በረንዳ ላይ በሚገኙ የንግድ ሱቆች ላይ ሲሆን በአደጋው ሳቢያም አንድ ሚሊየን ብር የሚገመት ንብረት ወድቧል ተብሏል። ኮሚሽኑ ሀያ ሚሊየን የሚጠጋ ንብረት ከውድመት ታዲጌያለሁ ብሏል።

ሁለተኛው የእሳት አደጋ የደረሰው በኮሊፌ ክፍለ ከተማ ወረዳ አራት ልዩ ስሙ አለም ባንክ አካባቢ በሚገኙ የንግድ ሱቆች ላይ ሲሆን በአደጋው 850 ሺ ብር የሚጠጋ ንብረት እንደጠፋና ስምንት ሚሊየን የሚገመት ንብረት ደግሞ ማዳን ተችላል፡፡

የጎርፍ አደጋዎቹ የደረሱት ደግሞ ሁለቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ ሲሆን አንደኛው በወረዳ አምስት ሶር አምባ ሆቴል አካባቢ ሲሆን ሌላኛው የጎርፍ አደጋ ደግሞ በወረዳ ሁለት ጣሊያን ሰፈር አካባቢ በመኖርያ ቤት የደረሰ የጎርፍ አደጋ ነው። በሁለቱም የጎርፍ አደጋዎች በግምት ሁለት መቶ ሺ ብር የሚገመት ንብረት መጥፋቱ ተገልጿል፡፡

Via #ኢትዮ_ኤፍኤም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#በአዲስ_አበባ ከተማ ከሰኔ 30 በኋላ በከተማዋ እንዳይንቀሳቀሱ የታገዱ ሞተር ሳይክሎች ኮድ 3 የሆነ የንግድ ታርጋ በማዉጣት በቴክኖሎጂ ታግዘዉ በከተማዋ መንቀሳቀስ እንዲችሉ እየሰራ መሆኑን የተላላኪ ኤክስፕሬስ ሃላፊነቱ የተጠበቀ የግል ማህበር አስታወቀ፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሽልማት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሽልማት (በካቢኔ ውሳኔ) ፦ 🇪🇹 ለመላው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ ቡድን 10 ሚሊዮን ብር 🇪🇹 የወርቅ ቅብ ሰሃን " እናመሰግናለን " የሚል ለኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ 🇪🇹 አትሌት ዳዊት ስዩም 250 ካሬሜትር መሬት 🇪🇹 አትሌት መቅደስ አበበ 250 ካሬሜትር መሬት 🇪🇹 አትሌት ወርቅውሃ ጌታቸው 350 ካሬሜትር መሬት 🇪🇹 አትሌት ለሜቻ ግርማ 350…
#ሽልማት

ወርቅ ያመጡ አትሌቶች #በአዲስ_አበባ 500 ካሬ ሜትር የመሬት ስጦታ ተበረከተላቸው። ሶጣታው የተበረከተው በከተማው አስተዳደር ካቢኔ ውሳኔ ነው።

🇪🇹 አትሌት ለተሰንበት ግደይ 500 ካሬ ሜትር መሬት

🇪🇹 አትሌት ጎተይቶም ገ/ስላሰ 500 ካሬ ሜትር መሬት

🇪🇹 አትሌት ታምራት ቶላ 500 ካሬ ሜትር መሬት

🇪🇹 አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ (ልዩ ተሸላሚ) 500 ካሬ ሜትር መሬት እና ወርቅ ቅብ " እናመሰግናለን " የሚል ስጦታ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update #AddisAbaba

የ2ኛውን ዙር የሀገር አቀፍ ብሄራዊ ፈተና ለመፈተን #በአዲስ_አበባ ከተማ አስተዳደር የተመዘገቡ ተማሪዎች በክፍለ ከተማቸው በኩል በ16 / 4 /2015 ዓ/ም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሳይንስና ቴክኖሎጂ 5 ኪሎ ካምፓስ እንዲገቡ የከተማው ትምህርት ቢሮ ዛሬ አሳስቧል።

የ2ኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከታህሳስ 18 እስከ ታህሳስ 21 ቀን 2015 ዓ/ም ድረስ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥ መግለፁ ይታወሳል።

@tikvahethiopia
" በክልሉ ሰላማዊ ትግል መታገል ባለመቻሉ  ነው ወደ ትጥቅ ትግል የተቀላቀልነው ፤ ... ካሁን በኃላ ታጥቆ የሚነቀሳቀስ ኃይል የለንም " - ጋነግ

