TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ኢትዮ ቴሌኮም⬇️

‹‹ከሁለት የስልክ ቀፎዎች በላይ ወደ ሀገር #ማስገባት አይቻልም የሚለው ገደብ ተነስቷል፡፡››
.
.
ኢትዮ ቴሌኮም ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡም ሆነ ከሀገር ውስጥ የሚገጣጠሙ የስልክ ቀፎዎችን ለማስከፈት ወደ ጉምሩክ እና ኢትዮ ቴሌኮም መስሪያ ቤቶች መሄድ እንደማያስፈልግ ኢትዮ ቴሌኮም አስታውቋል፡፡

የስልክ ቀፎዎች አገልግሎት ከመጀመራቸው በፊት በኢትዮ ቴሌኮም እና በጉምሩክ በኩል ህጋዊነታቸው እንዲረጋገጥ ሲደረግ ቆይቷል፡፡

ዓላማውም ህገ ወጥነትን ለመከላከል ተብሎ እንደ ነበር ይታወቃል፡፡ አሰራሩም ወጥነት የሌለው፣ክፍተቶች ያሉበት እና ደንበኞችን ከማጉላላት ባለፈ የጎላ ፋይዳ ያልታየበት መሆኑን የኢትዮ ቴሌኮም የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አብዱራሂም አህመድ ለአብመድ ተናግረዋል።

ከሁለት የስልክ ቀፎዎች በላይ ወደ ሀገር ማስገባት እንደማይቻል የሚከለክለው እገዳም ተነስቷል ነው ያሉት አቶ አብዱራሂም፡፡ በመሆኑም IMI ቁጥር ያላቸውን ማለትም ደረጃውን የሚያሟሉ የስልክ ቀፎዎችን ኢትዮጵያ ውስጥ መገልገል እንደሚቻል አረጋግጠዋል፡፡

በመሆኑም ወደየተቋማቱ መሄድ ሳያስፈልግ አዳዲስ የስልክ ቀፎዎችን #መገልገል ይቻላል፡፡

ኢትዮ ቴሌኮም በዘርፉ የሚስተዋሉ የኮንትሮባንድ እና የቴሌኮም ማጭበርበርን ለመግታትም ዘመናዊ ቴክኖሎጅዎች ተግባራዊ ያደርጋል
ነው ያሉት፡፡ እንደ አቶ አብዱራሂም መረጃ የታሪፍ ቅናሽ አና የስልክ ቀፎዎችን አለማስመዝገብ ከትናንት ነሀሴ 17/12/10 ዓ.ም ጀምሮ #ተግባራዊ ተደርጓል፡፡

©አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia