TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
አቶ ግርማ የሺጥላ ተገደሉ። የአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ የሺጥላ ዛሬ በሰሜን ሸዋ " መሀል ሜዳ " ላይ በተፈፀመባቸው ጥቃት ተገድለዋል። የአቶ ግርማን ግድያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል። ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፤ " ሐሳብን በሐሳብ ማሸነፍ ያቃታቸው አካላት የወንድማችንን የግርማ የሺጥላን ነፍስ ነጥቀዋል። " ብለዋል። ዶ/ር ዐቢይ የግድያውን ሁኔታ በተመለከተ #ዝርዝር_መረጃ…
" አቶ ግርማ የሺጥላን ጨምሮ አምስት ሰዎች ተገድለዋል " - የአማራ ክልል መንግስት

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ባወጣው የሀዘን መግለጫ በአቶ ግርማ የሺጥላ ላይ የተፈፀመው ግድያ ዛሬ ከሰዓት በኋላ፤ የመንግሥትና የድርጅት ሥራዎችን ሠርተው ከመሃል ሜዳ ወደ ደብረ ብርሃን ሲመለሱ በመንዝ ጓሳ ላይ መሆኑንና ግድያው የተፈፀመው በታጠቁ ኢ-መደበኛ ኃይሎች እንደሆነ ገልጿል።

ከእሳቸው በተጨማሪ በግል ጥበቃዎቻቸው እና ቤተሰቦቻቸው ላይ ጥቃት መፈጸሙ የተገለጸ ሲሆን እስካሁን #የአምስት_ሰዎች ሕይወት ስለማለፉ መረጃው እንደደረሰው ክልሉ ባወጣው መግለጫ ጠቅሷል።

ክልሉ በመግለጫው፥ "ይህንን የሽብር ሥራ እየሠሩ ያሉ እንዲህ አይነት ኃይሎች ላይ የክልሉ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ ይወስዳል፡፡ የጥቃቱን አድራሾችም ለሕግ ያቀርባል " ብሏል።

አክሎም፥ "የጥፋት ኃይሎች ከዚህ በላይ ዓላማ ያላቸው እና ክልሉን የማፍረስ ተልዕኮ ይዘው የሚንቀሳቀሱ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ከዚህ በኋላ የክልሉ መንግሥት እንደማይታገስ እና ጥብቅ እርምጃ እንደሚወስድ እናረጋግጣለን " ሲል ገልጿል።

@tikvahethiopia
#ቴክኖ_ሞባይል

እጅግ ዘመናዊ፣ ለአያያዝ እና አጠቃቀም ምቹ የሆነው አዲሱ ስፓርክ 10 ሲሪየስ ከቴክኖ ሞባይል ቀርቦሎታል !

ማራኪ ዲዛይን ያለው ባለ 6.8 ኢንች ስክሪን ልዮ ስታሪ ግላስ የተባለ ብርጭቆ ፓናል የተላበሰ ሲሆን ይህም ከፍተኛ ጭረት እንዲቋቋም እና ለእይታ ማራኪ  ያደርገዋል።

ሁለት ዋና ካሜራዎችን ከተጨማሪ የፍላሽ መብራት ጋር የያዘ ሲሆን ከፊት ለፊት ቁልጭ አርጎ ፎቶ ማንሳት የሚያስችል ባለ 32 ሜጋ ፒክስል ሰልፊ ካሜራ ይዞ ቀርቧል።

በየትኛውም የስልክ መሸጫ መደብሮቻችን ያገኙታል።
ለበለጠ መረጃ: Facebook, Instagram, Tiktok

ቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ
#Spark10Series #TecnoMobile #Ethiopia #Spark10pro
#ExodusPhysiotherapy

በኤክሶደስ የፊዚዮቴራፒ ስፔሻሊቲ ክሊኒክ የምንሰጣቸው የህክምና አገልግሎቶች ፦
- ለአንገት፣ለትክሻ፣ለወገብ ህመም;ከዲስክ መንሸራተት ጋር በተያያዘ ለሚመጣ ችግር፣ ለማዞር ወይንም ሚዛን የመጠበቅ ችግር፣ ለፊት መጣመም፣ ከስትሮክ በኋላ ለሚመጣ ግማሽ የሰውነት ክፍል መዛል፣ ለስፖርታዊ ጉዳቶች ፣ ከህፃናት የእድገት ውስንነት ጋር በተያያዘ ለሚከሰቱ የእንቅስቃሴ ችግሮች ፣ በአጠቃላይ ከነርቭ፣ ከጡንቻ፣ ከመገጣጠሚያ ጋር በተገናኘ ለሚከሰቱ ችግሮች መፍትሄ ያግኙ ይዳኑ !

የስራ ሰዓት ዘወትር ከሰኞ እስከ ቅዳሜ     #ከጠዋቱ 2:30 እስከ #ምሽት 1:00 ሰዓት
አድራሻችን ፦ 22 ከመክሊት ህንፃ ፊት ለፊት ባሮ ህንፃ ላይ እንገኛለን።

ስልክ ፦ 0979099909/ 0911039377
በቴሌግራም ቻናላችን ጠቃሚ መረጃ ያግኙ
https://publielectoral.lat/ExodPhysioClinic
" የግጭቱ ምክንያት ነዋሪዎችን ለማወያየት ወደ ገጠር በመጓዝ ላይ በነበረ አንድ አመራር ላይ የተፈጸመ ግድያ ነው " - አቶ ታደሰ ካይ (የደቡብ ኦሞ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪና የሰላም እና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ)

በደቡብ ክልል ፤ ደቡብ ኦሞ ዞን ሳላማጎ ወረዳ በተቀሰቀሰ ግጭት የወረዳው አመራርን ጨምሮ 11 ሰዎች ሲገደሉ ሌሎች 6 መቁሰላቸውን ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል።

የግድያ ጥቃቱ የደረሰው ከትናንት በስቲያ በመስክ ጉዞ ላይ የነበረ አንድ የወረዳ አመራር " ማንነታቸው ባልታወቁ " ሰዎች በተተኮሰ ጥይት መገደሉን ተከትሎ ነው።

ግድያውን ተከትሎ በወረዳው በሚገኙ ቦዲ እና ደሚ በተባሉ የጎሳ አባላቶች መካከል ግጭት መቀስቀሱን የአይን እማኞች ለሬድዮ ጣቢያው ገልጸዋል።

በጎሳ አባላቱ መካከል የተነሳው ግጭት የሳላማጎ ወረዳ ማዕከል ወደ ሆነችው የሐና ከተማ መዛመቱና ፤ በከተማዋ ሕይወታቸው ካለፉት መካከል ሕጻናት እና ነፍሰ_ጡሮች እንደሚገኙበት የአይን እማኞች ተናግረዋል።

የዞኑ ባለስልጣናት በሳላማጎ ወረዳ ግጭት መከሰቱን አረጋግጠው ፤ በጥቃቱ 11 ሰዎች ሲሞቱ ሌሎች 6 ደግሞ መቁሰላቸውን አሳውቀዋል።

የደቡብ ኦሞ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪና የሰላም እና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ታደሰ ካይ ለሬድዮ ጣቢያው በሰጡት ቃል፤ ነዋሪዎችን ለማወያየት ወደ ገጠር በመጓዝ ላይ በነበረ አንድ አመራር ላይ የተፈጸመው ግድያ ለግጭቱ ምክንያት መሆኑን ገልጸዋል።

የአመራሩን ሞት ተከትሎ " የእኛ ሰው ተገደለ " በሚል ሁለቱ ጎሳዎች ወደ ግጭት በመግባታቸው በተጨማሪ ሰዎች ላይ የሞት እና የአካል ጉዳት ሊደርስ መቻሉን ነው አቶ ታደሰ አመልክተዋል።

በአሁኑ ጊዜ ወረዳው እየተረጋጋ መምጣቱንና ጥቃት አድራሾችን ለሕግ አሳልፎ ለመስጠት ከአካባቢው ነዋሪዎች እና ከአገር ሽማግሌዎች ጋር ምክክር መደረጉን ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ በሰጡት ቃል አሳውቀዋል።

@tikvahethiopia
" ማኅበረሰቡ ፈፃሚዎችን ሊያወግዝና ተገቢው ማጣራት ተደርጎ ፍትኅ እንዲሰፍን የበኩሉን ድርሻ መወጣት ይኖርበታል " - አቶ ክርስቲያን ታደለ

በአማራ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ የሺጥላ ላይ የተፈፀመው ግድያን " በማንም ለምንም ዓላማ ይፈፀም ተቀባይነት የሌለው ወንጀል " መሆኑን የኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ ገለፁ።

አቶ ክርስቲያን ፤ " በወንድማችን ግርማ የሽጥላ ላይ በተፈፀመው ግድያ በእጅጉ አዝኛለሁ " ብለዋል።

" ድርጊቱ በማንም ለምንም ዓላማ ይፈፀም ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው ወንጀል ነው። " ያሉት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባሉ " ማኅበረሰቡ ፈፃሚዎችን ሊያወግዝና ተገቢው ማጣራት ተደርጎ ፍትኅ እንዲሰፍን የበኩሉን ድርሻ መወጣት ይኖርበታል " ሲሉ አሳስበዋል።

አቶ ክርስቲያን፥ በሁሉም በኩል የሚደረጉ ፍረጃዎችና የሴራ ትንተናዎች ወንጀሉን በአግባቡ በመመርመር  ገዳዮችን ለፍትህ ለማቅረብ የሚደረገውን ጥረት እንዳይጎትቱ ብርቱ ጥንቃቄዎች ሊደረጉ ይገባል ብለዋል።

" የአማራ ሕዝብ ሰላሙንና አንድነቱን እንዲጠብቅ አሳስባለሁ " ያሉት አቶ ክርስቲያን ታደለ ፤ " ለመላው ለቤተሰቦቹና ወዳጅ ዘመዶቹ ልባዊ መጽናናትን እመኛለሁ " ሲሉ ሀዘናቸውን ገልጸዋል።

@tikvahethiopia
#ELPJC

" ... የሀገራችንን የፖለቲካ ችግሮችን የአመለካከት ልዩነቶችንና ስብራቶችን እርስ በርስ በመገዳደል ለውጥ ማምጣትና ማስተካከል አይቻልም " - ምክር ቤቱ

የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መገለጫ በአቶ ግርማ የሺጥላ ላይ የተፈፀመውን ግድያ እንደሚያወግዝ እና በደረሰባቸውም አሰቃቂ ሞት በእጅጉ ማዘኑን ገልጿል።

ምክር ቤቱ " የሀገራችንን የፖለቲካ ችግሮችን፣ የአመለካከት ልዩነቶችንና ስብራቶችን እርስ በርስ በመገዳደል ለውጥ ማምጣትና ማስተካከል አይቻልም " ብሏል።

" ሥር የሰደዱ ግጭቶች እንኳን ቢሆኑ በአመጽ ሳይሆን በመነጋገር፣ በመወያየት፣ በመግባባትና በመደማመጥ፣ እንዲሁም በመተባበር ብቻ መፈታት ይኖርባቸዋል " ሲልም አስገንዝቧል።

በአቶ ግርማ ላይ የተፈፀመውን ግድያ በጽኑ እንደሚያወግዝ የገለፀው ምክር ቤቱ መንግስት ይህን አስነዋሪ ተግባር የፈጸሙ አካላትን በአፋጣኝ በቁጥጥር ስር በማዋል ተገቢውን የህግ ተጠያቂነት እንዲያረጋግጥ ጠይቋል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ

አፖሎን ተጠቅመው ቪዛ ካርድ ሲያዙ በ72 ሰዓት ውስጥ በአዲስ አበባ ከተማ በተመችዎት ቦታ ካርድዎን እናደርስሎታለን

መተግበሪያውን ኣውርደው ካርድዎን ይዘዙ።

https://apollo.bankofabyssinia.com/download-apollo

#Apollodigitalproduct #AbyssiniaDigital #Abyssiniabank #poweredbybankofabyssinia #BankofAbyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
#ኢትዮ_ቴሌኮም

በነዳጅ ማደያዎች በፍጥነት መስተናገድ ይችሉ ዘንድ ማድረግ ያለብዎትን ቅድመ-ዝግጅቶች እናስታውስዎ

⛽️ የቴሌብር አገልግሎት ተጠቃሚ ካልሆኑ ቴሌብር ሱፐርአፕን ከ onelink.to/75zfa5 በማውረድ ወይም በ*127# የቴሌብር አካውንት መክፈት

⛽️ ከቴሌብር ጋር ከተሳሰሩ 20 ባንኮች በሞባይል ባንኪንግ፣ በቴሌብር ወኪሎች እና በኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎት ማዕከሎች ገንዘብ ወደ ቴሌብር አካውንትዎ ያስተላልፉ፡፡

⛽️ ቴሌብር ሱፐርአፕን ሲጠቀሙ ቪ.ፒ.ኤን (VPN) እየተተቀሙ ከነበረ ያጥፉ

⛽️ ለተጨማሪ ድጋፍ ወደ 127 ይደውሉ ወይም በጽሁፍ ወደ 126 ወይም የቴሌብር ማህበራዊ ገጾቻችን ጥያቄዎን ይላኩ

ማስታወሻ: የነዳጅ ክፍያ በቴሌብር በመፈጸምዎ ምንም አይነት ተጨማሪ የአገልግሎት ክፍያ አይጠየቁም።

ለተጨማሪ መረጃ bit.ly/3V3wjPF
TIKVAH-ETHIOPIA
" አቶ ግርማ የሺጥላን ጨምሮ አምስት ሰዎች ተገድለዋል " - የአማራ ክልል መንግስት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ባወጣው የሀዘን መግለጫ በአቶ ግርማ የሺጥላ ላይ የተፈፀመው ግድያ ዛሬ ከሰዓት በኋላ፤ የመንግሥትና የድርጅት ሥራዎችን ሠርተው ከመሃል ሜዳ ወደ ደብረ ብርሃን ሲመለሱ በመንዝ ጓሳ ላይ መሆኑንና ግድያው የተፈፀመው በታጠቁ ኢ-መደበኛ ኃይሎች እንደሆነ ገልጿል። ከእሳቸው በተጨማሪ በግል…
#Update

ትላንት ከእነ አቶ ግርማ የሺጥላ ጋር ከተገደሉት ሰዎች መካከል አንዱ የአማራ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሹፌር የሆኑት አቶ ልየው መንጌ መሆናቸውን ፅ/ቤቱ አሳውቋል።

አቶ ልየው ፤ የአማራ ብልፅግና ቅ/ጽ/ቤት ሀላፊ የነበሩትን አቶ ግርማ የሺጥላን ይዘው ከመሀል ሜዳ ወደ ደብረ ብርሃን ሲመለሱ ትናንት ሚያዚያ 19/2015 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ በተፈፀመው ጥቃት መገደላቸውን ነው የተገለፀው።

በትላንት ከሰዓቱ ጥቃት አቶ ግርማ የሺጥላን ጨምሮ 5 ሰዎች መገደለቸው ይታወቃል።

በሌላ በኩል ፥  የአቶ ግርማ የሺጥላ የአስከሬን ሽኝት ነግ እሑድ ሚያዝያ 22/2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ ወዳጅነት አደባባይ እንደሚከናወን ቀብራቸውን ለማስፈፀም የተቋቋመ ኮሚቴ ገልጿል።

የቀብር ሥነ ሥርዓቱ በወላጆቻቸው ፍላጎት እና ጥያቄ መሰረት በተወለዱበት ሰሜን ሸዋ ዞን " ማሀል ሜዳ " እንደሚፈጸም ተገልጿል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray " በሳምንት 3 የትምህርት ፕሮግራሞች የነበሩትን ወደ 5 እና 6 በመቀየር አንድ ሴሚስተር የሚጨርሰውን ጊዜ እናሳጥራለን " - ዶ/ር ኪሮስ ጉዑሽ ትግራይ ውስጥ ትምህርት የሚጀምርበት ቀን ይፋ ተደርጓል። የትግራይ ትምህርት ቢሮ ለ4 ዓመታት በኮቪድ-19 እና በጦርነት ምክንያት ተቋርጦ የቆየውን መደበኛ ትምህርት ለማስጀመር ቀን ቆርጧል። የመንግሥትም ይሁን የግል ተቋማት ከሚያዚያ 18 /2015…
#Tigray

ከዓመታት በኃላ በትግራይ ያሉ #ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ገበታቸው ለመመለስ ምዝገበ እየተካሄደ ይገኛል።

የትግራይ ትምህርት ቢሮ  ለዓመታት በኮቪድ-19 እና በጦርነት ምክንያት ተቋርጦ የቆየውን መደበኛ ትምህርት ለማስጀመር ከሚያዚያ 18 ጀምሮ ምዝገባ እንደሚከናወን እና ሚያዚያ 23 ትምህርት እንደሚጀመር ማሳወቁ የሚዘነጋ አይደለም።

ተማሪዎች ያለፋቸውን ጊዜ ለማካካስ በሳምንት 3 የትምህርት ፕሮግራሞች የነበሩትን ወደ 5 እና 6 በመቀየር አንድ ሴሚስተር የሚጨርሰውን ጊዜ ለማሳጠር እንደሚሰራ መነገሩም ይታወሳል።

በትግራይ ጦርነት ምክንያት ክፉኛ ከተጎዱት መካከል #ተማሪዎች ዋነኛዎቹ ሲሆኑ ተማሪዎች ለበርካታ ወራት ከትምህርት ርቀው ይገኛሉ።

እንደ ህፃናት አድን ድርጅት (Save the Children) መረጃ በትግራይ 2.3 ሚሊዮን ሕጻናት ወደ ትምህርት ገበታቸው አልተመለሱም።

ፎቶ ፦ ድምፂ ወያነ

@tikvahethiopia
#BerhanBank

We Are Hiring!

Berhan Bank seeks to hire applicants for the positions of
1. Customer Service Officer
2. Junior Customer Service Officer

Link; https://publielectoral.lat/berhanbanksc
#ቴክኖ_ሞባይል

በስፓርክ 10 ሲሪየስ  ፎቶ ሲያነሱ፣ ቪዲዮ ሲቀረፁ፣ ጌም ሲጫወቱ፣ ስለ ባትሪ እንዳያስቡ !

አንዴ ቻርጅ ከተደረገ ረጅም ሰዓታት እየተጠቀሙበት የሚቆይ፥ በፍጥነት ቻርጅ ማድረግ የሚችል አዲሱ ቴክኖ ስፓርክ 10 ሲሪየ ከ 5000 mAh ባትሪ ጋር እና በ18 ዋት ፈጣን የኃይል መሙያ ድጋፍ ጋር ቀርቦሎታል። ፎቶ ሲያነሱ፣ ቪዲዮ ሲቀረፁ፣ ጌም ሲጫወቱ፣ ስልክ ላይ በመነጋገር ቢቆዩ ቴክኖ ስፓርክ 10 ሲሪየስ ባትሪ ንቅንቅ አይልም።

በየትኛውም የስልክ መሸጫ መደብሮቻችን ያገኙታል።
ለበለጠ መረጃ: Facebook, Instagram, Tiktok

ቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ
#Spark10Series #TecnoMobile #Ethiopia #Spark10pro
#IOM

እንደ ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት መረጀ በመቶዎች የሚቆጠሩ የቱርክ ዜጎችን ጨምሮ ከ3,500 በላይ ሰዎች በሱዳን ያለውን ከባድ ጦርነት ሸሽተው በመተማ በኩል ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል።

ከሚያዚያ 21 እስከ 25 ባለው ጊዜ ውስጥ ከ3500 በላይ የሆኑ የ35 ሀገራት ዜጋ  ስደተኞች ተመዝግበዋል።

ከተመዘገቡት አጠቃላይ ስደተኞች መካከል ከ40 በመቶ በላይ የቱርክ ዜጎች ሲሆኑ፣ ኢትዮጵያውያን 14 በመቶ ናቸው።

ባለፈው ሳምንት መጨረሻ 200 የነበረው የስደተኞቹ ቁጥር  ያለፈው ማክሰኞ ወደ 1,300 ደርሷል።

ድርጅቱ በሱዳን ድንበር ላይ ለሚደርሱ 700 ያህል የሶስተኛ ሀገር ዜጎችን ለመቀበል የትራንስፖርት እርዳታ በርካታ ኤምባሲዎች ጥያቄዎች  እንዳቀረቡለት ታውቋል።

የአይኦኤም ባለስልጣናት ከድንበር ከተማ መተማ ወደ ጎንደር እና አዲስ አበባ ከተሞች የሚመጡ ስደተኞች መብዛትን ተከትሎ  ትራንስፖርት በማዘጋጀት ላይ ናቸው።

ድርጅቱ የሱዳኑ ግጭት  270,000 የሚደርሱ ሰዎችን ወደ ጎረቤት ደቡብ ሱዳን ፣ ቻድ፣ ግብፅ እና ኢትዮጵያ እንዲሰደዱ ሊያደርግ ይችላል ብሏል።

በሱዳን ወታደሮች እና ታጣቂዎች መካከል የተደረገው ጦርነት ሚያዝያ 15 ቀን 2023 ከተቀሰቀሰ ወዲህ፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ሲሞቱ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ደግሞ ለስደት ተዳርገዋል።

በርካታ የሀገሪቱ ዜጎችም በከፍተኛ የውሃ፣ የምግብ፣ የመድሃኒት እና የነዳጅ እጥረት እየተሰቃዩ ነው።

በሌላ በኩል፤ ከቀናት በፊት በተፋላሚ ወገኖች ስምምነት የተደረሰበት የ72 ሰዓታት የተኩስ አቁም ለተጨማሪ ቀናት እንዲራዘም የተደረገ ቢሆን አሁንም በሀገሪቱ ግጭት ቀጥሏል።

ተኩስ አቁሙ እንዲራዘም የተደረገው በሱዳን ጎረቤት አገራት እንዲሁም በተባበሩት መንግሥታት፣ በአሜሪካ እና በዩናይትድ ኪንግደም ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ነው ተብሏል።

ምንጭ፦ አጀንስ ፍራንስ ፕሬስ / ዶቼ ቨለ

@tikvahethiopia