TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ክስ በመመስረት ሂደት ላይ መሆኗን አሳወቀች። ቤተክርስቲያኗ ይህን ያሳወቀችው ዛሬ ከህግ ባለሙያዎች ጋር በመሆን በሰጠችው መግለጫ ነው። ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ክስ ለመመስረት ጥያቄ የቀርበ ሲሆን ክስ የመመስረት ሂደት ጊዜ ስለሚፈልግ ጊዜያዊ እግድ እንዲሰጥ ጥያቄ መቅርቡ ታውቋል። ክሱ / እግዱ የቀረበው በልደታ ምድብ ሁለተኛ መሰረታዊ…
#Update

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፤ የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ያሬድ ዛሬ ምሽት 3:45 አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ከሚገኘው መንበረ ጵጵስናቸው ተወስደው ታስረው እንደነበር ቤተክርስቲያኗ አሳውቃለች።

ብፁዕነታቸው በዛሬው ዕለት ማምሻውን ነበር ከአዲስ አበባ ወደ ሀገረ ስብከታቸው መድረሳቸው የተጠቆመው።

ዘግየት ብለው የቤተክርስቲያኗ መገናኛ ብዙሃን ባወጡት መረጃ ብፁዕ አቡነ ያሬድ በአሰላ #መቆየት_አይችሉም ተብለው በዚህ ሰዓት ወደ አዲስ አበባ እንዲመለሱ መደረጉን አሳውቀዋል።

በሌላ በኩል፤ " በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ሻሸመኔ ከተማ በሕገ ወጥ የተሾመው ቡድን መንበረ ጵጵስናና ቤተ ክርስቲያን ሰብረን እንገባለን በማለት በምእመናን ላይ ስጋት ተፈጥሯል ። " ሲሉ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የሲዳማ፣ ጌዲዮ፣ አማሮ ፣ ቡርጂና ምዕራብ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተናግረዋል።

ከሰሞኑን የሀገረ ስብከቱ አገልጋዮች ያለምክንያት እየታሰሩ ነው ያሉት ብፁዕነታቸው ይህንንም ለሚመለከተው የዞን ፀጥታ አካል ለማሳወቅና ጥበቃ እንዲያደርጉ ብንደውልም ፣ መልእክት ብንጽፍም ሊመልሱልን አልቻሉም ብለዋል።

በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት ለኦሮምያ ክልል የሚመለከታቸው አካላት በተለይም ጥበቃና ከለላን በተመለከተ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አስቀድሞ ደብዳቤ ቢጻፍም ምንም አይነት የቃልም ሆነ የተግባር መልስ እንዳልተሰጣቸው ተናግረዋል።

ብፁዕነታቸው ፤ " መንግሥት በሕገ ወጡ ቡድን የሚደረገውን ድርጊት ማስቆም ካልቻለ ምእመናን ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ለመጠበቅ በሚያደርጉት ጥረት ለሚፈጠረው ችግር ኃላፊነቱን ይወስዳል" ብለዋል። ምእመናን ቤተ ክርስቲያናቸውን እንዲጠብቁም መልእክት አስተላልፈዋል።

@tikvahethiopia