TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ADHD

የስዊድን መንግሥት ፦
° ጥንቃቄ የጎደለው ትኩረት የማጣት፣
° ከፍተኛ የመቅበጥበጥ፣ 
° ብዙ የማውራት፣
° ግትርነት
° እራስን የመግዛት ቀውስ (ADHD -attention deficit hyperactivity disorder) ችግር በብዛት የሚታይባቸው ልጆች በሀገሪቱ ቁጥራቸው መጨመሩን ዛሬ አስታወቀ።

የሀገሪቱ የማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በሰጠው ቃል የስዊድን የጤና እና ደህንነት ቦርድ መረጃ ADHD ተብሎ የሚገለጸው #የአእምሮ_ጤና_ችግር እ.ኤ.አ. ከ2022 ጀምሮ 10 በመቶ በሚሆኑ ወንዶች ልጆች ላይ እንዲሁም 6 በመቶ በሚሆኑት አዳጊ ሴት ልጆች ላይ በምርመራ መታየቱን ይፋ አድርጓል።

የችግሩ ተጋላጭ ልጆች ቁጥር ሊጨምርም ይችላል ተብሏል።

በመላው ዓለምም ከ5 እስከ 7 በመቶ የሚሆኑ ልጆች ለዚህ ችግር የተጋለጡ ናቸው።

ለዚህ ችግር የሚያጋልጡ ምክንያቶች ፦
- የተለያዩ እንደ ሊድ ወይም እርሳስ ባሉ ማዕድናት የተበከለ አካባቢ መኖር፣
- በእርግዝና ወቅት መድኃኒቶች፣ አልኮል ወይም ሲጋራ / ትንባሆ ማጨስ ማዘውተር ሊሆኑ እንደሚችሉ ይገመታል።

ከዚህም በተጨማሪ በደም አማካኝነት በዘር የአእምሮ ህመሞችም ሊተላለፉ እንደሚችሉ ነው የተገለጸው።

ይህ የአእምሮ ችግር (ADHD) ያለባቸው ልጆች ቁጥር ለምን እንደጨመረ መንስኤውን ለማወቅ ጥናቶች እየተካሄዱ ነው።

#DeutscheWelle

@tikvahethiopia