TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ስሎቬኒያ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ #ማብቃቱን አወጀች!

የስሎቬንያ መንግስት የኮሮና ቫይረስ ወረርሽን ማብቃቱን በይፋ አወጀ። ሀገሪቱ ወረርሽኙ (ኮቪድ-19) ማብቃቱን ያወጀች #የመጀመሪያዋ የአውሮፓ ሀገር ሆናለች።

የሀገሪቱ መንግስት እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው ባለፉት 2 ሳምንታት ከ7 በታች አዲስ የኮሮና ቫይረስ ኬዝ መመዝገቡን ተከትሎ ነው ተብሏል።

#NIPH የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝ መቀነስ አሳይቷል ፤ ባለፉት 14 ቀናት የተመዘገበው 35 ኬዝ ብቻ ነው ብሏል።

ከተለያዩ የአውሮፓ ህብረት ሀገራት ወደ ስሎቪኒያ የሚገቡ ሰዎች ከዚህ በኃላ ኳራንታይ መግባት አይጠበቅባቸውም ተብሏል።

ከአውሮፓ አባል ሀገራት ውጭ የሚመጡና የኮሮና ቫይረስ ምልክቶች የሚታይባቸው የውጭ ዜጎች ግን ለ14 ቀናት ኳራንታይ መግባት ይጠበቅባቸዋል።

የስሎቪኒያ መንግስት የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝ ማብቃቱን ይፋ ቢያደርግም አሁንም በሽታው የመሰራጨት እድል ስላለው የመከላከል እርምጃዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጿል።

እስሁን ድረስ በስሎቬኒያ 1,465 ሰዎች በቫይረሱ መያቸው ሲረጋገጥ ከእነዚህ መኃል 103 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል፤ 270 ሰዎች አገግመዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#UPDATE የዓለም ጤና ድርጅት በቻይና የተከሰተውን የኮሮና ቫይረስ ዓለም አቀፍ የጤና ስጋት ነው በሚል አወጀ። ድርጅቱ ቫይረሱን በዓለም አቀፍ የጤና ስጋትነት ያወጀው ከቻይና ውጭ ወደ ሌሎች ሀገራት መዛመቱን ተከትሎ ነው ተብሏል። የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም እንዳስታወቁት፥ የኮሮና ቫይረስ በዓለም ጤና ስጋትነት የታወጀበት ዋነኛው ምክንያት በቻይና እየሆነ ባለው ሳይሆን…
#NewsAlert

የዓለም ጤና ድርጅት ከ3 ዓመት በኃላ ኮቪድ-19 ዓለም አቀፍ አጣዳፊ የጤና ስጋት መሆን #ማብቃቱን ይፋ አደረገ።

የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ከዚህ ቀደም አውጀውት የነበረው የኮቪድ-19 የምድራችን አጣዳፊ የጤና ስጋት አሁን ላይ ማብቃቱን አሳውቀዋል።

ይህ ውሳኔ የተላለፈው ትላንት ለዚሁ ጉዳይ የተቋቋመው ኮሚቴ ለ15ኛ ጊዜ በመገናኘት ባደረገው ስብሰባ ወቅት ባቀረበው ምክረ ሃሳብ መሆኑን ዶ/ር ቴድሮስ ገልጸው በዚህም መሰረት የኮሚቴውን ምክረ ሃሳብ በመቀበል የኮቪድ-19 ዓለም አቀፍ አጣዳፊ የጤና ስጋትነት ማብቃቱን አውጀዋል።

ይህ ማለት ግን ኮቪድ አብቅቷል ማለት እንዳልሆነ አስገንዝበዋል።

የዓለም ጤና ድርጅት እኤአ ጥር 20/2020 ላይ ነበር ኮቪድ-19 የዓለም አቀፍ የጤና ስጋት ብሎ ያወጀው።

ይኸው ወረርሽኝ በትንሹ 20 ሚሊዮን ሰዎችን ገድሏል (እንደ WHO መረጃ) ፣ በርካቶችን ቤተሰብ አሳጥቷል ፤ የዓለምን ኢኮኖሚ እንዳልነበር አድርጓል።

@tikvahethiopia