TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update አብዲ ኢሌ⬆️

የሶማሌ ክልልን ለአስር ዓመታት ገደማ ያስተዳደሩት #አብዲ_ሙሃመድ_ዑመር ያለመከሰስ መብታቸው በትላንትናው ዕለት ተገፏል።

የሶማሌ ክልል ምክር ቤት ትላንት ባካሄደው መደበኛ ያልሆነ ጉባዔ ነው አብዲ ሙሃመድ ዑመርን ጨምሮ የሰባት አባላቱ ያለመከሰስ መብት እንዲነሳ የወሰነው።

ምክር ቤቱ የግለሰቦቹን መብት ያነሳበት ምክንያት በቅርቡ በክልሉ ከተነሳው አለመረጋጋት ጋር ተያይዞ እንደሆነም አስታውቋል።

የአባላቱን ያመለከሰስ መብት የማንሳት ውሳኔውንም ምክር ቤቱ #በሙሉ ድምጽ እንዳፀደቀው ነው የተገለፀው።

ከዚህ በፊት የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ ሙስጠፋ ሙሀመድን ዑመርን የክልሉ ጊዜያዊ ፕሬዝደንት አድርጎ መሾሙ አይዘነጋም።

ክልሉን ለበርካታ ዓመታት የመሩትን አቶ አብዲ ሙሐመድ ኡመርን በመተካት ለሁለት ሳምንታት ክልሉን በፕሬዚዳንትነት ሲመሩ የቆዩት አቶ አህመድ አብዲ ሞሐመድ፤ አቶ ሙስጠፋ ጊዜያዊ ፕሬዚዳንት ሆነው እንዲቀጥሉ የፓርቲው ሕገ-ደንብ እንደሚፈቅድላቸው ገልጸው ነበር።

©ቢቢሲ

📌አብዲ ኢሌ ትላንት ያለመከሰስ መብታቸው ተገፎ ዛሬ በፌደራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
@tsegbwolde @tikvahethiopia
አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን‼️

በዛሬው ዕለት አዲስ አበባ ውስጥ በተለምዶ ቦሌ ሚካኤል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ተፈጥሮ የነበረው የጸጥታ ችግር ተራ የቡድን ጸብ እንጂ ከፖለቲካ ግጭት ጋር የተገናኘ እንዳልሆነ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።

በቡድን ጸቡ ተካፋይ የነበሩትን 231 ተጠርጣሪዎች #በሙሉ በቁጥጥር ስር አውሎ ባደረገው ማጣራት ከጉዳዩ ጋር ቀጥታ ግንኙነት አላቸው የተባሉ 72 ወጣቶችን በማስቀረት ቀሪዎቹን 159 ወጣቶች በምክር #መልቀቁንም አስታውቋል።

የፖሊስ ኮሚሽኑ የኢንዶክትሪኔሽን እና የህዝብ ግንኙነት ምክትል ዳይሬክተር ኮማንደር #ፋሲካ_ፈንታ ማምሻውን ለአርትስ ቲቪ እንዳስታወቁት በወጣቶቹ መካከል የተፈጠረውን ጸብ ከቄሮ የወጣቶች ቡድን ጋር በማገናኘት የፖለቲካ ግጭት አስመስሎ የተናፈሰው ወሬ ፍጹም መሰረተ ቢስ ነው። እንደኮማንደር ፋሲካ ገለጻ የጸቡ መነሻ በአንድ የላዳ ታክሲ ሹፌር እና በአካባቢው በነበሩ ወጣቶች መካከል “መንገድ አሳልፈኝ አላሳልፍም” በሚል ጭቅጭቅ የተነሳ አለመግባባት ነው።

ትናንት መጋቢት 8 ቀን 2011 ዓ.ም ከቀኑ 10 ሰዓት አካባቢ በቦሌ ክፍለከተማ ወረዳ አንድ ክልል አየርአምባ ትምህርት ቤት ከፍ ብሎ በሚገኘው የጫት መሸጫ ሱቆች አካባቢ ተከስቶ በነበረው በዚሁ ተራ ግጭት ቂም የያዘው የታክሲ ሹፌር ወደሰፈሩ በመሄድ ለጓደኞቹ በአካባቢው ወጣቶች ጥቃት እንደደረሰበት ተናግሮ ለጸብ ሲዘጋጁ ካደሩ በኋላ በዛሬው ዕለት ወደስፍራው በመምጣት አጥቅተውኛል ካላቸው ወጣቶች ጋር ግጭት እንዲፈጠር አድርጓል።

እንደኮማንደር ፋሲካ ገለጻ ፖሊስ አስቀድሞ መረጃ ስለደረሰው ወደስፍራው ሃይል በማሰማራት ጸቡን ለመከላከል ጥረት በማድረግ ላይ እያለ በሁለቱ ሰፈር ወጣቶች መካከል በተቀሰቀ ጸብ በእንቅስቃሴ ላይ የነበሩ ሶስት ተሽከርካሪዎች መስተዋት ሲሰበር በተመሳሳይ በመስተዋት ተሰርተው የነበሩ የጫት መሸጫ ሱቆች እና በአካባቢው በሚገኝ የኦሮሚያ ባንክ ቅርንጫፍ ቢሮ መስተዋት ላይም መጠነኛ ጉዳት ደርሷል።

ፖሊስ በሁለቱም ወገን የጸቡ ተካፋይ ናቸው ያላቸውን 231 በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ ማጣራቱንና በቀጥታ በግጭቱ ተሳታፊ ናቸው ያላቸውን 67 ወንዶችና 5 ሴቶች በድምሩ 72
ተጠርጣሪዎች በእስር አቆይቶ ቀሪዎቹን 159 ተጠርጣሪዎች በሙሉ ዳግም በዚህ አይነት ጥፋት ላይ እንዳይገኙ መክሮ መልቀቁን ተናግረዋል።

ኮማንደር ፋሲካ እንዳሉት እውነታው ይኸው ሆኖ ሳለ አንዳንድ አክቲቪስቶች በማህበራዊ ሚዲያ “በቦሌ ቄሮ እና በአዲስ አበባ ወጣቶች መካከል ግጭት ተቀሰቀሰ” በማለት ባሰራጩት የሃሰት መረጃ ያልተገባና ለፖለቲካ አላማ የታቀደ ተግባር በመፈጸም የህብረተሰቡን ደህንነት ስጋት ውስጥ ለመክተት ሞክረዋል። ከተማዋ አለመረጋጋት እንደሌላት በማሰብ ብዙዎች ለደህንነታቸው ስጋት እንዲገባቸውም ምከንያት ሆነዋል። ይህ ተግባር ፍጹም ሃላፊነት የጎደለውና ማመዛዘን ከሚችል አካል የማይጠበቅ ነው ያሉት ኮማንደሩ እንዲህ አይነት የሃሰት መረጃ የሚያሰራጩ ግለሰቦችም በህዝብ ሰላምና ደህንነት ላይ ከፍተኛ ወንጀል እየፈጸሙ መሆኑን ሊገነዘቡና ሊጠነቀቁ ይገባል ነው ያሉት።

ህብረተሰቡም በዚህ አይነት #የፈጠራ_መረጃ እንዳይደናገር ያሳሰቡት የፖሊስ ሃላፊው ለማይበርድ ግጭት የሚዳርጉ የሃሰት ወሬዎችን ባለማራገብ ሰላሙን እንዲጠብቅ መልዕክት አስተላልፈዋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከዚህ ግጭት ምርመራ ጋር ተያይዞ ያሉትን ቀሪ ውጤቶች በቀጣይ ለህዝቡ ይፋ እንደሚያደርግም ኮማንደር ፋሲካ ተናግረዋል።

Via ArtsTV
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሲዳማ ህዝብ የክልል ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ የወላይታ ህዝብን የወከሉ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት #በሙሉ ድጋፍ መስጠታቸውን የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳጋቶ ኩምቤ በዛሬው ዕለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ተናግረዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዶ/ር ዳንኤል በቀለ የDAS ተሸላሚ ሆነዋል።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ (ዶ/ር) የዘንድሮው የጀርመን አፍሪካ ፋውንዴሽን (DAS) ተሸላሚ ሆነዋል።

ፋውንዴሽኑ በዛሬው ዕለት እንዳስታወቀው ዶ/ር ዳንኤል ለሰብዓዊ መብቶች መከበር ላበረከቱት የህይወት ዘመን አስተዋፅኦ ከፍተኛውን ሽልማት ለመስጠት መወሰኑን አስታውቋል።

