TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
(የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን) በ " ወሊሶ በዓለ ወልድ ቤተ ክርስቲያን " ከፍተኛ የዶግማ እና ቀኖና ጥሰት በተፈፀመበት ሁኔታ ቤተክርስቲያን ሕገወጥ ነው ያለችው የ " ጳጳሳት " ሹመት መከናወኑን ከተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ይህንን ክስተት ተከትሎ  ፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ አስቸኳይ መግለጫ ሰጥቷል። መግለጫውን…
ብፁዕ አቡነ አብርሃም ምን አሉ ?

ብፁዕ አቡነ አብርሃም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፦

" በፈተና የሚያጸናው ሁል ጊዜ ፈተናዎችን እያሳለፈ ለዘመናት ሲጠብቃት የነበረ እግዚአብሔር ዛሬም ጥበቃውና መግቦቱ እንደማይለያት ሙሉ እምነት አለን ፣ በደረሰው ክስተትም እጅግ አዝነናል ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ታዝናለች።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከ3ሺ ዘመን በላይ የራሷን አንድነት ከማስጠበቅ አልፋ የሀገርን አንድነት ስታስጠብቅ ለሰው ልጆች አንድነት ትልቁን ድርሻ በመውሰድ ስትሠራ የኖረች አሁንም ያለች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ነች።

ይህንን አንድነቷን የሚንድ ሕጋዊ ሰውነቷን የሚጥስ አላስፈላጊ ክስተት ተፈፅሟል።

በዚህም ቅዱስ ፓትርያርኩ በአስተላለፉት ጥሪ መሠረት ከሀገር ውስጥ ከሀገር ውጭ የምትገኙ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ከነገው ዕለት ጀምሮ የቅዱስነታቸውን ጥሪ በመቀበል እንድትገኙ።

የተፈጠረው ችግር በዝርዝርና በጥናት ቅዱስ ሲኖዶስ አይቶ የመጨረሻውን ውሳኔ እስከሚሰጥበት ጊዜ ድረስ ምእመናንና አገልጋዮች ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ሁላችሁም በየአላችሁበት ቤተ ክርስቲያንን ጠብቁ።

ተመሳስለውና የሌለ ሐሳብ እያቀረቡ ሕዝብን ከሚለያዩ ሠዎች እንድትጠበቁና እንድትጠብቁ በጽናት፣ በትእግስትና በፍቅር ሕጋዊ በሆነ ነገር ሁሉ ቤተ ክርስቲያንን እንድትጠብቋት በአንድነቷ የተረከብናትን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በአንድነቷ ለነገው ትውልድ ለማስረከብ የእያንዳንዳችንን ድርሻ እንድንወጣ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። "

(ከአ/አ ሀገረስብከት)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ብፁዕ አቡነ አብርሃም ምን አሉ ? ብፁዕ አቡነ አብርሃም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፦ " በፈተና የሚያጸናው ሁል ጊዜ ፈተናዎችን እያሳለፈ ለዘመናት ሲጠብቃት የነበረ እግዚአብሔር ዛሬም ጥበቃውና መግቦቱ እንደማይለያት ሙሉ እምነት አለን ፣ በደረሰው ክስተትም እጅግ አዝነናል ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ታዝናለች። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ…
" ክሰቱት በሀገር ላይ ጭምር የሚያስከትለውን ጉዳት በመመልከት መንግስት ሕጋዊ ኃላፊነቱን ይወጣ " - የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፤ ከፍተኛ የዶግማና ቀኖና ጥሰት በመፈፀም ተፈፅሟል ካለችው ህገወጥ የ " ጳጳሳት " ሹመት ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ መንግስት የቤተክርስቲያኗን ህጋዊ ሰውነት በማስጠበቅ ኃላፊነቱን እንዲወጣ አስቸኳይ ጥሪ አቅርባለች።

ብፁዕ አቡነ አብርሃም ፤ " ሕጋዊ ሰውነቷ የተረጋገጠ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በሕጋዊ ሰውነቷ የመጠበቅ የማስጠበቅ ኃላፊነቱ የመንግሥት ነው " ብለዋል።

የተፈጸመው ድርጊት " ግፍ ነው " ሲሉ የገለፁት ብፁዕነታቸው " መንግሥት ይሄንን ተመልክቶ የቤተ ክርስቲያኗን ሉዓላዊነት #በመጠበቅ እና #በማስጠበቅ የራሱን ድርሻ እንዲወጣ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም ጥሪ እናቀርባለን " ብለዋል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ክስተቱ #በሀገር ላይ ጭምር ጉዳት የሚያስከትል መሆኑን በመጠቆም መንግስት በጉዳዩ ላይ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርባለች።

@tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA
ባንካችን አቢሲንያ ከሳፋሪኮም ጋር በአጋርነት መሥራት ጀመረ፡፡

የባንካችን ደንበኞች የሳፋሪኮም አየር ሰዓት በአቢሲንያ ሞባይል ባንኪንግ ካሉበት ሆነው ወይም አቅራቢያዎ በሚገኙት የባንካችን ቅርንጫፎች መሙላት ይችላሉ፡፡

#BankofAbyssinia #Abyssinia #Banking #BankingService #MobileBanking #Digital #DigitalEthiopia #DigitalPayment #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
STEMpower እና Visa ከTikvah-Ethiopia ጋር በመሆን የሚያዘጋጁት የሥራ ፈጠራ እና መሰረታዊ የፋይናንስ ክህሎት ስልጠና በሰባተኛ ዙር ተመልሶ መቷል።

ባለፉት ዙሮች ወደ 1500 የሚጠጉ ሰልጣኞች መሳተፍ ችለዋል። በዚህ 7ተኛ ዙር ደግሞ ተጨማሪ 300 ሰልጣኞችን ለማሳተፍ ዝግጅት ተደርጓል። እርስዎም ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ተመዝግበው የስልጠና እድሉን መጠቀም ይችላሉ።

ስልጠናው የሚያካትተው፦

* የ6 ቀን መሰረታዊ የገንዘብ አያያዝ ትምህርት እና የስራ ፈጠራ ክህሎት ስልጠና

* በተጨማሪ የ3 ወር የንግድ ማማከር እና ድጋፍ

* 9 ወር የማማከር ድጋፎች፣ የኔትዎርኪንግ እና የተለያዩ ክትትሎች በተጨማሪም ቢዝነ  ፕሮቶታይፕ (prototype) የሚያስፈልገው ከሆነ ፕሮቶታይፕ መስሪያ ጥሬ ዕቃዎችን ጨምሮ ነጻ የማምረቻ ላብራቶሪ አገልግሎት ለመስጠት ዝግጅታችንን በመጨረስ ላይ እንገኛለን።

በስልጠናው የሚሳተፉ፦

- የሥራ ፈጠራ ክህሎቱን ማዳበር እና ከላይ የተጠቀሱትን አገልግሎቶች መጠቀም የሚፈልግ፤

- በግብርና፣ ጤና፣ አገልግሎት፣ ምህንድስና እና ቴክኖሎጂ እና ሌሎችም ዘርፎች የሥራ ፈጠራ ሃሳብ ላላቸው ቅድሚያ እንሰጣለን፤

- ሴት የሥራ ፈጣሪዎች እንዲመዘገቡ እናበረታታለን።

በሥልጠናው መሳተፍ የምትፈልጉ እና የፈጠራ ሀሳብ ያላችሁ እስከ  ሰኞ ጥር 29፣ 2015 ዓም ተመዝግባችሁ ስልጠናውን እና ሌሎች አገልግሎቶቹን በነጻ መውሰድ ትችላላችሁ።

መመዝገቢያ ሊንክ፡ https://forms.office.com/r/6jrgpFiwtt

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ቅዱስ ሲኖዶስ ህገወጥ ነው ያለውና ቤተክርስቲያንን ያሳዘነው ፤ ምዕመኑንም ያስደናገጠው የ " ጳጳሳት " ሹሙት ምንድነበር ?

ትላንት የኢትዮጵያን ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከፍተኛ የሆነ የዶግማና ቀኖና ጥሰት ተፈፅሞ ጳጳሳትን የመሾም ተግባር መከናወኑን መግለጿ ይታወሳል።

ይኸው ሲመተ ጳጳሳት ፤ #ከቅዱስ_ሲኖዶስ እውቅና ውጭ #በሕገወጥ መልኩ የተከናወነ መሆኑን ነው ቤተክርስቲያን ያሳወቀችው።

ድርጊቱ በርካታ ምእመናንንም ያስደነገጠ ነበር።

ቤተክርስቲያኗ ከፍተኛ የሆነ የዶግማና ቀኖና ጥሰት በተፈፀመበት መልኩ ተከናውኗል ያለችውን ሹመት ማነው ያካሄደው ?

ያንብቡ : https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-01-23-2
#ECSOC

ዛሬ የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምከር ቤት የአገር በቀል እና የውጭ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን በማስተባበር የትግራይ ክልል መዲና መቐለ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።

ከጉዞው ዋነኛ ዓላማዎች ወስጥ ፦

• በትግራይ ያለው የሰብአዊ እና መልሶ ግንበታ እና መልሶ-ማቋቋም ፈተናዎች እና ሁኔታዎች በክልሉ ካሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ለመስማት እና ለመረዳት፤

• የሰብዓዊ ድጋፍ ለተፈናቃዮች በተሻለ ሁኔታ ለማድረስ፤ የምልሶ ግንባታ ስራዎችን ለማስጀመር በሚያስችሉ መንገዶች ላይ፤ በክልሉ ካሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጀቶች ጋር ለመነጋገር እና ለመወያየት መሆኑን ታውቋል።

ፕሮግራሙ የተዘጋጀው ከትግራይ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጥምረት ተቋም ጋር በመተባባር መሆኑን ለመረዳት የቻልን ሲሆን የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ከስፍራው ተጨማሪ መረጃዎችን ይልካሉ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ECSOC ዛሬ የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምከር ቤት የአገር በቀል እና የውጭ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን በማስተባበር የትግራይ ክልል መዲና መቐለ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል። ከጉዞው ዋነኛ ዓላማዎች ወስጥ ፦ • በትግራይ ያለው የሰብአዊ እና መልሶ ግንበታ እና መልሶ-ማቋቋም ፈተናዎች እና ሁኔታዎች በክልሉ ካሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ለመስማት እና ለመረዳት፤ • የሰብዓዊ ድጋፍ ለተፈናቃዮች…
ፎቶ፦ የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት የሀገር በቀልና የውጭ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን በማስተባበር 60 ልዑካንን በመያዝ መቐለ ገብቷል።

የጉዞው ወነኛ አላማዎች በትግራይ ያለው የሰብአዊ እና መልሶ ግንባታ እና መልሶ ማቋቋም ፈተናዎችና ሁኔታዎች በክልሉ ካሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ለመስማትና ለመረዳት ነው።

የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት በስፍራው ስለሚገኙ ሂደቱን እየተከታተሉ ያሳውቁናል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ፦ የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት የሀገር በቀልና የውጭ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን በማስተባበር 60 ልዑካንን በመያዝ መቐለ ገብቷል። የጉዞው ወነኛ አላማዎች በትግራይ ያለው የሰብአዊ እና መልሶ ግንባታ እና መልሶ ማቋቋም ፈተናዎችና ሁኔታዎች በክልሉ ካሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ለመስማትና ለመረዳት ነው። የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት በስፍራው ስለሚገኙ ሂደቱን እየተከታተሉ ያሳውቁናል።…
#አሁን

አሁን በመቐለ ከተማ የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ም/ቤት ልዑክ ከትግራይ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር ምክክር እያደረገ ይገኛል።

የትግራይ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ህብረት / ACSOT የቦርድ ሊቀመንበር እና የትግራይ ልማት ማህበር ዋና ዳይሬክተር ተስፋይ ገብረ እግዚያብሔር ውይይቱን ሲከፍቱ ከተናገሩት ፦

" ስለደርሰብን ስብራት ኣብዝተን በማውራት የምንቀይረው ብዙ ኣይኖርም።

በትንሹ ከተግባባን፣ በብዙ ከሰራን በመከራ ላይ ላለው ህዝባችን ልንደርስለት እንችላለን።

ሁኔታው ልትገነዘቡ የመጣቹህ እንግዶች፣ ትላንት ዕዱልን ኣጥታቹህ ሞራላዊና ህጋዊ ግዴታቹ ሳትወጡ ለቀራቹህ ሁሉ፣ ዛሬም ህዝባችን ስቃይ ኣለበቃም እና፣ ድምፃቹህ፣ እውቀታቹህ፣ ጉልበታቹህ ያስፈልገዋል እና

✓ መጠልያ ውስጥ ያሉት ወደ ቀያቸው፣ የተሰድዱትም ወደ ኣገራቸው

✓ ተማሪዎች ወደ ናፈቃቸው ትምህርታቸው፣ ሰራቶኞችም ወደ ስራቸው፣

✓ ህመምተኞች የሚፈልጉት መድሃኔት እንዲያገኙ፣ የተማላ የምግብ ኣቅርቦት እንዲኖር፤

✓ ነፃ የዜጎችና የሸቀጦች እንቅስቃሴ እንዲኖር፣ የባንክ ኣገልግሎት እንዲጀመር በፍፁም ቅንነት ድምፃቹ እንድታሰሙ፣ የምትችሉትን ሁሉ እንድትሰሩ በታላቅ ትህትና እጠይቃቸዋለሁኝ፣ ትችላላቹም። "

(ሙሉ ንግግራቸው ከላይ ተያይዟል)

Photo : Tikvah Family (Mekelle)

@tikvahethiopia