የጋምቤላ ነጻነት ግንባር " ካሁን በኃላ በስሜ ታጥቆ የሚንቀሳቀስ ሀይል የለም " አለ። ቡድኑ ትጥቅ ማውረዱንም ገልጿል።

በጋምቤላ ክልል እና ደቡብ ሱዳን አዋሳኝ አካባቢዎች ሲንቀሳቀስ የነበረው የጋምቤላ ነጻነት ግንባር የተባለ ታጣቂ ቡድን በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ከመንግስት ጋር ከስምምነት ላይ ከደረሰ ወዲህ 205 አባላቱ ወደ ተሀድሶ ስልጠና መግባታቸውን አሳውቋል።

የክልሉ መንግስት በበኩሉ በሰላማዊ መንገድ ልዩነቶችን በመፍታት ታጣቂዎቹ ወደ ተሀድሶ ስልጠና መግባታቸውን ገልጿል።

የጋምቤላ ነጻነት ግንባር እና የክልሉ መንግስት ከየካቲት ወር 2015 ዓ.ም ጀምሮ በደቡብ ሱዳን #ጁባ እና #በአዲስ_አበባ ውይይቶችን ካደረጉ በኃላ ከስምምት ላይ መድረሳቸውን ተናግረዋል፡፡ 

የጋምቤላ ነጻነት ግንባር ሊቀመንበር አቶ ጋትሉዋክ ቡም ፥ በክልሉ ሰላማዊ ትግል መታገል ባለመቻሉ   ወደ ትጥቅ ትግል መቀላቀላቸውን ጠቁመዋል፡፡

ሆኖም ከመንግስት ጋር በተደረጉ ተከታታይ ውይይቶች በሰላማዊ መንገድ ለመቀንቀሳቀስ ወደ ጋምቤላ መመለሳቸውን ተናግረዋል፡፡

ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ሚያዚያ 12/2015 ዓ.ም 195 የሚደርሱት ታጣቂዎች በሰላማዊ መንገድ ትጥቅ መፍታታቸውን አመልክተዋል ሲል የጀርመን ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ ዘግቧል።

የፎቶ ባለቤት ፦ የጋምቤላ ክልል ሴክሬተሪያት

@tikvahethiopia
ጥምረት የፊልም ፌስቲቫል ሁለተኛው ቀን መርኃግብር ዛሬም ይቀጥላል!

ዛሬ በሚኖረን መርኃግብር፦

#በአዳማ ፦ "Hade Sinquee
📍በኦሊያድ ሲኒማ 🕒 ከ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ በሮች ይከፈታሉ።

#በባህርዳር ፦ " I Love You Too ብለው በሳቅ ገደሉኝ" እና "የእኔን ልጅ ሊገል አስቦ ስላልወጣ የልጄ ምትክ አድርጌዋለሁ"
📍በሙሉዓለም አዳራሽ 🕒 ከ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ በሮች ይከፈታሉ።

#በአዲስ አበባ ፦  "አንድ ሰው" ፤ "ተላላፊ" ፤ "ወሬ ነው" እና "እሱ ለራሱ ነው እንጂ ለኢትዮጵያ አስቦ አይደለም" የተሰኙ 4 ዶክመንተሪዎች ለዕይታ ይቀርባሉ።
📍በጣሊያን ባህል ማዕከል 🕒 ከ 11፡ 00 ሰዓት ጀምሮ በሮች ይከፈታሉ።

ለበለጠ መረጃ ቻናላችንን ይቀላቀሉን 👉  https://publielectoral.lat/TimretEth
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ጥምረት የፊልም ፌስቲቫል #3ኛው ቀን መርኃግብር ዛሬም ይቀጥላል!

ዛሬ በሚኖረን መርኃግብር፦

#በአዲስ አበባ ፦  "እኝህ ጀግና ገበሬ በሳቅ ገደሉኝ እና ይኸው ተጋብተናል" የተሰኙ 4 ዶክመንተሪዎች ለዕይታ ይቀርባሉ።
📍በጣሊያን ባህል ማዕከል 🕒 ከ 11፡ 00 ሰዓት ጀምሮ በሮች ይከፈታሉ።

#በአዳማ ፦ "ኢሬቻ የሰላም እና የአብሮነት እሴት"
📍በኦሊያድ ሲኒማ 🕒 ከ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ በሮች ይከፈታሉ።

