TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#እንድታውቁት #ለጥንቃቄ

" በካፒታል ገበያ አዋጅ መሰረት የቀረበ የአክስዮን ሽያጭ " በሚል የሚቀርቡ ማስታወቂያዎች እውቅና  የላቸውም ተብሏል።

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ፤ አንዳንድ ኩባንያዎች " በካፒታል ገበያ አዋጅ መሰረት የቀረበ የአክስዮን ሽያጭ " በሚል የሚያስነግሩት ማስታወቅያ እውቅና የሌለው ነው ሲል አሳውቋል።

አንዳንድ ኩባንያዎች " በካፒታል ገበያ አዋጅ መሰረት የቀረበ የአስክሲዮን ሽያጭ " በሚል ማስታወቂያ እያስነገሩ አክሲዮን እየሸጡ እንደሆነ ደርሼባቸዋለሁ ያለው ባለስልጣን መ/ቤቱ ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ መክሯል።

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የአክስዮን ሽያጮችን መመዝገብና ማጽደቅ እንዳልጀመረ ገልጾ አሁን ላይ የአክስዮን ምዝገባ የሚያደርግበትንና የደንበኛ ሳቢ መግለጫ የሚያጸድቅበትን የህግ ማዕቀፍ በማዘጋጀት ላይ እንደሚገኝ አስገንዝቧል።

አክስዮን ሻጭ ኩባንያዎችም የአክስዮን ሽያጭ ሂደቱ በባለስልጣኑ ታይቶ ባልጸደቀበትና ባልተመዘገገበበት ሁኔታ ሽያጩ በካፒታል ገበያ አዋጅ መሰረት የተዘጋጀ እንደሆነ በማስታወቅያ ማስነገር ህብረተሰቡን የሚያሳስት ነው ብሏል።

የዚህ አይነት አሳሳች የሆኑ የአክስዮን ሽያጭ ማስታወቅያዎችን በማንኛውም መንገድ በሚያስነግሩ ኩባንያዎች ላይ የባለስልጣን መ/ቤቱ በካፒታል ገበያ አዋጅ አንቀጽ 106 በተሰጠው ስልጣንና ኃላፊነት መሰረት አስፈላጊውን ህጋዊ እርምጃ የሚወስድ መሆኑንም አስጠንቅቋል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል።)

Via @TikvahethMagazine
#ለጥንቃቄ

" በፎሬክስ ትሬዲንግ የኦንላይን ስራ ትርፋማ እናደርጋችኋለን " የሚል የፌስቡክና የቴሌግራም ማስታወቂያ በሚያስነግሩ የተደራጁ ቡድኖች መጭበርበራቸውን ተበዳዮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል። 

እነዚህ የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገጾች ስያሜአቸው ከፎሬክስ ትሬዲንግ ጋር የተያያዘ ሲሆን " ትሬድ እናደርጋለን ትርፋማ ትሆናላችሁ " የሚል ቃል በመግባት ከሰዎች ገንዘብ እያስላኩ የማጭበርበር ስራ ላይ መሰማራታቸውን ተበዳዮች ገልፀዋል።

የሚጠቀሙት የማጭበርበር ስልት ምንድነው ?

አጭበርባሪዎቹ በማኅበራዊ ሚዲያ በተለይ በፌስቡክ እና በቴሌግራም ሌሎች ሰዎችን ለመሳብ " እኔ 10 ሺ ብር ኢንቨስት አድርጌ 180 ሺ ብር አግኝቻለሁ እናንተም ኢንቨስት አድርጉ " የሚል የምስክርነት ቪዲዮ አሰርተው ይለቃሉ።

መልዕክቶቹንም በፌስቡክ #Sponsored በማድረግ ብዙ ሰው ጋር ተደራሽ እንዳደረጉት ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተመልክቷል።

አጭበርባሪዎቹ ሰዎችን የሚቀርቡት ስማቸውን ፤ አድራሻቸውን ፤ ፎቶአቸውን የውጪ ሀገር ዜጋ አስመስለው ሲሆን በተጨማሪም የውጪ ሃገር የቢዝነስ አማካሪ እንደሆኑ ጭምር ያስመስላሉ።

አጭበርባሪዎቹ የውጪ ሃገር ሰው እንደሆኑ ያስመስሉ እንጂ ገንዘቡን የሚያስልኩት በሀገር ውስጥ ባንኮች መሆኑን ተበዳዮች ለቲክቫህ ከላኩት ማስረጃ ማየት ተችሏል።

በርካታ ተበዳዮች ስለ ፎሬክስ አሳሳች የቪዲዮ ምስክርነት የሚሰጡ ሰዎችን ተመልክተው 10ሺ ብር ለቡድኑ በመላክ መጭበርበራቸውን ገልፀዋል።

ተበዳዮች ገንዘቡ እንዲመለስላቸው ሲጠይቁ ገንዘባቸው ኢንቨስት ስለተደረገ ገንዘቡን ለማስለቀቅ ተጨማሪ 36ሺ ብር ሲጠየቁ ሌሎች ተበዳዮችን ደግሞ "10 ሺ ኢንቨስት አድርጌ 180ሺ አትርፌአለሁ" የሚል የቪዲዮ ምስክርነት በኢንግሊዝኛና አማርኛ ቋንቋ ቀርፀው ከላኩ ገንዘቡን እንመልሳለን ብለው እንዳታለሏቸው አስረድተዋል።

ተበዳዮች ገንዘባቸው እንዲመለስላቸው ገፍተው መጠየቅ ሲጀምሩ ቡድኖቹ አድራሻቸውን አጥፍተው እንደሚሰወሩ ተበዳዮች ሲገልፁ ቀርፀው የላኩትን ቪዲዮ ሌሎችን ለማታለል እያዋሉት እንደሆነ በማየታቸው ሌሎች ሰዎች በእንደዚህ አይነት ማታለያ ከመጭበርበር እራሳቸውን መጠበቅ እንዳለባቸው አስጠንቅቀው ፥ አጭበርባሪዎቹን የሚመለከተው የህግ አካል ሊከታተላቸው እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።

ሊደረግ የሚገባ ጥንቃቄ ምንድነው ?

- ማኛውም ገንዘባችሁን አምጡ እያሉ በኦንላይን ለሚጠይቁ አካላት ፦
• ማንነታቸውን በትክክል የሚገልፅ መታወቂያ እንዲልኩ
• የሚሰሩበትን አድራሻ (ሀገር፣ ከተማ፣ አካባቢ) እና ከትክክለኛው አካል ህጋዊ ፍቃድ እንዳላቸውና እሱን እንዲልኩ መጠየቅ ይገባል።

- በተለይም በቴሌግራም ሆነ ፌስቡክ የሰማያዊ ማረጋገጫ ምልክት (✅️) መግዛት ቀላል ስለሆነ ይህ ምልክት ያለበት ሰው እውነተኛ እና ታማኝ ነው በሚል የተሳሳተ አመለካከት እንዳትጭበረበሩ ተጠንቀቁ። ማንኛውም ሰው ይሄን ምልክት እየገዛ የተረጋገጠና እውነተኛ ታማኝ ሰው ለመምሰል ይሞክራል።

- " በትንሽ ብር ብቻ እጅግ ብዙ መቶ ሺዎች የሚገኝበት ነው " ስንባል እንዲህ የሚሉንን ሰዎች በበቂ ጥያቄ ማፋጠጥ፣ እያንዳንዱ አካሄዳቸውን መመርመር፣ በሌሎች በርካታ መንገዶች ሰዎቹን በጥያቄ መፈተሽ ይገባል።

ይወያዩ ፦ @BirlikEthiopia

Via 👋  @TikvahethMagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#ለጥንቃቄ

በ " ፌስቡክ " እንደልብ በሚተዋወቁ መልዕክቶች ምክንያት በርካታ ወጣቶች ውድ ጊዜያቸውን እና ገንዘባቸውን እየተባሉ እየተጭበረበሩ ነው።

" ፌስቡክ " ላይ ግለሰቦች ክፍያ ከፈፀሙ " Sponsored " የሆኑ መልዕክቶችን ብዙ ሺህ ተጠቃሚዎች ጋር ያደርሳሉ።

ተቋሙ ገንዘብ እየተቀበለ የማያሰራጫቸውን መልዕክቶች ትክክለኝነት እያረጋገጠ ይሁን አይሆን የሚታወቅ አንዳች ነገር ባይኖርም በርካቶች ግን በሀሰተኛ መልዕክቶች ወጣቶች እየተጭበረበሩ ይገኛሉ።

ከሰሞኑን ስለ " ሀሰተኛ የትሬድ ስራ " እና በዛ ምክንያት ገንዘባቸው ተበልቶ እና መፍትሄ አጥተው ስለተቀመጡ ሰዎች ዳሰሳ መስራታችን ይታወሳል።

ለዛሬ ደግሞ በተመሳሳይ መልክ ስለሚደረግ ማጭበርበር በአጭሩ እንመለከታለን፤ ይኸውም ዋና ዓላማቸው ስራ የሌላቸውን ወጣቶች እና ሌሎች የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎችን በሀሰተኛ መልዕክቶች አታሎ ገንዘባቸውን ማጭበርበር ነው።

በፌስቡክ ላይ ስፖንሰር በሚሆን መልዕክት  "
- ስራ የሌላችሁ ስራ እንቀጥራችኃለን፣ 
- በቀን ውስጥ ከ20 ሺህ ብር በላይ ትሰራላችሁ ፣
- በአጭር ጊዜ ውስጥ ጥሩ ገንዘብ በማግኘት የራሳችሁን ስራ ትጀምራላችሁ " የሚሉ የማጭበርበሪያ መልዕክቶች በስፋት ሲሰራጩ ተመልክተናል።

