TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
‹‹ከከሰልና #እንጨት ጋር አብረን እንድንጓዝ ተገደናል፡፡›› ነዋሪዎች
.
.
በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ከከሚሴ በደዌ ሃረዋ በሚወስደዉ መንገድ ነዋሪዎች በትራንስፖርት ችግር #እንግልት እየደረሰባቸዉ ነዉ፡፡ የሚመደቡ የህዝብ ማመላለሻ አዉቶብሶች በቂ ባለመሆናቸዉ በአንድ አዉቶብስ ከ100 እስከ 120 ሰዎች እንደሚጓጓዙ የአካባቢዉ ነዋሪዎች ተናግረዋል።

የአካባቢዉ ህብረተሰብ እንደ አማራጭ #የጭነት መኪኖችን ለመጓጓዣነት እየተጠቀመባቸዉ ነዉ፡፡ የአካባቢዉ የትራንስፖርት ችግር ነዋሪዎችን በአይሱዙ መኪኖች ከከሰልና እንጨት ጋር አብረዉ እንዲጓዙ አስገድዷቸዋል፡፡ ለትራፊክ አደጋ #እያጋለጣቸዉ መሆኑን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል፡፡

ለአብነት በቅርቡ በደረሰ #የትራፊክ_አደጋ የ12 ሰዎች ህይወት ማለፉን ተሰምቷል፡፡ የደዌ ሃረዋ ትራፊከ ፖሊስ ምክትል ሳጅን መሃመድ ጀማል ህብረተሰቡ የሚያስፈልገዉን የትራንስፖርት አገልግሎት እያገኘ አለመሆኑ ይታወቃል በተደጋጋሚ ትርፍ የሚጭኑትን አሽከርካሪዎች እየቀጣን ነዉ፣ ሆኖም መፍትሄ አልመጣም ብለዋል፡፡ የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ተቀዳሚ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ ሃሰን በብሄረሰብ አስተዳደሩ የሚታየዉን የትራንስፖርት ችግር ለመፍታት ግብረ ሃይል ተቋቁሞ እንቅስቃሴ መጀመሩን ገልፀዋል፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ትኩረት~~ማንቡክ ለሚገኙ ዜጎች‼️

በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ዳንጉር ወረዳ ማንቡክ ቀበሌ እየተፈፀመ ያለውን የዜጎች #ስቃይ እና #እንግልት የፌደራሉ መንግስት በአስቸኳይ ሊያስቆመው ይገባል፤ ወንጀለኞችንም ሳይውል ሳያድር ለፍርድ ሊያቀርብ ይገባል። ዜጎች በገዛ ሀገራቸው ወጥተው ለመግባት #የሚሳቀቁበት እና #የሚፈሩበት ምክንያት ሊኖር አይገባም።

ለሀገር መከላከያ ሰራዊት
ለፌደራል ፖሊስ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
" መንግሥት የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችን እስር እና እንግልት ያቁም " - የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማሕበር

የኢትዮጵየ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማህበር ባወጣው መግለጫ ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ ባለሙያዎች የሚሰሩበት አውድ እየጠበበ ጋዜጠኞች ስራቸውን በነፃነት እንዳይሰሩ በመንግስት የፀጥታ አካላት #እየተሸማቀቁ እና #እንግልት እየደረሰባቸው እንደሆነ መታዘቡን ገልጿል።

ከሰሞኑን ፤ የማህበሩ መስራችና የስራ አስፈፃሚ አባል እንዲሁም የማህበሩ የህዝብ ግንኙነት ክፍል ኃላፊ ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻውን ጨምሮ ፦
👉 ጋዜጠኛ አራጋው ሲሳይ ፣
👉 ጋዜጠኛ ገነት አስማማው ፣
👉 ጋዜጠኛ ጌትነት አሻግሬ ፣
👉 ጋዜጠኛ በየነ ወልዴ፣
👉 ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ አስፋው በመንግስት ሀይሎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አሳውቋል።

አንዳንዶቹ ያሉበት ቦታ እና ምን ሁኔታ ላይ እንዳሉ እንኳን ቤተሰቦቻቸውም በቂ መረጃ ሳይኖራቸው በእስር ላይ ይገኛሉ ብሏል።

ማህበሩ ፤ ጋዜጠኞች ያለ ፍርድ ቤት ማዘዣ እየታሰሩ፣ እየታፈኑና ቤታቸውና ቢሯቸው እየተበረበረ መሆኑ ባለሞያዎች ስራቸውን በነፃነት እንዳይሰሩ፤ የፕረስ ምህዳሩ የበለጠ እንዲጠብ እያደረገ ነው ሲል ገልጿል።

ማህበሩ የተቋቋመው እንደዚህ አይነት ሙያውን የሚያቀጭጩ ጫናዎችን ለመታገል መሆኑን በመግለፅ የመንግሥት እርምጃዎችን በፅኑ አውግዟል።

ጋዜጠኞች በወንጀል ሲጠረጠሩ ጉዳያቸውን እስር ቤት ሳይቆዩ መከታተል እንደሚችሉ ከሁለት ዓመት በፊት በወጣው በመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቢደነገግም ይህ ግን #ተግባራዊ_አለመደረጉ ማህበሩ እንደሚያሳስበው ገልጿል።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማሕበር መንግስት፦
- የፕረስ ነፃነት እንዲረጋገጥ
- ያጸደቃቸውን ህገ-መንግስታዊና ዓለም አቀፋዊ ህጎች እንዲያከብርና ውስጡን እንዲፈትሽ
- ያለምንም የህግ አግባብ ያሰራቸውን የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች በአስቸኳይ እንዲፈታ
- ባለሙያዎች ላይ የሚያደርሰውን ማሸማቀቅ እንዲያቆም ጠይቋል።

@tikvahethiopia