#በባህርዳር ፦ "ባህላዊ የግጭት አፈታት በአባ ገዳዎች"
📍በሙሉዓለም አዳራሽ 🕒 ከ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ በሮች ይከፈታሉ።
ለበለጠ መረጃ ቻናላችንን ይቀላቀሉን 👉  https://publielectoral.lat/TimretEth
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
#አማራ_ክልል ከትጥቅ ግጭት ጋር በተያያዘ #አሳሳቢነታቸው የቀጠለ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) የተላከልን መግለጫ ከላይ ተያይዟል። @tikvahethiopia
#አማራ

በአማራ ክልል የተለያዩ ዞኖች ውስጥ ንጹሐን ሰዎች መገደላቸውንና የአካል ጉዳት መድረሱን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ።

በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ገላን ክፍለ ከተማ ጎዳና ላይ የነበሩ ሰዎች ማቆያ መገኘቱ ይፋ ተደርጓል።

በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መሠረት የታሰሩ ሰዎችም የተጠረጠሩበት ወንጀል ምርመራ በአስቸኳይ በማጠናቀቅ ፍትሕ የማግኘት መብታቸው እንዲረጋገጥ ተጠይቋል።

ኮሚሽኑ ዛሬ መስከረም 4 ቀን 2016 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ በአማራ ክልል የተለያዩ ዞኖች ንጹሐን ሰዎች መገደላቸውን እና የአካል ጉዳት መድረሱን አስታውቋል።

ኮሚሽኑ ፦
- ከነዋሪዎች፣
- ከተጎጂዎች፣
- ከተጎጂ ቤተሰቦች
- ከዐይን ምስክሮች ባሰባሰባቸው መረጃዎች መሠረት የትጥቅ ግጭቱ ወደ ክልሉ ልዩ ልዩ ወረዳዎች መስፋፋቱን ተረድቷል" ሲል የጠቀሰው መግለጫው፣ "በነዋሪዎች ላይ የሚያደርሰው ጉዳትም ተባብሶ ቀጥሏል" ብሏል።

" ለምሳሌ ከነሐሴ 19 ቀን 2015 ዓ.ም እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2015 ዓ.ም. ድረስ በተለይም ፦
- በምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረማርቆስ ከተማ፣
- በሰሜን ጎጃም ዞን አዴትና መራዊ፣
- በደቡብ ጎንደር ዞን ደብረታቦር፣
- በማእከላዊ ጎንደር ዞን ደልጊ፣
- በሰሜን ሸዋ ዞን ማጀቴ፣ ሸዋ ሮቢት እና አንጾኪያ ከተሞች እና በአካባቢዎቻቸው በሚገኙ አንዳንድ የገጠር ቀበሌዎች በግጭቱ ዐውድ በርካታ ሲቪል ሰዎች መሞታቸውን " አስታውቋል።

ኢሰመኮ አክሎ፣ " ለአካል ጉዳት መዳረጋቸውን እና የንብረት ውድመት እንደደረሰባቸው ለመረዳት ተችሏል " ብሏል።

ኮሚሽኑ በመግለጫው፣ " በተኩስ ልውውጦች ወይም በከባድ መሣሪያ ተኩስ ከሚሞቱ ሰዎች መካከል በመንገድና በእርሻ ሥራ ላይ እንዲሁም በቤታቸው ውስጥ የነበሩ ሰዎች ጭምር የሚገኙ መሆኑን ቤተሰቦች እና የዐይን ምስክሮች ያስረዳሉ " ሲል አስገንዝቧል።

" በዚሁ የግጭቱ ዐውድ በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች በመንግሥት የጸጥታ አካላት ከሕግ/ፍርድ ውጭ የተፈጸሙ ግድያዎች (extrajudicial killings) እጅግ አሳሳቢ ነው "ም ብሏል።

" ለምሳሌ ከሐምሌ 24 እስከ ጳጉሜን 4 ቀን 2015 ዓ.ም. ድረስ በተለይም ፦
- በአዴት፣
- በደብረማረቆስ፣
- በደብረ ታቦር፣
- በጅጋ፣
- በለሚ፣
- በማጀቴ፣
- በመራዊ፣
- በመርጦ ለማርያምና ሸዋ ሮቢት ከተሞች ተስፋፍተው በተፈጸሙ ከሕግ/ፍርድ ውጪ የሆኑ #ግድያዎች ሰለባ " የሆኑ ሰዎች እንዳሉ መግለጫው ያስረዳል።