ዶ/ር ዳንኤል ከ30 ዕጩዎች መካከል #በሙሉ_ድምፅ የተመረጡ ሲሆን ሽልማታቸውንም በኅዳር ወር እንደሚቀበሉም ተገልጿል።

ዶ/ር ዳንኤል ኮሚሽኑ ነፃ እንዲሆን ከፍተኛ ሚና መጫወታቸውን ፋውንዴሽኑ አሳውቋል።

ሽልማቱ "የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በከፍተኛ ደረጃ እንዲለወጥና ገለልተኝነቱ እንዲረጋገጥ ፣ ሥልጣንና ኃላፊነቱ እንዲሰፋ ለተጫወቱት ቁልፍ ሚና እውቅና የሚሰጥ" መሆኑ ተገልጿል።

ከ25 ዓመታት በላይ በየዓመቱ ሲካሄድ የቆየው ይህ ሽልማት ፣ በሙያቸው የላቀ አመራር ላሳዩና ለእድገትና ለመሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽዖ ላበረከቱ አፍሪካውያን እውቅና የሚሰጥ ነው።

Credit : EHRC

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የፈተና ውጤታችሁን ከነገ ጀምሮ መመልከት ትችላላችሁ። በህክምና /Medicine/ ሙያ የብቃት ምዘና ፈተና የወሰዱ ተመዛኞች የፈተናው ውጤት ከነገ ጀምሮ መመልከት ይቻላል። ከታህሳስ 21-27/2014 ዓ.ም የተሰጠውን የብቃት ምዘና ፈተና የወሰዱ የህክምና /Medicine/ ተመዛኞች ከየካቲት 01/2014 ዓ.ም ጀምሮ hple.moh.gov.et ላይ በመግባት ሙሉ ስም እና የፈተና መለያ ቁጥር…
#MoH

በህክምና /Medicine/ ሙያ የብቃት ምዘና ፈተና የወሰዱ ተመዛኞች የፈተናው ውጤት ትላንት የካቲት 1 ይፋ ሆኗል።

ተመዛኞች ከትላንት ማክሰኞ ጀምሮ በ hple.moh.gov.et ላይ በመግባት ሙሉ ስም እንዲሁም የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) በማስገባት የፈተና ውጤታቸውን እየተመለከቱ ነው።

በሌሎችም የሙያ ዘርፎች ፈተና የወሰዱ ተመዛኞች ውጤት በቅርብ ቀን ይፋ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።

በሌላ መረጃ የወለጋ ዩኒቨርሲቲ የብቃት ምዘና ፈተና የወሰዱ የ2014 የሕክምና ሳይንስ /Medicine/ ተመራቂዎች #በሙሉ ማለፋቸውን ገልጿል።

ውድ ቤተሰቦቻችን የተለያዩ የ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን መልዕክቶች በ @tikvahuniversity በኩል ማግኘት ትችላላችሁ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
159_በመንደር_የንግድ_ቁጥጥር_የአሠራር_ሥርዓት_መመሪያ_ቁጥር_159_2016.pdf
#AddisAbaba #ንግድ

የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ማህበረሰብ ያለወከባ በተረጋጋ መንፈስ የንግድ ተግባሩን ለማከናወን እንዲያስችል ዕድል ይፈጥርለታል የተባለ አዲስ መመሪያ ስራ ላይ መዋሉን ለማወቅ ተችሏል።

አዲሱ መመሪያ  " በመንደር ንግድ ቁጥጥር አሰራር ስርዓት መመሪያ 159/2016 " እንደሚባል ከአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

መመሪያው በየትኛው አስተዳደር እርከን የትኛው አይነት እርምጃ እንደሚወሰድ በግልጽ ያስቀመጠ ሲሆን ይህም ሲታይ የነበረውን ግልጽ እና ፍትሃዊ ያልሆነ አሰራር ያስቀራል ተብሏል።

በአዲሱ የመንደር ንግድ መመሪያ መሰረት የወረዳ የንግድ ቁጥጥር ባለሙያ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወስድ ህጉ የሚፈቅድለት በተመደበበት መንደር ላይ ፦
ያለ ንግድ ፍቃድ
ባልታደሰ ፍቃድ
በታገደ አልያም በተሰረዘ ንግድ ፈቃድ የሚነግድ የንግድ ድርጅት ላይ #ብቻ_ነው። ይህን ሲያደርግም ለቅርብ ኃላፊ ማሳወቅ አለበት።

ከዚህ ወጪ ያሉት ጥፋቶች #በሙሉ እርምጃ ሳይወስድ ለቅርብ ኃላፊው በፅሁፍ በማሳወቅ ለውሳኔ ወደ ንግድ ቢሮ መላክ ይጠበቅበታል ፤ የተወሰነውን ውሳኔ የማስፈፀም ኃላፊነትም አለበት።

መመሪያው ፦ https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/87886

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia