TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
Audio
ሃላሌ!! #ይርጋለም!!

የአገር ሸማግሌዎች፣ የሀይማኖት አባቶችና ወጣቶች የተገኙበት የሰላም ኮንፈረንስ #በይርጋለም ከተማ ተካሂዷል፡፡

ወጣቶች ጥያቄያቸው ምላሽ እስኪያገኝ ድረስ የሲዳማ "ሃላሌ" ባህላዊ ስርዓት ተከትለው በሰላማዊ መንገድ እንዲጠይቁ የሲዳማ አገር ሸማግሌዎች አሳስበዋል፡፡

"ኤጄቶዎች" ወይም የሲዳማ ወጣቶችና አገር ሸማግሌዎች የጋራ የሰላም ኮንፈረንስ ማካሄድ ከጀመሩ በኋላ ለውጥ መታየቱን የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ #ሚሊዮን_ማቲዮስ አስታውቋል፡፡

"ኤጄቶዎች" የሲዳማ የክልልነት ጥያቄ የሚረጋገጥበትን ህዝበ ውሣኔ እንዲያስፈፅም የክልሉ ምክር ቤት ለምርጫ ኮሚሽን ቢስታውቅም ዘግይቷል ሲሉ ቅሬታቸውን አሰምተዋል፡፡

ምንጭ፦ የአሜሪካ ድምፅ ራድዮ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ትኩረት በሲዳማ ዞን ለሚገኙ ከተሞችና ወረዳዎች!

📣ትኩረት #ይርጋለም #አለታ_ወንዶ #ጩኮ #ለኩ #ሀገረ_ሰላም በሚባሉ ከተሞች የሚገኙ ዜጎች አሁንም ያለው ሁኔታና አለመረጋጋት እንደሚያሰጋቸው ተናግረዋል። በአንዳንድ ከተሞች ክቡር የሆነው የሰው ህይወት ጠፍቷል። ዝርፊያ ተፈፅሟል፤ ሰዎች ህይወታቸውን ሙሉ ለፍተው ያፈሩት ንብረት ወድሞባቸዋል። መልዕክታቸውን ለTIKVAH-ETH በስልክ #ደውለው የተናገሩት የየከተሞቹ ነዋሪዎች የሚመለከተው አካል በሙሉ ከዚህ የከፋ ችግር ከመፈጠሩ በፊት ሁኔታዎችን ተቆጣጥሮ #እንዲያረጋጋ ተማፅነዋል። ሀገሪቱ ያለችበት ሁኔታ አስፈሪ ነው፤ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ለሀገር ሰላም ቅድሚያ እንዲሰጥም ጥሪ አቅርበዋል። የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ምሁራን...ሌሎችም ለሀገር እና ወገን ተቆርቋሪዎች ወጣቱን በመምከር፣ በማረጋጋት ከጥፋት በመመለስ በኩል ሀገራዊ #ሃላፊነታቸው ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በሌላ በኩል...

ሀዋሳ ከተማ #የጦርነት_አውድማ እንደሆነች ተደርጎ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሠራጨው መረጃ ከእውነት የራቀ ነው። በዚህ ፈታኝ ወቅት ሀገሪቱን ወደማያባራ ግጭት ውስጥ እድትገባ ፅኑ ፍላጎት ያላቸው የፌስቡክ አርበኞች በመኖራቸው የምንሰማቸውን መረጃዎች #በደንብ ልናጣራ እና ልንመረምራቸው ይገባል።


🚫📱💻በሲዳማ ዞን እና ዙሪያው በሚገኙ ከተሞች የኢንተርኔት አገልግሎት እንደተቋረጠ ነው። ከየከተሞቹ ነዋሪዎች በስልክ የሚደርሱኝን የተጣሩ መረጃዎች ወደናተ የማደርስ ይሆናል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ይርጋለም #ሞረቾ #አገረሰላም~የፀጥታ ሁኔታ!

ትናንት ግጭት እና ተቃውሞ በታየባት ሐዋሳ ከተማ ዛሬ አንፃራዊ መረጋጋት እንደሚታይ የጀርመን ራድዮ ገለፀ። የጀርመን ራድዮ ዘጋቢ እንደገለፀዉ ከሐዋሳ ውጪ በሞሮቾ፣ ይርጋለም እና አገረሰላም በተባሉት ከተሞች #አሁንም ግጭቶች እና አለመረጋጋቶች እንዳሉ የዓይን እማኞች ሰቅሶ ዘግቧል። በሞሮቾ የሚገኝ አንድ የዓይን እማኝ እንዳለው ወጣቶች ከመከላከያ ሠራዊት ጋር በነበራቸው ግጭት «የሚያውቃቸው ወጣቶች #ሞተዋል። መንገዶች በትላልቅ ድንጋዮች #ተዘግተዋል። ከሐዋሳ በዲላ በኩል ወደ ሞያሌ እና ኬንያ የሚወስደውም መንገድ ተዘግቷል።» አገረሠላም የሚገኙ የዓይን እማኞች እንደገለፁት ደግሞ «ትናንትና ሰዎች ሞተዋል። ወጣቶች ቤት #አቃጥለዋል።» በከተማዋ የመከላከያ ሰራዊት የገባ ሲሆን ዛሬ ላይ መጠነኛ መረጋጋት ይታያል። «ሆኖም ከተማዋ ውስጥ ዛሬም አልፎ አልፎ ተኩስ ይሰማል።» የሲዳማ ዞን ፖሊስ በሐዋሳ አጎራባች አካባቢዎች አሁንም አለመረጋጋት መኖሩን ለ ጀርመን ራድዮ አረጋግጧል። በሲዳማ በተለያዩ አካባቢዎች የታዩትን አለመረጋጋቶች ተከትሎ ደረሰ ስለተባለዉ ጉዳት ግን ፖሊስ መረጃ በማሰባሰብ ላይ እንደሆነ ተገልጿል።

Via #DW
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ይርጋለም

በይርጋለም ከተማ የክልሉ ገዢ ፓርቲ/ደኢህዴን/ ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ባጢሶ ባቲሶ በከተማው ከትናንት ማለዳ ጀምሮ አለመረጋጋት ተፈጥሮ እንደነበር አረጋግጠዋል። በዚህም አራዳ በሚባል አካባቢ የሰባት ግለሰቦች መኖሪያ ቤቶች፣ በሌላ ስፍራ ደግሞ ሦስት ቤቶች #መቃጠላቸውን፣ የዱቄት ፋብሪካ መቃጠሉን፣ የከንቲባውና የድርጅት ጽህፈት ቤቱ መኪኖች፣ የበጎ አድራጎት ድርጅት መኪና፣ የአረጋሽ ሎጅ ሦስት መኪኖች መቃጠላቸውን ተናግረዋል።

Via #BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሲዳማ ዞን ከተሞች እንዴት ዋሉ? የዛሬው ሁኔታ ምን ይመስል ነበር? #ሀዋሳ #ይርጋለም #ወንዶገነት #ለኩ #ሀገረሰላም

ከ20 ደቂቃ በኃላ እመለሳለሁ!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሀዋሳ

ካለፉት ሁለት ቀናት የተሻለ ሰላም እና መረጋጋት በዛሬው ዕለት ነበር። ከተማዋ ወደቀደመው እንቅስቃሴዋ እየገባች ነው። የተወሰኑ ባጃጆች እና ታክሲዎች ሲንቀሳቀሱ ነበር/ከመናኸሪያ ሞቢል-ፒያሳ የታክሲ እንቅስቃሴ ነበር/። ብዙሃኑ የንግድ ቤቶች ተዘግተው ነው የዋሉት። አብዛኞቹ ባንክ ቤቶችም ዝግ ነው የዋሉት። በየሰፈሩ ያሉ ሱቆች ተከፍተው ደምበኞቻቸው ሲያስተናግዱ ነበር። እንደሰማሁት ከሆነ በሸቀጦች ላይ መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ ታይቷል። ከሁከቱ ጋር ግንኙነት አላቸው የተባሉ ተጠርጣሪዎችን አሁንም የፀጥታ አካላት እያሰሩ እንደሆነ ከከተማው ነዋሪዎች ሰምቻለሁ። ከትላንት ምሽት ጀምሮ የመጠጥ ውሃ ተመረዘ ተብሎ ሲናፈስ የነበረው ወሬም ሀሰትና ህዝቡን ለማሸበር የተደረገ እንደሆነ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች በሚዲያ ገልፀዋል።

#ይርጋለም

ባለፉት ሁለት ቀና ከፍተኛ የፀጥታ ችግር የነበረባት እድሜ ጠገቧ ይርጋለም ከተማ ዛሬ ፀጥ ረጭ ብላ ውላለች። በከተማው ምንም አይነት እንቅስቃሴ አልነበረም። ሱቆች፣ ባንኮች፣ ሆቴሎች ዝግ ነው የዋሉት። በከተማይቱ ውስጥ የመከላከያ እና የፌዳራል የፀጥታ ሃይላት በመኪና ሲዘዋወሩ እንደነበር የከተማው ነዋሪዎች ተናግረዋል።

#አለታወንዶ

ባለፉት ሁለት ቀናት በአለታ ወንዶ የነበረው የፀጥታ ችግር ዛሬ መጠነኛ መሻሻል አሳይቷል። ከተማዋ ሙሉ በሙሉ ከእንቅስቃሴ ውጭ ሆናለች። ሰዎች አልፎ አልፎ ካልሆነ አይንቀሳቀሱም። አንዳንድ ሱቆች ተከፍተው ነበር። ልክ እንደሀዋሳ በአለታ ወንዶ ከተማ የዋጋ ጭማሪ ነበር። ያነጋገርናቸው ነዋሪዎች እንደገለፁልን ከተማውን ወደቀደመው ሰላማዊ እንቅስቃሴ ስራዎች እየተሰሩ ነው። ካለፉት ሁለት ቀናት ዛሬ ከተማዋ ትሻላለች።

ይቀጥላል👇
#አምቦ #ለኩ #ጅማ #ከሚሴ #ይርጋለም #ሃዋሳ #ሶዶ

ኑ ትውልድ እንገንባ!

#አዲስ_አበባ
0970514616/ዮናስ ገ/መስቀል/
0924140293/መባ/

#ሰበታ
0932540523/ያሬድ ለማ/
0921421493/ያብስራ ካሳ/

#መቐለ
0912178520/ኤርሚያስ ደጀኔ/
0923602445/ፊራኦል መስፍን/

#ራያ_ቆቦ
+251949256094/ሉላይ/

#ጅማ
0911670454/አሰፋ/

#ድሬዳዋ
0915034762/መሃሪ/

#አዳማ
0949377735/ሰላም/

#ሀዋሳ
+251926429534/ተስፋ/
+251935932153/ብስራት/

#ለኩ
0919687777/ዳዊት እንዳለ/

#ይርጋለም
0953804369-/አሸናፊ/
0964039768-ብርሀኑ/

#ከሚሴ
0915543171/ሁሴን/

#ወላይታሶዶ
+251913776084/Aso/
0926172318/Beza/

•ከ1ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ መደበኛ የመማሪያ እና አጋዥ መፅሃፍትን በመለገስ ለመጭው ትውልድ የተሻለች ኢትዮጵያን እናውርስ!!

📚የዘንድሮው አመት ተፈታኝ ተማሪዎች እና ወላጆች በዚህ ስራ ላይ በስፋት በመሳተፍ ለመጭው ትውልድ አርዓያ ትሆኑ ዘንድ ጥሪያችንን እናቀርባለን!

5ኛው አመት የTIKVAH-ETHIOPIA የመፅሃፍት ማሰባሰብ ዘመቻ!

በዚህ ሀገራዊ ስራ መሳተፍ የምትፈልጉ የበጎ አድራጎት ማህበራትና ግለሰቦች @tsegabwolde

በሁሉም ከተሞች ያሉ አስተባባሪዎችን በየዕለቱ እናሳውቃለን!

@tsegabwolde @tikvahethiopia