ከላይ በተጠቀሱት ቦታዎች " በተፈጸመ ከሕግ አግባብ ውጭ ከሆኑ ሰዎች መካከል ቤት ለቤት በተደረገ ፍተሻ የተያዙ ሰዎች፣ በግጭቱ ወቅት መንገድ ላይ የተገኙ እና ያልታጠቁ ሰዎች፣ ' የጦር መሣሪያ ደብቃችኋል አምጡ ' በሚል የተያዙ ሰዎች፣ የሰዓት እላፊ ገደቦችን ተላልፈው የተገኙ ሲቪል ሰዎችና በቁጥጥር ስር የዋሉ የታጣቂው ቡድን (በተለምዶ ፋኖ በመባል የሚታወቀው) አባላት የሚገኙበት ሲሆን፤ በኮሚሽኑ እና በአስቸኳይ ጊዜ መርማሪ ቦርዱ አማካኝነት የተሟላ ምርመራ ሊደረግበት የሚያስፈልግ ነው " ይላል መግለጫው።

" ከዚህ በተጨማሪም የአስቸኳይ ጊዜ መምሪያ ኮማንድ ፖስት በይፋ ካሳወቃቸው እስሮችና ቦታዎች ውጪ በተለይ በአማራ ክልል፣ በኦሮሚያ ክልል እና በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በአስቸኳይ ጊዜ ዐውዱ የተስፋፋና የዘፈቀደ እስር የተፈጸመ "ም ተመላክቷል።

ኮሚሽኑ ይህን ሲያብራራም፣ "ለምሳሌ በአማራ ክልል ፦
- በባሕር ዳር፣
- በደብረ ታቦር፣
- በደብረ ማርቆስ፣
- በፍኖተ ሰላም፣
- በጎንደር፣
- በላሊበላ፣
- በመካነሰላም፣
- በቆቦ እና በሸዋ ሮቢት ከተሞች፤ በኦሮሚያ ክልል በተለይ #በሸገር ከተማ እና #በአዲስ_አበባ ከተማ የተፈጸሙ የዘፈቀደ እስሮች ይገኙበታል " ሲል አክሏል።

" ከእነዚህ ታሳሪዎች ውስጥ በደቡብ ክልል ፖሊስ ማሰልጠኛ ኮሌጅ ግቢ (በተለምዶ አቦስቶ በመባል የሚታወቀው ቦታ) የነበሩ ታሳሪዎችን ጨምሮ ከተለያየ ጊዜ መጠን በኋላ የተለቀቁ መኖራቸውን ማወቅ የተቻለ ቢሆንም፤ በአንጻሩ ገና ቁጥራቸው በትክክል ያልታወቀ ሰዎች ይህ መግለጫ እስከወጣበት ጊዜ ድረስ በእስር ላይ ይገኛሉ " ነው ያለው።

እንደ ኮሚሽኑ መግለጫ፣ " በመንግሥት የጸጥታ አካላት የሚታሰሩ ሰዎች በአብዛኛው ' ለታጣቂ ቡድኑ ድጋፍ ታደርጋላችሁ ' እና/ወይም 'የጦር መሣሪያ ደብቃችኋል ' በሚል ምክንያት ነው " ብሏል።

አክሎም ፣ " በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ገላን ክፍለ ከተማ ውስጥ ሲዳ አዋሽ ወረዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኘው ጊዜያዊ ማቆያ ማእከል ውስጥ ተይዘው የነበሩ " ሰዎች ማረጋገጡን አስታውቋል።

" ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በፊትና በኋላም ከተለያዩ ክልሎች የመጡ ሕፃናት እና ሴቶችን ጨምሮ በርካታ ውሏቸውን ጎዳና ያደረጉ ነዋሪዎች ከጎዳና ላይ ተነስተው እንዲቆዩ የሚደረግበት ቦታ መሆኑን የጠቀሰው መግለጫው ፤ በቅርቡ ወደ ማእከሉ ከተወሰዱት ውስጥ 29 ሰዎች በመታወቂያ ካርዳቸው ተለይተው እንዲለቀቁ መደረጉን " አትቷል።

አክሎም ፤ " የተወሰኑት ደግሞ በመልሶ ማቋቋም ፕሮግራም ወደየመጡበት አካባቢዎች እንዲመለሱ የተደረገ መሆኑን፣ በጣቢያው ውስጥ ተከስቶ የነበረው ተላላፊ በሽታ በቁጥጥር ስር የዋለ መሆኑን ኮሚሽኑ በክትትሉ ተመልክቷል " ብሏል።

ኮሚሽኑ በመጨረሻም የተለያዩ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን ጨምሮ ፤ " በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መሠረት የታሰሩ ሰዎችም የተጠረጠሩበት ወንጀል ምርመራ በአስቸኳይ በማጠናቀቅ ፍትሕ የማግኘት መብታቸው እንዲረጋገጥ " ሲል ጠይቋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ያዘጋጀው #ከኢሰመኮ በተላከለት መግለጫ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
🇪🇹 #NationalDialogue 🇪🇹

የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን #በአዲስ_አበባ ደረጃ ለ7 ቀናት አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደትን ትላንት አጠናቋል።

ከዚህ ጋር በተያያዘም  ፥ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች ጥያቄ እያቀረበ ፤ ማብራሪያም እየጠየቀ ይገኛል።

በብዛት ከሚነሱት ጉዳዮች መካከል አንዱ ፥ በአዲስ አበባ ከተማ ደረጃ የተመረጡ 25 ተወካዮች እውነት የወከሏቸውን የአዲስ አበባ ማህበረሰብ ክፍሎች ፍላጎት እና ሀሳብ የማንጸባረቅ ብቃቱ አላቸው ወይ ? የሚል ነው።

እንዲህ ላሉት ጥያቄ አዘል ትችቶች የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ምን ይላል ? 

ዶ/ር ዮናስ አዳዬ (ኮሚሽነር) ፦

“ ትችቶቹን #እናከብራቸዋለን። ተችዎቹ በራሳቸው አመለካከት ልክ ናቸው።

እኛ ግን በሀገራዊ ምክክር ጉባዔ ላይ የሚሳተፉ ብለን ያቀድነው 3,500 ሰዎችን ነው በአጠቃላይ።

25 ተመረጡ የተባሉት #አጀንዳውን_የሚያቀርቡልን እንጂ ተመርጠው ወደ #National_dialogue የሚሄዱ አይደሉም።

➡️ አንደበተ ርቱዕ ናቸው ?
➡️ የህብረተሰቡን ጥያቄ ያንጸባርቃሉ ? ለሚለው ጥያቄ ህዝቡ ‘ በአንጻራዊነት እነዚህ #ይሻሉኛል ’ ብሎ ከመረጣቸው መቀበል ነው ” ሲሉ መልሰዋል።

ያንብቡ 👇
https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-06-05

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ የ2017 ዓ/ም የመስቀል ደመራ በዓል አከባበር በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ። #ኦርቶዶክስተዋሕዶ @tikvahethiopia
#Ethiopia

" በ2,575 የተለያዩ ደብሮችና ቦታዎች በሰላም ተከብሮ ተጠናቋል " - የአዲስ አበባ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ

በመላው ሀገሪቱ በተለይም #በአዲስ_አበባ መስቀል አደባባይ የተከበረው የ2017 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል በሰላም መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አሳውቋል።

የፌዴራል ፖሊስ በዓሉ በሰላም እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረገው ህዝብ ፣ ለሀይማኖት አባቶች ፣ ለበዓሉ አስተባባሪ ኮሚቴዎች ፣ ለወጣቶችና በተለይ ደግሞ  የተሰጣቸውን ግዳጅ በሚገባ ለተወጡት የፀጥታ እና ደኅንነት ኃይሎች ምስጋና አቅርቧል።

በሌላ በኩል ፤ የአዲስ
አበባ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የዘንድሮው የመስቀል ደመራ በዓል በመስቀል አደባባይ ጨምሮ በ2,575 የተለያዩ ደብሮችና ቦታዎች በሰላም ተከብሮ መጠናቀቁን አሳውቀዋል።

ከንቲባዋ ፥ " በዓሉ በድምቀት እንዲከበር አስተዋፅዖ ላደረጉ የሀይማኖት አባቶች ፣ የከተማው ወጣቶች ፣ ሲያስተባብሩ ለነበሩ በየደረጃው ያሉ አመራሮች እንዲሁም ዶፍ ዝናብ ሳይበግራቸው በዓሉ ደማቅ በሆነ መንገድ እንዲከበር ላደረጉ የጸጥታ ሃይሎችና የከተማው ነዋሪዎች ሁሉ በከተማ አስተዳደሩ ስም ምስጋና እናቀርበላ " ብለዋል።

#የኢትዮጵያኦርቶዶክስተዋሕዶቤተክርስቲያን
#Ethiopia #AddisAbaba

@tikvahethiopia