ወጣቶች እነዚህን አካላት ለዚሁ ጉዳይ በሚያናግሯቸው ጊዜ በቅድሚያ የምዝገባ ገንዘብ ይጠይቋቸዋል፤ በኃላም የውሃ ሽታ ይሆናሉ።

የወጣቶችን ስራ ማጣት እንደ አጋጣሚ ተጠቅመው ከሌላቸው ገንዘብ ላይ ለመንጠቅ የሚሰሩት እነዚህ አስነዋሪ አጭበርባሪዎች መልዕክታቸውን ተደራሽ ለማድረግ የተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎችን የሚጠቀሙ ቢሆንም በይበልጥ የተከፈለባቸው የ " ፌስቡክ " መልዕክቶች ዋነኛዎቹ ናቸው።

ምን ጥንቃቄ ማድረግ አለብን ?

- አንድ የስራ ማስታወቂያ ስንመለከት ስራው የት እንደሆነ ? የቢሮው አድራሻ ? ህጋዊነቱን የሚያሳይ ማስረጃ ? መጠየቅ አለብን።

- " ስራ ለመቀጠር ብር ክፈሉ " የሚሉ ዘራፊዎችን ለምን ? ብሎ ማፋጠጥ ፤ እንዲሁም ስልካቸውን እና አድራሻቸውን መመዝገብ ይገባል።

- አንድ ስራ በቀን 100 ሺህ ፣ 50 ሺህ ብር ይከፈልበታል ሲባል እንዴት ? በምን መልኩ ? ምን ተሰርቶ ? በየትኛው ህጋዊ መንገድ ብሎ መጠየቅ እና መጠራጠር ይገባል።

በ " ፌስቡክ " ወይም በ " ቴሌግራም " ላይ የማረጋገጫ ምልክት ያላቸው ሰዎች ሁሉ እውነተኛ ናቸው ብላችሁ እንዳታምኑ፤ እነዚህ ምልክቱን ገዝተው መጠቀም ይችላሉና።

ከምን በላይ በተለይ " ፌስቡክ " በክፍያ የሚያስተላልፋቸውን መልዕክቶች ትክክለኝነትን የሚያረጋግጥበትን መንግድ መዘርጋት ካልቻለ ትልቅ ቀውስ መፍጠሩን ይቀጥላል።

ማንኛውም ሰው ተነስቶ ለፌስቡክ የመክፈያ መንገድ ካበጀ ፤ ዜሮ ተከታይ ቢኖረም ፤ ህገወጥ ዝርፊያ ላይ የተሰማራ ቢሆንም እስከከፈለ ድረስ ማስረጃ የሌለው መልዕክት ሊያሰራጭ ይችላል።

በተለይም በርካታ ወጣቶች ስራ ፈላጊ በመሆናቸው ስራ ያላቸው ዜጎችም ከሚያገኙት ገቢ የተሻለ ለማግኘት ሲሉ እነዚህን አካላት ያነጋግራሉ። የሚጠየቁትን ገንዘብም ክፈሉ ሲባሉ ሊከፍሉ ይችላሉ።

አንደንዶች ደግሞ በፌስቡክ የክፍያ መልዕክት የሌላቸው እና የማይሸጡትን ዕቃ በማስተዋወቅ ሰዎችን ገንዘብ ካስላኩ በኃላ የውሃ ሽታ ሆነው ይቀራሉ።

" ፌስቡክ " አሰራሩን ማስተካከል ካልቻለና ገንዘብ እየሰበሰበ ብቻ በትንሽ ዶላር ብዙሃን ጋር ያልተረጋገጡ መልዕክቶችን የሚያሰራጭ ከሆነ በተዘዋዋሪ ቁጥጥር ባለማድረጉ በተጠቃሚዎች ላይ ለሚደርሰው ድርጊት ኃላፊነት ሊውስድ ይገባል።

ከምንም በላይ ግን ተጠቃሚዎች እንዲሁም ውድ ቤተሰቦቻችን እራሳችሁን ከአጭበርባሪዎች ጠብቁ።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
#ለጥንቃቄ

ቴሌግራም ላይ ከተለያዩ ሰዎች አጭር ጹሑፍና ሊንክ እየተላከሎት ነው ?

ቴሌግራም ላይ ከተለያዩ ሰዎች ጹሑፍና ሊንክ ያለው መልዕክቶች እየተላኩ ነው። ብዙዎች ይህ ጉዳይ በተደጋጋሚ እየደረሳቸው እንደሆነና የጥንቃቄ መልዕክቱን እንድናስተላልፍ ጠይቀውናል።

በመልዕክት የሚላከው ሊንክ ምንድን ነው?

በመልዕክቱ አብሮ የሚደርሶት ሊንክ የቴሌግራም አካውንቶን ለመጥለፍ የተዘጋጀ ቴሌግራምን የሚመስል ድረ-ገጽ ነው። ሊንኩን ሲከፍቱት ስልክ ቁጥር አስገብተው ወደ ቴሌግራም እንዲገቡ ይጠይቆቃል።

ቁጥሮን አስገብተው የሚመጣው ሌላኛው ገጽ በቴሌግራሞት የተላከሎትን አጭር የማረጋገጫ ቁጥር እንዲያስገቡ የሚጠይቅ ነው።

የተላከሎትን የማረጋገጫ ቁጥር ካስገቡ የእርሶን ቴሌግራም በቀጥታ ይህን ወጥመድ ያዘጋጁ ሰዎችም መጠቀም ይጀምራሉ። በዚህም መልዕክቶችን ለሌሎች መላክና እርሶ እንደላኩት አድርገው ማቅረብ ይችላሉ።

ይህ ገጽ ልክ ቴሌግራምን እንዲመስል ተደርጎ የተሰራ ሲሆን የሚያስገቡት መረጃ ግን ወደ ቴሌግራም ሳይሆን ይህንን ወደ ሚቆጣጠሩት ሰዎች የሚላክ ነው። ይህ አይነቱ ማጭበርበር ማጥመድ (Phishing) በመባል ይታወቃል።

ምን ማድረግ እችላለሁ ?

ይህ ችግር ካጋጠሞት ቀጥታ ቴሌግራሞት ላይ Setting ላይ በመግባት #Device የሚለውን በመጫን የእርሶ አካውንት በምን በምን ስልኮች ላይ እየሰራ እንደሚገኝ ማየት ይችላሉ። በዚህም ከእርሶ ቁጥጥር ውጪ ያሉ ስልኮችን በሙሉ ማስወጣትና እርሶ የሚጠቀሙበትን ብቻ ማስቀረት ይችላሉ።

ሁለተኛው መንገድ ይህ ችግር ከተመፈጠሩ በፊት የሚያገለግል ሲሆን ሁለተኛ ዙር የደኅንነት ማረጋገጫ (Two-Step verification ) መጠቀም ድንገት ለእንደዚህ አይነት ችግሮች ብንጋለጥ ተጨማሪ የደኅንነት ማረጋገጫ ይሆነናል። (ስለዚህ ዝርዝር ሊንኩን ተጭነው ያንብቡ)

Via 👋  @TikvahethMagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#ለጥንቃቄ

በአዲስ አበባ በከተማ " ጉንፋን መሰል " ህመም መከሰቱና ነዋሪዎች ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባቸው የጤና ባለሙያዎች እየመከሩ ናቸው።

በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ሃኪም ዶ/ር ስንሻው አባይ ፤ በአዲስ አበባ በከተማ ለተከሰተው " ጉንፋን መሰል ህመም " ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል ብለዋል።

ጉንፋን መሰል ህመሙ፦
- ከአፍንጫ ብዙ ፈሳሽ መውጣት፣
- ሳል፣
- ራስ ምታት፣
- ጉሮሮን የማቃጠል ስሜት፣
- ድካም፣ የምግብ ፍላጎት መቀነስ የመሳሰሉት እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡

ዶክተሩ ፤ ሰሞኑን የተከሰተው ጉንፋን መሰል ህመም የላይኛውን የመተንፈሻ አካል ክፍል የሚያጠቃ ነው ብለዋል፡፡

ህመሙን ለመከላከል እና ለማስታገስ ፦
* ፈሳሽ መውሰድ፣
* ከቅዝቃዜ ራስን ማራቅ (ሙቀቱን የተመጣጠነ ማድረግ)፣
* መኖሪያ ቤትን አየር እንዲያገኝ ማድረግ፣
* በቂ የሆነ እረፍት መውሰድ እና የመሳሰሉትን ተግባራዊ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን መክረዋል።

በሌላ በኩል ፤ በቤት ውስጥ የእፅዋት ዝርያዎችን በፍም (እሳት) ላይ በማጨስ ጭሱን መታጠን ሳንባ እንዲያብጥ ወይም እንዲቆጣ በማድረግ ለጉዳት እንደሚዳርግ ተናግረዋል፡፡

ማህበረሰቡ ፦
° በህዝብ ማመላለሻ ትራንስፖርት ውስጥ መስኮቶችን በመክፈት፣
° በንግድ ቤቶች፣ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም ሰው በተሰበሰበበት ቦታዎች የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል በማድረግ፣
° የእጅን ንፅህና በአግባቡ በመጠበቅ እንዲሁም አስም ያለባቸው ምልክቶቹ እንደታዩባቸው ወደ ህክምና ተቋማት ሄደው መታየት እንዳለባቸው መክረዋል።

የጤና ሚኒስቴር ከህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በጋራ በመሆን በ2 ሺህ ያህል ናሙናዎች ላይ ምርመራ አድርጎ አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች የጉንፋንና ኢንፍሉዌንዛ በሽታ መከሰቱን ከሁለት ሳምንት በፊት ይፋ አድርጓል።

የዝናብ ወራት ማለፉን ተከትሎ በጥቅምትና ህዳር ወቅት ላይ አብዛኛውን ጊዜ የጉንፋንና ኢንፍሉዌንዛ በሽታ ይከሰታል፡፡

በጤና ሚኒስቴር የኮቪድ-19 ምላሽ ግብረ-ሃይል ዋና አስተባባሪ ዶክተር መብራቱ ማሴቦ ፤ ከጥቅምት ወር መጀመሪያ ጀምሮ በአንዳንድ የሀገሪቱ አካባቢዎች የጉንፋንና ኢንፍሉዌንዛ በሽታ መከሰቱን ተናግረዋል።

" እጅን በመታጠብ፣ አፍና አፍንጫን በመሸፈን በሽታውን በቀላሉ መከላከል ይቻላል " ያሉ ሲሆን በበሽታው የተያዙ ሰዎች በቂ እረፍት በመውሰድ፣ ፈሳሽና ትኩስ ነገሮች በመጠቀምና ተገቢውን ህክምና በማግኘት ስርጭቱ እንዳይስፋፋ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የጤና ባለሙያዎች የሚሰጧቸውን ምክረ-ሀሳቦች በመተግበር፣ በርና መስኮቶችን በመክፈት፤ በቂ የአየር ዝውውር እንዲኖር በማድረግ መከላከል እንደሚቻልም ነው የገለፁት፡፡

መረጃው የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ እና ኢዜአ ነው።

@tikvahethiopia
#ለጥንቃቄ

የተከሰተው ጉንፋን መሰል በሽታ በከፍተኛ ሁኔታ የመሰራጨት ባህሪ ስላለው በመከላከያ መንገዶች ላይ ትኩረት ማድረግ ያስፈልጋል ሲል የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ አሳስቧል።

ቢሮው ምን አለ ?

- በከተማው በተለይ ከጥቅምት ወር መጀመሪያ ጀምሮ በብዙ ሰዎች ላይ ጉንፋን መሰል በሽታ ተከስቷል።

- ይህ ወቅታዊና በየዓመቱ ከቅዝቃዜ ጋር ተያይዞ የሚከሰት ሲሆን፤ በወረርሽኝ መልክ የሚገለጽ አይደለም።

- የተከሰተውን የቫይረስ አይነት ለመለየት ከትምህርት ቤቶች፣ ጤና ተቋማት እንዲሁም ከፍተኛ መተላለፊያ በሆኑ ቦታዎች ላይ ከሚገኙ ከ178 ሰዎች ናሙና ተወስዶ ምርመራ ተደርጓል። በዚህም 17 በመቶ በላይ የኢንፍሉዌንዛ ቫይረስ እና 3 በመቶ የሚሆነው ከኮቪድ-19 ቫይረስ ጋር የተገናኘ መሆኑ ተረጋግጧል።

- ይህ ህመም በተለይም እድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች የሆኑ ህጻናት ላይ የሚከሰት ሲሆን፤ ከመቶ ሰዎች መካከል ሃያ የሚሆኑት ላይ ይስተዋላል።

ምልክቶቹ ፦

° ከፍተኛ ራስ ምታት፣
° ሳል፣
° ከአፍንጫ ብዙ ፈሳሽ መውጣት፣
° ጉሮሮን የማቃጠል ስሜት፣
° ጡንቻ አካባቢ ህመም፣
° የድካም እና የምግብ ፍላጎት መቀነስ የመሳሰሉት ናቸው።

- ምልክቶቹ ሲታዩ ወደ ህክምና ተቋም በመሄድ እራስን ከከባድ ህመም መከላከል ያስፈልጋል።

- በበሽታው የተያዙ ሰዎች አፋቸውን እና አፍንጫቸውን ሳይሸፍኑ ሲያስሉ ወይም ሲያስነጥሱ እንዲሁም ቫይረሱ ያረፈባቸውን ነገሮች ከነኩ በኋላ አፍን፣ አፍንጫ ወይም ዓይንን መንካት ቫይረሱ እንዲሰራጭ የሚያደርጉ መንገዶች ናቸው።

የመከለከያ መንገዶች ምንድናቸው ?

ትምህርት ቤቶች እንዲሁም ሰው በተሰበሰበበት ቦታዎች የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል ማድረግ፣

በሕዝብ ማመላለሻ ትራንስፖርት ውስጥ መስኮቶችን መክፈት፣

የእጅን ንፅህና በአግባቡ መጠበቅ

በንክኪ ወቅት እጅን በመታጠብ በሽታውን በቀላሉ መከላከል ይቻላል።

* በሽታው በከፍተኛ ሁኔታ የመሰራጨት ባህሪ ስላለው በመከላከያ መንገዶች ላይ ትኩረት ማድረግ ያስፈልጋል።

በበሽታው የተያዙ ሰዎች ማድረግ ያለባቸው ምንድነው ?

በበሽታው የተያዙ ሰዎች ህክምናው ከቤት የሚጀምር ሲሆን ህመሙን ለመከላከል እና ለማስታገስ ፦
በቂ እረፍት መውሰድ፣
ፈሳሽና ትኩስ ነገሮች መጠቀም
በአካባቢው በቂ የአየር ዝውውር እንዲኖር ማድረግ ከዚህ በተጨማሪ ተገቢውን ህክምና በማግኘት ስርጭቱ እንዳይስፋፋ ማድረግ ይገባል።

#ማሳሰቢያ ፦ በሽታው ከአንድ ሳምንት በላይ የሚቆይ ከሆነ በአቅራቢያው ወደሚገኝ የህክናምና ተቋም በመሄድ አስፈላጊውን አገልግሎትና የጤና ባለሙያዎች ምክረ ሃሳቦች ማግኘት ይገባል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃው ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ነው ያገኘው።

@tikvahethiopia
#ለጥንቃቄ

" በምዕራብ ኦሞ ዞን ባለፉት ሦስት ወራት 9,000 #ህፃናት በኩፍኝ ተጠቅተዋል። 11 ሞት ተመዝግቧል " - የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ፦
° 65 በመቶ የሚሆን #ገዳይ የወባ ዝርያ እንዳለ፣
° በአንድ ዓመት ውስጥ 101 ሰዎች በወባ እንደሞቱ፣
° ማኅበረሰቡ ወደ ሕክምና ተቋማት እንዲሄድና አጎበር የመጠቀም ልምዱን እንዲያዳብር የክልሉ ጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ ዳይሬክተር አቶ ተስፋፅዮን ተረፈ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ኩፍኝ በምን ደረጃ ላይ ይገኛል ?

* ምዕራብ ኦሞ ዞን ባለፉት 3 ወራት 9,000 #ህፃናት በኩፍኝ ተጠቅተዋል። 11 ሞት ተመዝግቧል። በክልሉ በአንድ ዓመት ውስጥ 12,700 የኩፍኝ ኬዞች ተገኝተዋል። 

* ከሌሎች ቦታዎች በተለዬ መልኩ በምዕራብ ኦሞ ዞን አሁንም ከፍተኛ ሥራ የሚጠይቅ የኩፍኝ ወረርሽኝ ስርጭት አለ። በመቀጠልም በቤንቺ ሸኮና ከፋ ዞኖች በተወሰኑ ወረዳዎች ይስተዋላል።

* አርሶ አደሮች በሚኖሩባቸው ( #በተለይም ምዕራብ ኦሞ)፣ የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች የክትባት አሰጣጡን አፌክት ያደርገዋል።

* #አርሶ_አደሮች ባሉባቸው አካባቢዎች ላይ ችግሩ እንዲቀረፍ ለማድረግ የጤና ባለሙያዎች በአካባቢው ተንቀሳቀሰው ሕክምና እንዲሰጡ እየተደረገ ነው።
 
* የኩፍኝ ኬዞች ያሉባቸው አራት ዞኖች ናቸው። ቤንቺ ሸኮ ዞን ላይ ወደ 3,000፣ ከፋ ዞን ከ1,000 በላይ ኬዞች ነበሩ ፤ አሁን መቆጣጠር ተችሏል።

* ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ የኩፍኝ ክትባት ዘመቻ ለማድረግ ጤና ሚኒስቴር ፈቅዷል። ከአምስት ዓመት በታች ለሚሆኑ ሕፃናት ክትባት ይደረጋል።
 
ወባ በምን ደረጃ ይገኛል?

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃልፊ አቶ ኢብራሄም ተማሙ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፦

- ለሁለት ዓመታት #የወባ_ወረርሽኝ በክልሉ ተከስቶ ቆይቷል። የኩፍኝ ወረርሽኝም በተለይ በምዕራብ ኦሞ ዞን ልዩ ትኩረት ይሻል። ከእስከዛሬው ጋር ሲነጻጸር ግን ኬዞቹ እየቀነሱ ነው። ግን አሁንም ሥራ ይጠይቃል።

- የወባ ወረርሽኝ ቆዬ ስንል በርካታ ሥራዎችን ሰርተናል ከወባ ጋር ተያይዞ ወደ 1.2 ሚሊዮን የአጎበር ስርጭት ተካሂዷል። ከ6,000 ኪ.ግ በላይ እርጭት ተካሂዷል።

- አሁንም ውሃ ያቆሩ ቦታዎች ላይ እርጭት እያካሄድን ነው ፤ በጣም በተለየ መንገድ ምዕራብ ኦሞ ላይ ከ6 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ያለው ግብዓት አሰራጭተን የመከላከሉን ሥራ እየሰራን ነው።

አቶ ተስፋፅዮ በበኩላቸው ስለ ወባ ምን አሉ ?

* የተወሰኑ ወረዳዎችን ላያካትት ይችል ይሆናል እንጂ ሁሉም  ዞኖች በጣም ከፍተኛ የወባ ጫና ያለባቸው ናቸው።

* በአመት ውስጥ #በ6_ዞኖች በወባ ወደ 101 ሞት ተመዝግቧል። አሁን ግን ማኅበረሰቡ  በአቅራቢያቸው ህክምና እያገኙ ስለሆነ የህመም (የኬዝ)፣ የሞት መጠኑ በዛው ልክ ቀንሷል።

* ላለፉት ሁለት ዓመት ለዚህ መንስኤ የሆኑ ጥናቶች ለማድረግ ሞክረናል፣ የምላሽ ሥራው ተሰርቷል።

* እስካሁን ባለው በአጠቃላይ ወደ 400,054 ሰዎች በአንድ ዓመት የወባ አይነቶች ተለይተው ህክምና ያገኙ ናቸው።

* በተሰሩ ሥራዎች በተለይ ከአራት ወራት በፊት እስከ 15,000 ሰዎች በወባ ይጠቁ ነበር። አሁን ባለንበት በሳምንት በወባ የመጠቃቱ ሁኔታ ከ7,000 እስከ 6,000 ሰዎች ዝቅ ለማድረግ ተችላል።

* በመከላከል ላይ ያለ ክፍተት ነው የወባ ቁጥር ከፍ ብሎ እዲታይ እያደረገ ያለው። ምዕራብ ኦሞ ፣ ካፋ ዞን በሚገኙ አካባቢዎች ላይ አርብቶ አደሮች ናቸው በተለይ ተጋላጭ የሆኑት።

* ከጤና ኬላ ጀምሮ እስከ ከፍተኛ ሆስፒታል ድረስ የወባ ህክምና አለ።

* ሞት እያስከተለ ያለው ቆይተው ስለሚመጡ ነው። ቆይተው ሲመጡ ደግሞ በክልላችን #ከ65 ፐርሰት በላይ ፋልሲፋረም የሚባል በባህሪው #ገዳይ የሆነ ዝርያ ነው ያለው።

* በእኛ ክልል ላይ የሚበዛው ያ " ፋልሲፋረም " ነው። ሰዎች ወዳውኑ ምልክቱን እንዳዩ የመወሳሰብ ደረጃ ላይ ሳይደርስ ወደ ጤና ተቋማት ሂደው መታከም አለባቸው። ችግሩ ሲወሳሰብ ደም ሊፈልግ ይችላል፣ #ነፍሰ ጡሮችን በተለይ ወዲያው የመግደል ዕድሉ ከፍተኛ ነው።

ለ2ቱም ወረርሽኞች ለሞት አደጋው መከሰት ምክንያቱ ፦

° የሕሙማን ወደ ሕክምና #ዘግይቶ መምጣት፣

° #የጤና_ኤክስቴንሽኖች ወረርሽኝ አካባቢዎች ላይ አክቲቭ አለመሆንና በወቅቱ ለይቶ አለመላክ ነበር።

* በዘላቂነት ችግሮቹን ለማስወገድ ክልሉ የንቅናቄ መድረክ እንያዘጋጀ ነው። አሁንም ዝናብ ወጣ እየገባ እያለ ስለሆነ ለወባ መራባት እጅግ በጣም ምቹ አጋጣሚ ስለሚፈጥር ማህበረሰቡ ጥንቃቄ ሊያደግ ይገባል።

ጥንቅሩ በአዲስ አበባ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው።

@tikvahethiopia
#ለጥንቃቄ

" ተጠርጣሪው ከ50 ሺህ እስከ 600 ሺህ ብር ከእያንዳንዳቸው መቀበሉ ተረጋግጧል " - ፖሊስ

" ያለምንም ቅድመ ክፍያ ቪዛ እናስጨርሳለን ! " በሚል #ቲክቶክ በተሰኘው የማህበራዊ መገናኛ ዘዴ ሐሰተኛ መረጃ በማሰራጨት ሲያጭበረብር የነበረ ግለሰብ መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።

" ያለምንም ቅድመ ክፍያ ወደ ተለያዩ ሀገራት ለሚጓዙ ሰዎች ቪዛ እናስጨርሳለን ! " እያለ በቲክቶክ ሲያጭበረብር የነበረው ይኸው ግለሰብ ከ25 በላይ የሚሆኑ ግለሰቦችን  በማጭበርበር ከ50 ሺህ እስከ 600 ሺህ ብር ከእያንዳንዳቸው መቀበሉ ተረጋግጧል።

በቲክቶክ ሀሰተኛ የግለሰቡ ማስታወቂያ የተጭበረበሩት አብዛኞች ወደ #ካናዳ ለመጓዝ ፍላጎት አሳይተው ከተጠርጣሪው ጋር የተገናኙ ናቸው።

" ያለምንም ቅድመ ክፍያ የቪዛ ፕሮሰስ እጨርሳለሁ " ቢልም ተበዳዮችን የተለያየ ቦታ እየቀያየረ እያገኛቸው  ቪዛ እንዳለቀላቸው እየነገረ እና ሌሎች ምክንያቶችን እየሰጠ ከእያንዳንዳቸው ከ50 ሺህ እስከ 600 ሺህ ብር የሚደርስ ገንዘብ ተቀብሏል።

ተጠርጣሪው የማታለል ወንጀል እየፈፀመ መሆኑ የታወቀው " ቪዛ አልቆልሃል " ተብሎ 600 ሺህ ብር የከፈለ አንድ ግለሰብ ወደ ካናዳ ሀገር ለመሄድ አየር መንገድ በተገኘበት ወቅት #ቪዛው_ሃሰተኛ መሆኑ ከተነገረው በኋላ ለፖሊስ በሰጠው ጥቆማ ነው፡፡

አሁን ላይ ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ውሎ ክስ ተመስርቶበታል።

ተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ በህግ አግባብ ቤቱ ሲበረበር ሀሰተኛ ሰነዶች እና ሰነዶቹን ለማዘጋጀት ሲጠቀምባቸው የነበሩ ልዩ ልዩ ቁሳቁሶች መገኘታቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ መረጃ ያሳያል።

#AddisAbabaPoliceCommission

@tikvahethiopia
Audio
#ለጥንቃቄ⚠️

እንዲህ ካሉ አጭበርባሪዎች ተጠንቀቁ።

ከላይ የምትሰሙት የድምፅ ቅጂ ከአንድ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል የተላከ ነው።

አጭበርባሪው ደዋይ ግለሰብ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ #ዋናው_ቢሮ እንደደወለ በማስመሰል በኦንላይን ዘረፋ ለመፈፀም ሞክሯል።

የደወለው #የባንክ_ሰራተኛ ጋር መሆኑን አላወቀም ነበር።

ሰራተኛው ግለሰቡ የሚለፈልፈውን ሁሉ እስከ መጨረሻ ድረስ አዳመጠው።

በኃላም የአንድ የባንኩን ቅርንጫፍ ዋና ስራ አስኪያጅ ስምን ይጠይቀዋል።

በዚህ ግዜ ከዋናው መ/ቤት ነኝ ያለው አጭበርባሪ ምን ይዋጠው ? መቀባጠር ይጀምራል።

በመጨረሻ ውርደቱን ተከናንቦ ስልኩን ዘግቷል።

እንዲህ ያሉ የማጭበርበር ስልቶች አንድ ሰሞን እንደጉድ ተበራክተው ነበር። አሁን ደግሞ ሰሞነኛውን የንግድ ባንክን ሁኔታ ተከትሎ እንደ አዲስ ተስፋፍተዋል።

ውድ ቤተሰቦቻችን ፦
* የማታውቋቸው የግል ስልኮችን ባለማንሳት ፣
* #የሚስጥር_ቁጥሮችን ባለመስጠት እራሳችሁን ከአጭበርባሪዎች ጠብቁ። የሚመለከታቸው አካላትም ይህን ነገር እንደ ቀላል ከማየት የማጭበርበር ስራ ላይ የተሰማሩ ሰዎች #በደወሉበት_ስልክ ክትትል በማድረግ ወደ ህግ ማቀረብ አለባቸው።

(የድምፅ ቅጂውን ለላከው የቤተሰባችን አባል ምስጋና እናቀርባለን)

@tikvahethiopia
Audio
#ለጥንቃቄ⚠️

" ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋናው መስሪያ ቤት ነው " እየተባለ ወደ ተለያዩ የባንኩ ደንበኞች ስልክ እየተደወለ የግል መረጃ መውሰድና የኦንላይን ዝርፊያ እየተሞከረ ይገኛል።

ቀደም ብሎ አንድ #አጭበርባሪ ግለሰብ (ጾታ - ወንድ) ሳያውቀው ለባንክ ሰራተኛ ደውሎ ያጋጠመውን ክስተት አጋርተናል።

የዜጎችን ሀቅና ገንዘብ አታለው ለመዝረፍ ስልክ ከሚደውሉት መካከል #ሴቶችም ስለሚገኙበት ጥንቃቄ አድርጉ።

ከላይ ባለው የድምፅ ቅጂ የምትሰሟት አጭበርባሪ ግለሰብ (ጾታ-ሴት) ከንግድ ባንክ ዋና መ/ቤት እንደደወለች በማስመሰል ፦ ደንበኞች የሞባይል ባንኪንግ ሲጠቀሙ ኔትዎርኩ please try again ፣ connection problem ፣ error ፣ service not available " የሚል ችግር እየገጠማቸው እንደሆነ ትገልጸለች።

በዚህ ምክንያት ባንኩ ከብዙ ደንበኞቹ ቅሬታ በመምጣቱ ፤ " ችግሩን በዋናው የንግድ ባንክ መ/ ቤት #ሲስተም ላይ ለማስተከል ነው " በማለት የደንበኛውን የግል መረጃዎች በመቀበልና በማታለል ዝርፊያ ለመፈፀም ሞክራለች።

አሁን ላይ እንዲህ ያሉት አጭበርባሪዎች ተበራክተዋል ተጠንቀቁ።

ለማንኛውም #የማታውቁት ስልክ የባንክ መረጃችሁን እንዳትሰጡ።

@tikvahethiopia