TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ለቀናት የስራ ማቆም አድማ ላይ የቆዩት የዓየር ትራፊክ ተቆጣጣሪ ሰራተኞች ዛሬ ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ መግታቸውን ፋና ዘገበ።

የኢትዮጵያ ሲቪል አቭዬሽን ባለስልጣን ዳይሬክተር ጀነራል ኮሎኔል #ወሰንየለህ_ሁነኛው
ሰራተኞቹ ወደ ስራ መመለሳቸውን አረጋግጠዋል።

ከመንግስት በተሰጠ አቅጣጫም በደመዎዛቸው ላይ #ማስተካከያ ለማድረግ ጥናት ይካሄዳል ብለዋል።

የሌሎች ሰራተኞችን ፊርማ #አስመስሎ በመፈረምና ሌሎች ስራ እንዲያቆሙ በማነሳሳት ወንጀል የተጠረጠሩ ዘጠኝ የሲቪል አቭዬሽን እና የዓየር ትራፊክ ሰራተኞች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ይታወቃል።

ተጠርጣሪዎቹም ትናንት በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡ ሲሆን፥ ፍርድ ቤቱም ለመርማሪ
ፖሊስ የስምንት ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ፈቅዷል።

©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia