TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሸገር

" እየፈረሱ ያሉት ቤቶች #አሁንም በመንግስት መዋቅር ዉስጥ ባሉ ሃላፊዎች ይሁንታ የተሰሩ ስህተቶች መሆናቸዉን እናምናለን " ሲሉ የሸገር ከተማ ከንቲባ አስታወቁ፡፡

በቅርቡ የተቋቋመውን የሸገር ከተማ ተከትሎ በተለይ ከቤት ፈረሳ ጋር ተያይዞ በርካታ ቅሬታዎች ከመነሳታቸው ባሻገር ዜጎች በመንግስት አካላት ፍቃድ ቤቱን እንደገነቡ ቢገልጹም መፍትሄ ማግኘት እንዳልቻሉ ይገለጻል፡፡

ፍቃዱን የሰጡ የመንግስት አካላት አሁንም በሃላፊነት ቦታ ላይ ሆነው የዜጎች ቤት እንዲፈርስ እያደረጉ ነው የሚለው ቅሬታም በተደጋጋሚ ጊዜ ይነሳል፡፡

ይህን ጉዳይ አስመልክቶ ከአሃዱ መድረክ ጋር ቆይታ ያደረጉት የሸገር ከተማ ከንቲባ ዶ/ር ተሸመ አዱኛ  ፤ ባለፈው የመንግስት መዋቅር ውስጥ በነበሩ የስራ ሃላፊዎች ስህተት ቤቶቹ እንደተሰሩ እንደሚያምኑ አስታዉቀዋል፡፡

#አሁንም እነዛ ሃላፊዎች በመንግስት መዋቅር ውስጥ የሚገኙ መሆናቸውን በመግለጽ ሆኖም ግን ለሰሩት ስህተት እርምጃ አለመወሰዱ ጥያቄ እያሥነሳ ቢሆንም ካለፈው ይልቅ ስለ ወደ ፊቱ በማሰብ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ያለዉ መሰል ስህተቶች እንዳይደገሙ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ቤት እየፈረሰባቸው ያሉ ዜጎች ለሚያነሱት ጥያቄ ምንም እንኳን በከተማዋ አስተዳደር ህገ ወጥ ስለሆናችሁ ነው የሚል ምላሽ ቢሰጣቸውም #ከመንግስት_አካላት ፍቃድ አግኝተው እንደሰሩ እየገለጹ ያሉ ግን በርካቶች ናቸው፡፡

Credit : Ahadu Mederk

@tikvahethiopia
" የአሁኑ ጥቃት ከከዚህ ቀደሙ ከበድ ያለ ነበር "

የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ፤ በፊንጫ ስኳር ፋብሪካ ላይ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት 14 ሰዎች መገደላቸውን አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ለ " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " በሰጠው ቃል ፤ በኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን በሚገኘው ፊንጫ ስኳር ፋብሪካ ላይ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት 11 የፋብሪካው ሰራተኞች እና 3 የአካባቢው ነዋሪዎች መገደላቸውን አረጋግጧል።

ፋብሪካው በተፈጸመበት በዚሁ ጥቃት እና ዘረፋ ምክንያት ስራ ማቋሙም ገልጿል።

ጥቃቱ የተፈጸመው ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ ግንቦት 12 ቀን 2015 መሆኑን የገለፀው የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ፤ ፋብሪካው ባለፈው 2014 ዓ.ም እና በዚህ ዓመት ተመሳሳይ ጥቃቶችን ቢያስተናግድም፤ የአሁኑ ከዚህ ቀደም ከነበሩት " ከበድ ያለ " እንደሆነ አመልክቷል።

የፊንጫ ስኳር ፋብሪካ እና በስሩ ያለው የሸንኮራ አገዳ እርሻ፤ በአጠቃላይ በ67 ሺህ ሄክታር ይዞታ ላይ ያረፈ ነው።

የቀደሙት ጥቃቶች ይበልጥኑ ኢላማ የሚያደርጉት የፋብሪካው እርሻ ላይ እንደነበር የገለፀው ግሩፑ ታጣቂዎቹ የአገዳ እና የእርሻ ማሽነሪዎችን የማቃጠል ድርጊት ይፈጽሙ እንደነበር አስታውሷል።

የአሁኑ ከዚህ ቀደም ከነበሩት የሚለየው ታጣቂዎቹ ወደ ፋብሪካ ጭምር በመግባት ጥቃቶቹን በመፈጸማቸው እንደሆነ አመልክቷል።

የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ጥቃቱን እንዲመረምር ያቋቋመው ግብረ ኃይል ፤ በጥቃቱ 11 የፋብሪካው ሰራተኞች እና ሶስት የአካባቢው ነዋሪዎች እንደተገደሉ ማረጋገጡን ኃላፊው አስታውቀዋል።

ሰኞ ዕለት ወደ አካባቢው የተሰማራው ይኸው ግብረ ኃይል፤ እንደ ልብ ተዘዋውሮ ለመስራት የሚያስችል ሁኔታ ባለመኖሩ የደረሱ ሌሎች ጉዳቶችን እስካሁን ሙሉ ለሙሉ ለማረጋገጥ እንዳልቻለ ተነግሯል።

ሆኖም ግብረ ኃይሉ እስካሁን ባሰባሰበው መረጃ ፦

- በታጣቂዎች ከተገደሉት ሶስት የአካባቢው ነዋሪዎች በተጨማሪ ጉዳት የደረሰባቸው ሌሎች አሉ።

- ውድመት እና ዘረፋ መፈፀሙ ተረጋግጧል።

- ቢሮዎች ወድመዋል። ፋብሪካው ውስጥ ያለ መቆጣጠሪያ ኮምፒውተር ተሰብሯል።

- የእርሻ ማሽነሪዎች፣ ትራክተሮች፣ አገዳ ወደ ፋብሪካው የሚያመላልሱ የተለያዩ [ተሽከርካሪዎች] ሙሉ ወድመዋል፤ የተጎዱም አሉ።

-  የፋይናንስ ሰነዶች ወድመዋል።

- ከተዘረፉት ንብረቶች ውስጥ የተለያዩ ተሽከርካሪዎች፣ ኮምፒውተሮች እና ፕሪንተሮች ይገኙበታል።

- ታጣቂዎቹ በፋብሪካው መጋዘን ውስጥ የተከማቹ ስኳር እና የአፈር ማዳበሪያ ዘርፈው ወስደዋል።

አጠቃላይ ጉዳቱን በዝርዝር ለማወቅ የሚያስችለው ምርመራ ገና አለመጠናቀቁ ተገልጿል።

ጥቃቱን ማነው የፈፀመው ?

ጥቃቱን የፈጸሙት ታጣቂዎች ማንነት በተመለከተ የተጠየቁት የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ የህዝብ ግንኙነት እና ተሳትፎ ክፍል ኃላፊ አቶ ረታ ደመቀ ፤ በእርሳቸውን የስራ ኃላፊነት የታጣቂዎችን ማንነት ለይተው መናገር እንደማይችሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

ከቅዳሜው ጥቃት በኋላ ፋብሪካው ወደሚገኝበት አካባቢ የመከላከያ ሰራዊት አባላት እንዲገቡ በመደረጋቸው በአሁኑ ወቅት በስፍራው " የተሻለ ሁኔታ "መኖሩን ኃላፊው አስረድተዋል።

ሆኖም አሁንም ቢሆን " በእርሻ መንደሮች አካባቢ ታጣቂዎች አሉ " የሚል ስጋት በሰራተኞች ዘንድ እንዳለ አመልክተዋል።

Credit : Ethiopian Insider

@tikvahethiopia
ፎቶ ፦ በፕሪቶሪያው የ #ሰላም_ስምምነት መሰረት የህወሓት ታጣቂ ኃይሎች #የመጀመሪያው_ዙር የተሀድሶና መልሶ የማቋቋም መርሀ ግብር ዛሬ ከመቐለ ከተማ በቅርብ ርቀት በምትገኘው ኩሓ በይፋ መጀመሩን ኢፕድ ዘግቧል።

በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ወቅት ላይ መንግስት በትግራይ ያሉ ታጣቂዎችን ከልማት አጋሮች ጋር በመተባበር ወደመደበኛ ህይወታቸው እስኪመለሱ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አሳውቋል።

Photo Credit : EPA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ዕግዱ ተነሳ።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን በማህበረ ቅዱሳን የቴሌቪዥን ጣቢያ ላይ ጥሎት የነበረውን #ጊዜያዊ ዕግድ ዛሬ አርብ ማንሳቱን አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በ " ሸገር ከተማ " እየተካሔደ ያለውን የመስጅድ ማፍረስ ተግባር በመቃወም በዛሬው እለት በአዲስ አበባ የተለያዩ መስጂዶች የተቃውሞ ሰልፍ ተካሂዷል። እንደ ሀሩን ሚዲያ ዘገባ ፤ በተቃውሞው ሰልፎቹ የከተማ አስተዳደሩ እየሄደበት ያለው አካሔድ #ትክልል_አለመሆኑን እና #በአስቸኳይ እንዲያቆም የተጠየቀ ሲሆን ያፈረሳቸውንም መስጂዶች ይቅርታ ጠይቆ መልሶ እንዲገነባ ተጠይቋል። በአንዋር መስጂድ…
#Update

ዛሬ በአዲስ አበባ የተለያዩ መስጂዶች ፤ በ " ሸገር ከተማ " እየተካሄደ ያለውን የመስጂድ ማፍረስ ተግባር የሚቃወሙ / የሚያወግዙ ሰልፎች መደረጋቸው ይታወቃል።

በተለይም በ " አንዋር መስጂድ " በነበረው ተቃውሞ ወቅት የፀጥታ ኃይሎች የኃይል እርምጃ መውሰዳቸውን የአይን እማኞች ገልፀው ነበር።

የቲክቫህ ቤተሰብ አባላትም በነበረው ሁኔታ በሰዎች ላይ ጉዳት ስለመድረሱ ማመልከታቸው ይታወቃል።

ማምሻውን በተገኘ መረጃ 2 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ስለ ጉዳዩ ምን አለ ?

ዛሬ አርብ (የጁምዓ) ሶላት ከተጠናቀቀ በኋላ በመርካቶ አካባቢ " ረብሻና ግርግር " ተፈጥሮ የሰው ሕይወት አልፏል፤ ህግ በማስከበር ስራ ላይ በተሰማሩ የፖሊስ አባላት ላይ ቀላልና ከባድ ጉዳት ደርሷል ሲል ገልጿል።

በአንዋር መስጂድ የጁምዓ ሶላት ከተጠናቀቀ በኋላ በሌሎች አካባቢዎች " መስጂዶች ፈርሰዋል " በሚል ምክንያት በመርካቶ ዙሪያ በተፈጠረ " ረብሻና ግርግር " የሁለት ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ ህግ በማስከበር መደበኛ ሥራ ላይ በነበሩ የፖሊስ አባላት ላይ ቀላልና ከባድ ጉዳት ደርሷል ብሏል።

በተለይ በተለምዶ " ጋዝ ተራ " እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ተፈጥሮ በነበረ " ግርግር " ሁለት ግለሰቦች ጉዳት ደርሶባቸው ለህክምና ሆስፒታል ከተላኩ በኋላ ሕይወታቸው አልፏል ሲል ገልጿል።

እንዲሁም አራት ግለሰቦች ጉዳት ደርሶባቸዋል ያለው ፖሊስ ህግን ለማስከበር በተሰማሩ 37 የፖሊስ አመራርና አባላት እንዲሁም 15 የሚሆኑ የተለያዩ የፖሊስ አጋዥ ሀይሎች ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸው ለህክምና ተልከዋል ብሏል።

" ረብሻውን ባስነሱት አካላት " ንብረትነታቸው የአዲስ አበባ ከተማ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ድርጅት በሆኑ ሁለት አውቶቡሶች ላይ ጉዳት ደርሷል ያለው ፖሊስ ፤ " መነሻውን አንዋር መስጂድ ያደረገው ረብሻ በጋዝ ተራ ፣ ቆርቆሮ ተራ ፣ ሰባተኛ አካባቢ ፣ አመዴ እና በተለያዩ አካባቢ ለማዛመት የተሞከረ ቢሆንም በፀጥታ አካሉ ጥረት ረብሻው ሳይስፋፋ መቆጣጠር ተችሏል " ብሏል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ፤ " በአንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች በአዲስ አበባ ከፍተኛ የሆነ ረብሻ እንደተነሳ ተደርጎ እየተናፈሰ ያለው መረጃ የተጋነነ ነው " ያለ ሲሆን " አጋጥሞ የነበረው ብጥብጥ በቁጥጥር ስር ውሎ አካባቢው ወደ መደበኛው እንቅስቃሴ ገብቷል ፤ ብጥብጡን በመምራትና በማስተባበር እንዲሁም ዋነኛ ተሳትፎ የነበራቸው 114 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ሥር በማዋል በህግ አግባብ ምርመራ እየተደረገባቸው ነው " ሲል ገልጿል።

ፖሊስ " በአዲስ አበባ በህዝበ ሙስሊሙም ሆነ በዕምነት ተቋሙ ላይ የተፈጠረ ችግር ሳይኖር በሌሎች ቦታዎች ላይ መስጂድ ፈርሷል በሚል ምክንያት ህገ-ወጥ ሰልፍ በማድረግ ሁከትና ብጥብጥ በማስነሳት በሰውና በንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል " ያለ ሲሆን " በሰው እና በንብረት ላይ ጉዳት እንዲደርስ አቅደው በተንቀሳቀሱ ግለሰቦች ላይ የፀጥታ አካላት እየወሰዱት ያለውን እርምጃ አጠናክረው ይቀጥላሉ ፤ የከተማችንን ሠላምና ፀጥታ ለማወክ የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦች ከህገ-ወጥ ድርጊታቸው እንዲታቀቡ " ሲል አስጠንቅቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ዛሬ በአዲስ አበባ የተለያዩ መስጂዶች ፤ በ " ሸገር ከተማ " እየተካሄደ ያለውን የመስጂድ ማፍረስ ተግባር የሚቃወሙ / የሚያወግዙ ሰልፎች መደረጋቸው ይታወቃል። በተለይም በ " አንዋር መስጂድ " በነበረው ተቃውሞ ወቅት የፀጥታ ኃይሎች የኃይል እርምጃ መውሰዳቸውን የአይን እማኞች ገልፀው ነበር። የቲክቫህ ቤተሰብ አባላትም በነበረው ሁኔታ በሰዎች ላይ ጉዳት ስለመድረሱ ማመልከታቸው ይታወቃል።…
#Update

የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት መግለጫ አውጥቷል።

በመግለጫው ፤ " መብቱን በሰላማዊ መንገድ ለመጠየቅ በወጣ ህዝበ ሙስሊም ላይ የተወሰደው እርምጃ ፍፅም ተቀባይነት የሌለው ፣ ኢ-ፍትሃዊና ኢ-ዲሞክራሲያዊ በመሆኑ እናወግዛለን " ብሏል።

ምክር ቤቱ ፤ በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በሸገር ሲቲ የመስጅድ ፈረሳ እንዲቆምና የፈረሱትም በአስቸኳይ መተኪያ እንዲሰጣቸው እንዲሁም በጉዳዩ ዙሪያ የሚመለከታቸው አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ በተደጋጋሚ በደብዳቤ ለሚመለከተው አካል ለማሳወቅ የተሞከረ ሲሆን የመስጅድ ፈረሳው ባለመቆሙ ህዝበ ሙስሊሙ ተቃውሞውን በዛሬው እለት በአደባባይ ድምፁን በሰላማዊ መንገድ አሰምቷል ብሏል።

" ይህንንም ሰላማዊ የመብት ጥያቄ ተከትሎ በታላቁ አንዋር መስጅድ የፀጥታ አካል በወሰዱት ኢ-ህገ መንግስታዊ እና ኢ ሰብአዊ እርምጃ የሰው ሂይወት አልፋል፣ ብዙሃን ቆስለዋል። " ሲል ገልጿል።

" ይህንን አስከፊ ጥቃት የፈፀሙ እና ያስፈፀሙ የፅጥታ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ አጥብቀን እንጠይቃለን " ያለው ምክር ቤቱ " በቀጣይም የሚመለከተው አካል በኦሮሚያ ክልል በሸገር ከተማ እየተከናወነ ያለውን ድርጊት እንዲያስቆምነና ወደ ውይይት በመምጣት ስር ነቀል የእርምትና እርምጃ ተጠናክሮ እንዲተገበር አጥብቀን እንጠይቃለን " ብሏል።

ምክር ቤቱ ፤ " የሀይማኖት ጉዳይ እና የእምነት ተቋማት ጉዳይ ሁሌም ቢሆን በስክነት መታየት ሲገባው ከዚህ ቀደም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በእምነት በተቋማቱ ጉዳይ ሲከተሉት የነበረውን አካያሄድ እንደ ተሞክሮ ከመውሰድ ይልቅ በዚህ አከያሄድ የተሰራው አስነዋሪ ተግባር የሀገራችንን ብሎም የከተማችንን ሰላምና ደህንነት አደጋ ላይ እየጣለ ይገኛል። " ሲል አሳውቋል።

በሸገር ከተማ መስጅድን በተመለከተ እየተከናወነ ያለው ድርጊት፣ሀላፊነት የጎደለው፣ የህዝበ ሙስሊሙን ክብር ያዋረደ፣ ሀገራችን ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ያላገናዘበ፣ የመንግስት የለውጥ ሪፎርምን ወደ ሀላ የሚመልስ በመሆኑ ጉዳዩ እንደ ሀገር ሊታሰብበት ይገባል ሲልም አስገንዝቧል።

የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፤ በዛሬው እለት በመስጅድ ፈረሳ ሳቢያ በሰላማዊ መንገድ መብቱን ለመጠየቅ በወጣው ህዝበ ሙስሊም ላይ በተወሰደው ኢ-ህገ መንግስታዊ እርምጃ ሒይወታቸው ላለፉ አላህ (ሱ.ወ) ጀነትን እንዲወፍቃቸው፣ ለመላው ህዝበ ሙስሊምም መፅናናትን ተመኝቷል።

የከተማችንም ህዝበ ሙስሊሙ በቀጣይ ጉዳዩን በሰከነ መንፈስ እንዲከታተል አደራ ብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ዕግዱ ተነሳ። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን በማህበረ ቅዱሳን የቴሌቪዥን ጣቢያ ላይ ጥሎት የነበረውን #ጊዜያዊ ዕግድ ዛሬ አርብ ማንሳቱን አሳውቋል። @tikvahethiopia
#ምስጋና

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለባለሥልጣን መ/ቤቱ ፈጣን ምላሽ ምስጋና አቅርባለች።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በማኅበረ
ቅዱሳን ቴሌቪዥን ጣቢያ ላይ፣ ግንቦት 13 ቀን 2015 ዓ.ም. ያስተላለፈውን ጊዜያዊ እገዳ እንዲያነሳ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣  ለባለሥልጣን መ/ቤቱ ያቀረበችውን ጥያቄ በመቀበል፣ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የተጻፈለት ደብዳቤ እንደደረሰው ሳይውል ሳያድር ጊዜያዊ እገዳውን አንስቷል።

በዚህም ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ፣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ያቀረበችውን ጥያቄ በአዎንታ ተመልክቶ አፋጣኝ ተግባራዊ ምላሽ በመስጠቱ፣ ከፍ ያለ ምስጋናን ማቅረቧን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት አሳውቋል።

ፅ/ቤቱ ፤ " ለወደፊቱም ተቋማዊ ግንኙነታችንን የበለጠ በማጠናከር በጋራ ለመሥራት ዝግጁ መኾናችንን እንገልጻለን " ብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት መግለጫ አውጥቷል። በመግለጫው ፤ " መብቱን በሰላማዊ መንገድ ለመጠየቅ በወጣ ህዝበ ሙስሊም ላይ የተወሰደው እርምጃ ፍፅም ተቀባይነት የሌለው ፣ ኢ-ፍትሃዊና ኢ-ዲሞክራሲያዊ በመሆኑ እናወግዛለን " ብሏል። ምክር ቤቱ ፤ በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በሸገር ሲቲ የመስጅድ ፈረሳ እንዲቆምና የፈረሱትም በአስቸኳይ መተኪያ እንዲሰጣቸው እንዲሁም…
#Update

በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሀጂ ኢብራሒምን ጨምሮ የአዲስ አበባ መጅሊስ ፕሬዝዳንት ሀጅ ሱልጣን አማን እንዲሁም ኡስታዝ አህመዲን ጀበል በትላንትናው እለት በጸጥታ አካላት ጉዳት ደርሶባቸው የህክምና ክትትል እያገኙ ያሉ ሙስሊሞችን ሆስፒታል በመገኘት መጠየቃቸውን ሀሩን ሚዲያ ዘግቧል።

በሌላ በኩል ፥ በትላንትናው ዕለት በጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት ሼይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ የተመራ ልዑክ በታላቁ አንዋር እና ኑር ( ሰፈር በኒ) መስጂዶች ከጁምዓ ሰላት በኃላ  በሸገር ከተማ አስተዳደር  "በሕገ ወጥ" ስም የፈረሱ መስጂዶች  ተቃውሞ ለማሰማት በወጡ ምዕመናንና በፀጥታ አስከባሪዎች መካከል የተፈጠረውን ችግር  በተመለከተ ወደ ፌደራል  ፖሊስ ኮሚሽን ዋናው መስሪያ  ቤት በማቅናት ከኮሚሽኑ የስራ ኃላፊዎች ጋር  ውይይት ማድረጋቸው ተገልጿል።

በዉይይቱ መሰረትም በጊዜያዊነት በፖሊስ ተዘግቶ የነበረው ኑር (ሰፈር በኒ) መስጂድን ለሰላት ክፍት ማድረግ ተችሏል።

በቀጣይ የተፈጠሩ ችግሮችን የሚያጠናና የመፍትሔ አማራጮችን ለሚመለከተው የመንግስት አካል የሚያቀርብ ከሁለቱም ተቋማት የተውጣጣ ኮሚቴ ተቋቁሟል።

ኮሚቴው ፤ ከጠቅላይ  ምክር ቤቱ ፣ከአዲስ አበባ  እና ከኦሮሚያ  እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤቶች ከእያንዳዳቸው ሶስት አባላት ያሉት ሲሆን ስራም እንደጀመረ ተነግሯል።

ሰላም ወዳዱ ሙስሊሙ ማህበረሰብ  በሁለቱ ተቋማት የተቋቋመው  መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ የደረሰበትን ውጤት እስኪያሳውቅ ድረስ በትዕግስት እንዲጠባበቅ ጥሪ ቀርቧል።

@tikvahethiopia