TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አንድ ወር የሚቆይ የፊርማ ማሰባሰብ ንቅናቄ!

በሚሊዮን ለሚቆጠሩ መስማት ለተሳናቸው ዜጎች፥ የምልክት ቋንቋ መግባቢያቸው ነው። የምልክት ቋንቋን ይፋዊ የሥራ ቋንቋ ማድረግ ደግሞ ለበርካታ የሰብዓዊ መብት ጥያቄዎች ምላሽና ለዕኩል እድል ተጠቃሚነት በር ከፋች ነው።

በዓለም ላይ 75 ሀገራት የምልክት ቋንቋን እንደ ብሔራዊ ቋንቋቸው መቀበልን ጨምሮ በሰነድ የተደገፈ ሕጋዊ እውቅና ሰጥተዋል፡፡ በአፍሪካ ደግሞ ኬንያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ኡጋንዳ፣ ዙምባቡዌ ብሔራዊ ቋንቋቸው አድርገው ተቀብለውታል፡፡

በኢትዮጵያም የምልክት ቋንቋ የሥራ ቋንቋ እንዲሆን እንጠይቅ!

በሀገራችን ይህ ተፈጻሚ እንዲሆን #እየተጠየቀ ነው። እርሶም ድምጽ በመስጠት፤ የተዘጋጀውን የፊርማ ማሰባሰብ ንቅናቄ በመቀላቀልና ለሌሎች በማጋራት #በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ዜጎች ድምጽ ይሁኑ።

ለመፈረም፦ https://chng.it/zJwncqjqC5

በጉዳዩ ላይ ሞያዊ ሂስና አስተያየት ለመስጠት Rootsandwingscampaign@gmail.com

#HandsSpeakEyesListen
#እጆች_ይናገራሉ_አይኖች_ያዳምጣሉ